Saturday, July 13, 2013

“ከማያውቁት መላዕክ የሚያውቁት ሰይጣን”

ከማያውቁት መላዕክ የሚያውቁት ሰይጣን

     በቅርቡ /ሚኒስትሩ ከነጋዴዎች ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ስለስደተኞች ጉዳይ ሲናገሩ፣ ቀደም ሲል የአረብ አገራትን የቤት ሰራተኞች ፍላጎት የሚሞሉት እንደ እነፊሊፒንስ ያሉ አገራት እንደነበሩ ጠቅሰው፣ አሁን ግን እነሱ ስላደጉና ዜጎቻቸውን በየአገራቸው ለመቅጠር ስለቻሉ ተረኞቹ የእኛ አገር ዜጎች ሆነዋልበማለት ካስረዱ በኋላ መፍትሄው እንደ እነ ፊሊፒንስ ማደግ ብቻ ነውብለዋል (ይሄ ነው ከፕሮፓጋንዳ የፀዳ መልስ ማለት!) እስከዛ ግን የኢቴቪ ጋዜጠኛዋ እንዳደረገችው ቢያንስ በህገወጥ ደላሎች አማካኝነት የሚደረገውን ጉዞ ለመግታት ብዙ ውይይቶች፣ ብዙ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች በማድረግ በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መቀነስ ይቻላል፡፡ ይሄኔ ፕሮፓጋንዳ ከእነአካቴው
አያስፈልግም፡፡ መርሳት የሌለብን ምን መሰላችሁ በአገሩ የሥራና የእድገት እድል እያለ ደቡብ አፍሪካም ሆነ አረብ አገር ለመጓዝ የሚመርጥ ማንም የለም (ከማያውቁት መላዕክ የሚያውቁት ሰይጣንይባል የለ!)
     በነገራችሁ ላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችም እኮ እየተሰደዱ ነው፡፡ እነሱ ግን በህገወጥ ደላላ ተታለው
አይደለም፡፡ የስደት ምክንያታቸውም እንደሌሎች ዜጎች ኢኮኖሚያዊ ሳይሆን ፖለቲካዊ ነው፡፡ እኔ ግን
በተቃዋሚዎች ስደት የአንዳንድ ኢህአዴግ arm twister ወይም እጅ ጠምዛዥ የሚላቸውን ማለቴ ነው) እጅ አለበት፡፡ ተቃዋሚዎች ግን ለአመራሮችም ሆነ ለአባላቶቻቸው ስደት ተጠያቂው ማነው ሲባሉ ጣታቸውን የሚሰነዝሩት ኢህአዴግ ላይ ነው፡፡ እንዴት ሲባሉም ገዢው ፓርቲ እያደረሰብን ነው የሚሉትን በደል ዘርዝረው ያስረዳሉ፡፡ ከተለመዱት እስርና ወከባ በተጨማሪ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታችንን ተነፍገናል የሚሉት ተቃዋሚዎች፤ በአገራቸው ጉዳይ ባይተዋር መደረጋቸውንም ይናገራሉ (በህዳሴው ግድብ ዙሪያ አላማከረንምየሚል ቅሬታቸውን ልብ ይሏል) ኢህአዴግ ከህዝብ ጋር ከተገናኘን አሲረን ሥልጣን የምንቀማው ስለሚመስለው መፈናፈኛ አሳጥቶናልየሚሉት ተቃዋሚዎች፤ ለዚህ ነው አመራሮችም ሆኑ አባላት የሚሰደዱት ባይ ናቸው፡፡ ዲሞክራሲ ለኢህአዴግ የምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነውየሚለው ኢህአዴግ ግን የተቃዋሚዎች ስደት ዲሞክራሲው ያመጣው ነው ይላል፡፡ (እድገቱ ያመጣው ነው እንደሚለው መሆኑ ነው!)እኔ ግን የስደት ነገር በጣም የሚያሳስበኝ መቼ መሰላችሁ? ቱባ ቱባ የኢህአዴግ ባለስልጣናት መሰደድ የጀመሩ ዕለት ነው (ምን አጥተው
እንዳትሉኝ ብቻ!) ለነገሩማ የተቃዋሚዎችን ያህል አይሆኑም እንጂ ስንቶቹ ለኮንፍረንስና ለህክምና እያሉ ተሰደው የለ፡፡ (የኢህአዴግ አባላትም ሲሰደዱ ተቃዋሚ ይሆናሉ አይደል?) ወዳጆቼ መሪዎች ስደት ከጀመሩ እኮ ሃይለኛ ቀውስ ነው የሚፈጠረው፡፡ (ተሰደው ካላየን አናምን እንዳትሉኝ!)
ከአንድናት ኢትዮጵያ ብሎግ


ኢትዮጵያ ክብር ለዘላለም ትኑር!

No comments: