Tuesday, June 30, 2015

በነጻ እንዲፈቱ በፍርድ ቤት የተወሰነላቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በድጋሚ ታሰሩ

ኢሳት ዜና (ሰኔ 23 2007)
ሰሞኑን ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ወስኖላቸው ፖሊስ በድጋሚ ለእስር በዳረጋቸው አራት የፓርቲ አባላት ላይ አቃቢ ህግ ይግባኝ ጠየቀ።
ተከሳሾች የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸው ከውጭ ሆነው ለመከታተል ጥያቄ ቢያቀርቡም ከሳሽ አቃቢ ህግ ተቃውሞን እንዳቀረበ ከሀገር ቤት የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
ጉዳዩን ለማየት የተሰየሙት ዳኛ ተከሳሾች እስካሁን ድረስ በእስር ቤት ስለመቆየታቸው የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው አንደኛ ተከሳሽ ባለመቅረቡ ምክንያት ክርክሩ ሰኔ 24 2007 እንዲካሄድ ውሳኔ ሰጥተዋል።
ከወራት በፊት መንግስት በሊቢያ የተገደሉ ኢትዮጵያዊያንን ድርጊት ለማውገዝ ጠርቶ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት አራቱ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ብጥብጥን ላማነሳሳት ተንቀሳቅሳችኋል ተብለው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሾች በሁለት ወር እስራት እንዲቀጡ ቢወስንም አራቱ ተከሳሾች ከተላለፈባቸው የእስር ጊዜ በላይ በእስር ቤት በመቆየታቸው ፍርድ ቤት እንዲለቀቁ ሲል ወስኗል ።
ይሁንና ተከሳሾችን ከፍርድ ቤት በር ላይ ጠብቆ ለእስር የዳረጋቸው ፖሊስ ሁሉንም ተከሳሾች በአዲስ አበባ ከተማ 6ተኛ ፖሊስ ጣቢያ ይዞ እንደሚገኝ ታውቋል።
ከሳሽ አቃቤ ህግ በበኩሉ ተከሳሾችን ሊለቅ ያልቻለው በተከሰሱበትና በተለቀቁበት ርዕስ ላይ ይግባኝ ስለጠየቀ መሆኑን አስረድቷል።
አቶ ኤርሚያስ ጸጋዬ፣ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ፣ ወይዘሪት ወይንሸት ሞላና፣ ቤተልሄም አካለ ወርቅ ከእስር እንዲፈቱ ውሳኔ ቢተላለፍባቸውም አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ይገኛል።
ባቀረበባቸው አዲስ ይግባኝ ላይ ክርክር ላማካሄድም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለረቡዕ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ከወራት በፊት መንግስት ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ከአንድ ሺ የሚበልጡ ለእስር ተዳርገው ከ 100 በሚበልጡት ላይ ክስ መመስረቱ የታወቃል።

እነ ወይንሸት ሞላ እያንዳንዳቸው 5000 ብር ዋስ ተጠየቀባቸው

•ነገ ደግሞ ይግባኝ በተባለባቸው ጉዳይ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ
መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤተልሄም አካለ ወርቅ ፖሊስ ምስክሮችን አስፈራርተውብኛል ካለው ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዛሬ ሰኔ 23/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት ቀርበው እያንዳንዳቸው የ5000 ብር ዋስ ተጠይቆባቸዋል፡፡
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እነ ወይንሸት ቀደም ብሎ ጉባኤንና ስብሰባን በማወክ በተከሰሱበት ወቅት ምስክሮቼን አስፈራርተውብኛል ያለው ፖሊስ ለምስክርነት የማረሚያ ቤት ፖሊስን ቢያስመዘግብም በዛሬው ዕለት ምስክሮቹን ይዞ መቅረብ ሳይችል ቀርቷል፡፡ በዚህም ተጨማሪ ቀጠሮ ጠይቆ የነበር ቢሆንም፣ እነ ወይንሸት የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀው እያንዳንዳቸው 5000 ብር ዋስ እንዲያስይዙ ፍርድ ቤቱ አዝዟል፡፡
እነ ወይንሸት ሞላ ቀደም ሲል የቄራ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲወጡ ውሳኔ በሰጠበት ጉዳይ ላይ የስድስተኛ ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀባቸው በሚል ነገ ሰኔ 24/2007 ዓ.ም ቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኘው ማስተዋል ፍቃዱን ጨምሮ ልደታ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ እነ ወይንሸት በፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ቢወሰንላቸውም ፖሊስ ውሳኔውን ባለማክበር አስሯቸው እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡
መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም ከጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ጋር በተያያዘ ብዙ ዜጎችን አስሮ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Monday, June 29, 2015

እነ ወይንሸት ሞላ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ ቆይተው ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት እንዲፈቱ ተወስኖላቸው ሰኔ 16/2007 ዓ.ም ከእስር ቤት ሲወጡ እንደገና በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ዛሬ ሰኔ 22/2007 ልደታ ፍርድ ቤት 11ኛ ምድብ ችሎት ቀርበው ቀደም ሲል ‹‹ሁከትና ብጥብጥ አስነስተዋል›› በሚል በተከሰሱበትና ከእስር በተለቀቁበት ክስ ላይ ይግባኝ ተጠየቀባቸው፡፡
አቃቤ ህግ እነ ወይንሸት የዋስትና መብታቸውን ተነጥቀው ጉዳያቸውን ማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ የጠየቀ ቢሆንም ዳኛዋ ‹‹በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ ከእስር የተፈቱ በመሆናቸው ዋስትና ሊከለከሉ አይገባም፡፡›› ብለዋል፡፡ ዳኛዋ እነ ወይንሸት እንደተለቀቁ እንጅ በእስር ላይ መሆናቸውን እንደማያውቁ ገልጸው 3 ወር ተፈርዶበት ቂሊንጦ የሚገኘው ማስተዋል ፈቃዱ ባለመቅረቡ፣ ከእሱ ጋር ረቡዕ ሰኔ 24/2007 ዓ.ም ቀርበው ክርክር እንዲጀምሩ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡ ሰኞ ሰኔ 29/2007 ዓ.ም ውሳኔ እንደሚሰጡም አሳውቀዋል፡፡
ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ኤርሚያስ ፀጋዬ በነፃ፣ እንዲሁም ወይንሸት ሞላና ዳንኤል ተስፋዬ ሁለት ወር እስር ተወስኖባቸው ሁለት ወር በመታሰራቸው እንዲፈቱ ተፈርዶላቸው ከእስር ሲለቀቁ እስር ቤት በር ላይ በፖሊስ ተይዘው ወደ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ መዛወራቸው ይታወቃል፡፡ ወይንሸት፣ ኤርሚያስና ዳንኤል ሰኔ 19/2007 ዓ.ም በቄራ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ቀርበው ፖሊስ ‹‹ከእስ እንዲለቀቁ በተወሰነላቸው ወቅት ምስክሮችና የምስክሮቹ ጓደኞች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ አድርሰውብኛል›› የሚል አዲስ ክስ አቅርቦባቸው 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ፡፡ በዚህ አዲስ ክስ ላይ የፖሊስን ምስክር ለመስማት ነገ ሰኔ 23/2007 ቄራ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

እነ ቴዎድሮስ አስፋው ጥፋተኛ ተባሉ



• ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ እንዲሰፍን እየታገልኩ መሆኔ በክስ ማቅለያነት እንዲወሰድልኝ›› ወጣት ቴዎድሮስ አስፋው
ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ ታስረው ‹‹ኢህአዴግ ሌባ ነው፣ ህገ መንግስቱ ወረቀት ነው፣ ታፍነናል፣ ታስረናል፣ መለስ የሞተው ደንግጦ ነው፣ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በቁሙ የሞተ ነው፣ ቴዎድሮስ ለህዝብ ነው የሞተው›› በሚል ብጥብጥና ሁከት ፈጥራችኋል፣ የሀሰት ወሬ አውርታችኋል ተብለው የተከሰሱት እነ ቴዎድሮስ አስፋው ዛሬ ሰኔ 22/2007 ዓ.ም አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡
ጥፋተኛ ከተባሉት መካከል አንደኛ ተከሳሽ ቴዎድሮስ አስፋው የሰማያዊ ፓርቲ አባል ሲሆን ያሬድ ደመቀ እና አንዋር ከድር የፓርቲው አባል አይደሉም፡፡ እነ ቴዎድሮስ ጥፋተኛ የተባሉት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀለኛ ህግ አንቀጽ 486/ለ የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ነው ተብሏል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት ቴዎድሮስ ‹‹የተመሰረተብኝ ክስ የሀሰት ነው፡፡ የተሰማው ምስክርም የሀሰት ነው›› ሲል ውሳኔው ፖለቲካዊ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
ዳኛው አንዴ ጠፋተኛ መባሉን በመግለፅ ውሳኔው ፖለቲካዊ መሆኑን ቅሬታ ማቅረብ እንደማይችል ገልጸው ማቅለያ እንዲያቀርብ በጠየቁበት ወቅትም ወጣት ቴዎድሮስ ‹‹የተባለውን ወንጀል ፈጽመዋል ብንባል እንኳ የነበረው ሁኔታ መታየት አለበት፡፡ 30 ኢትዮጵያውያን በጭካኔ የታረዱበት ወቅት ነው፡፡ በታሪካችን እንዲህ አይነት ውርደት አጋጥሞን አያውቅም፡፡ መንግስት የታረዱትን ወገኖቻችን ኢትዮጵያውይነት በሚክድ መልኩ ያወጣው መግለጫ ደግሞ የሚያበሳጭ ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆን አለመሆናቸውን ላጣራ ከማለቱ በተጨማሪ ለሚሰደዱት ኢትዮጵያውያን መቀጣጫ እንደሚሆን መግለፁ ደግሞ በጣም አሳፋሪ ነበር፡፡ ተፈፀመ የተባለውን ነገር እውነት ነው ቢባል እንኳ በዚህ ስሜታዊ በሚያደርግ ሁኔታ የተፈፀመ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል›› ብሏል፡፡
ወጣት ቴዎድሮስ አክሎም ‹‹እኔ ኢትዮጵያ ውስጥ ህግ ተርጓሚው ገለልተኛ ሆኖ እንዲሰራ በመታገል ህግ እንዲሰፍን የራሴን አስተዋጽኦ እያደረኩ እገኛለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ እንዲሰፍን እየታገሉ ከሚገኙት ወጣቶች መካከል አንዱ መሆኔ በክስ ማቅለያነት እንዲወሰድልኝ›› ሲል የክስ ማቅለያ አቅርቧል፡፡ ከቴዎድሮስ በተጨማሪ ያሬድ ደመቀና አንዋር ከድርም የክስ ማቅለያዎችን አቅርበዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም ቴዎድሮስ ለክስ ማቅለያነት ያቀረባቸው የመንግስት መግለጫ፣ ህግ እንዲሰፍን እየሰራ መሆኑና ቀሪዎቹ ተከሳሾች በማቅለያነት ያቀረቧቸው ጉዳዮችን በማስረጃ እንዲያቀርቡና በማቅለያነት የቀረቡት ጉዳዮችም ማቅለያ መሆን እንደሚችሉና እንደማይችሉ ለመወሰን ለሐምሌ 3/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር


Friday, June 26, 2015

የኢትዮጵያ መንግስት የአንዳርጋቸዉ ጽጌ አያያዝ የሁለቱን አገሮች ወዳጅነት አደጋ ላይ እንዳይጥል እንግሊዝ አሳሰበች


የተቃውሞ መሪውና ዜጋውም የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን የኢትዮጵያ መንግሥት የያዘበት ሁኔታ “ጨርሶ ተቀባይነት የሌለውና በሁለቱ ሃገሮች መካከል ያለውን ግንኙነትም የሚጎዳና አደጋ ላይ የሚጥል ነው” ሲል የእንግሊዝ መንግሥት ኢትዮጵያን ትናንት አሳስቧል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት የእንግሊዝን መንግሥት ስሞታ ያስተባብላል፡፡
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሃሞንድ ትናንት በሰጡት መግለጫ በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር መወያየታቸውንና “ብርቱ” ያሉትን መልዕክት ያስተላለፉላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የእንግሊዙ የዜና አውታር ሮይተርስ እንደዘገበው ሚስተር ሃሞንድ ከዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር ከተነጋገሩ በኋላ በሰጡት መግለጫ “እንግሊዛዊው ዜጋ አንዳርጋቸው ፅጌ ከታሠሩ አንድ ዓመት ቢያልፍም የመታሠራቸውን ጉዳይ በሕግ ፊት ለመሟገት እንኳ ሳይቻል ብቻቸውን ተነጥለው እንዲቆዩ ተደርጓል” ብለዋል፡፡
የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አክለውም የአቶ አንዳርጋቸው ደኅንነት በእጅጉ እያሳሰባቸው መሆኑንና የእንግሊዝ ቆንስላ አቶ አንዳርጋቸውን በየወቅቱ ማግኘት እንዲችል ለማድረግ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቃል ቢገባም በተደጋጋሚ የቀረቡት ጥያቄዎች ግን ያለመልስ መምከናቸው ያሳዘናቸው መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የእንግሊዝ መንግሥት ባለፈው ነኀሴ ሎንዶን የሚገኙትን የኢትዮጵያ ጉዳይ ፈፃሚ መልዕክተኛ ጠርቶ አቶ አንዳርጋቸው ላይ ቀደም ሲል ተላልፎ የነበረው የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እንደማይደረግ ማረጋገጫ እንዲሰጠው ጠይቆ እንደነበር፡፡
ጉዳዩ በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል ያለውን ግንኙት ወደአደጋ እየወሰደው እንደሆነ ማስጠንቀቃቸውን ሮይተርስ አክሎ ዘግቧል፡፡
“ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ያቀረብንላትን ጥያቄ ሳትቀበል መቅረቷ ተቀባይነት የለውም፡፡ የጉዳዩ አለመንቀሳቀስ እንግሊዝ በብዙ የምታከብረውን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለት ወገናዊ ግንኙነት ይጎዳዋል፡፡” ብለዋል ፊሊፕ ሃሞንድ፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አቶ አንዳርጋቸው የተያዙት በጥሩ ሁኔታ ነው ስትል ኢትዮጵያ የለንደንን ስሞታ ዛሬ አስተባብላለች፡፡
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለሮይተርስ ሲናገሩ ባለሥልጣኖቻቸው ከእንግሊዝ ጋር ሲተባበሩ መቆየታቸውንና አቶ አንዳርጋቸው የሚገኙበትንም ሁኔታ እንደሚያውቁ ገልፀዋል፡፡
“አንዳንዶች ሊስሉ የሚሞክሯቸው አሳዛኝ ታሪኮች መሠረተ ቢስ ናቸው” – ብለዋል አቶ ጌታቸው፡፡ አክለውም ይህ ሁኔታ በግንኙነቶቻችን መንገድ ላይ እንዲቆም ጨርሶ አንፈቅድም ብለዋል፡፡
“ይሁን እንጂ – አሉ አቶ ጌታቸው – እንግሊዛዊያኑ ወዳጀቻችን የሚጠይቁን አንድን የተፈረደበት ሽብርተኛ ያለቅድመሁኔታ እንድንለቅቅ ከሆነ ይህ የማይሆን ነገር ነው፡፡ ይህንን ይረዳሉ ብለን እናምናለን፡፡”
የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞን ለማፈን ጋዜጠኞችን፣ የመብቶች ተሟጋቾችን እና ብሎገሮችን እንደሚያስር እየገለፁ በየወቅቱ ቢከስሱም መንግሥቱ ግን በየወቅቱ ሲያስተባብል ይሰማል፡፡
Source: voanews

Abel Wabela: “To Fight Bystander Apathy…This is My Mission as a Human”

abel_wabela_freezone9bloggers_2
Abel Wabela. Drawing by Melody Sundberg.
In April 2014, nine bloggers and journalists were arrested in Ethiopia. Several of these men and women had worked with Zone9, a collective blog that covered social and political issues in Ethiopia and promoted human rights and government accountability. Four of them were Global Voices authors. In July, they were charged under the country’s Anti-Terrorism Proclamation. They have been behind bars ever since and their trial has only recently begun.
This marks the sixth post in our series – “They Have Names” – that seeks to highlight the individual bloggers who are currently in jail. We wish to humanize them, to tell their particular and peculiar stories. This week, Swedish blogger and artist Melody Sundberg writes about Abel Wabela, a member of Zone9 and the manager of Global Voices’ Amharic site.
I have never been to Ethiopia, but I have followed the never-ending trials of the bloggers closely through social media and conversations. A name often mentioned is that of Abel Wabela, a 28-year-old blogger, author and translator for Global Voices. During the first three months of the bloggers’ detention in Maekelawi*, Abel refusedto sign a prepared confession paper in which he, together with the other bloggers, were incriminated. For this, Abel underwent extreme torture. According to theEthiopian Human Rights Project (EHRP), he was beaten by a person using a stick, and his feet were whipped by someone using a computer plug cable. He was forced to lay on the floor while interrogators stomped on his back, neck and face. Since then, he has had to use a hearing aid as a result of worsened hearing impairment.
According to Endalk Chala, co-founder of the blogging group, Abel had suffered poor treatment even before his arrest. One day, three weeks before the arrest, Abel was beaten as he was walking home from work. Several people appeared and beat him so severely that he lost his consciousness, and they took his cell phone and laptop. He feared beating was a threat, intended to make him stop blogging. But Abel continued his work.
Abel Wabela. Photo courtesy of family.
Abel Wabela. Photo courtesy of family.
I wanted to know more about Abel, so I asked some of those close to him to describe their friend. Endalk Chala describes Abel as the most kindhearted and wonderful soul. Abel is a man of knowledge and a great conversationalist, and he believes in open and honest discussions. Jomanex Kasaye describes Abel as being straight forward and knowing what he stands for. At the same time, he is very humble. Abel is always hungry for more knowledge. He likes to spend his time in discussions with historians, university lecturers and authors. His faith is important to him. He loves attending in church. He often visited prisoners, having the country and its people in his heart. He always thinks of others rather than himself.
The heartless treatment of Abel continued after his detention in Maekelawi. Following one of the trials in February, prison officials had forgotten to handcuff him on the bus heading back to the prison. For this, Abel was punished. They tied him up with dog chains for the whole day, and took away his hearing aid. During a trial in May, Abel was once again punished for using his right to expression. Abel questioned the judges for not letting the detainees speak. For this, he was sentenced to four months for contempt of court.
The kind of treatment Abel has been put through could break anyone. Still, Abel has kept showing resistance. I ask myself: What is it that makes someone risk being jailed, beaten and tortured? Reading Abel's latest letter, I find the answer:
My purpose is to communicate. My aim is to learn. My reason is to engage in a deep insightful intuitive understanding of life and fight bystander apathy. This is my mission as a human. It is not a task I was given from a stranger. I will not allow anyone to trample on this basic right. I will not bargain with anyone whether they are people of political power, individuals, institutions or even a society to give away my basic speech right. I practice my free speech rights in a public sphere, in my own private space, on social media, in prison, in a court room, in a police interrogation rooms. I use my free speech rights responsibly without hindering other peoples’ rights and I want to practice it everywhere. In hindsight warnings, intimidations, arrest and torture have not stopped me from exercising my free speech rights neither they do in the future.
“To fight bystander apathy… This is my mission as a human.” The sentences form a simple answer to a difficult question. The reason Abel keeps using his freedom of expression is because it is a basic right that can be exercised everywhere in every situation. He has made the choice to use this right, because speaking out against injustice is to fight bystander apathy. I am more than certain that he will continue defending this right for the rest of his life.
We live in a world where some label the use of freedom of expression as an act of terrorism. We also live in a world where others are sacrificing their freedom while defending our right to speak our minds. The Zone9 Bloggers defended human rights. They chose to stand up against injustice. They chose to speak the truth. For this, they were robbed of their freedom.
I do not know Abel today, but I look forward to the day I will.
Following their arrest, the bloggers and journalists were jailed in Maekelawi. Maekelawi is the Federal Police Crime Investigation Sector in Addis Ababa. Political prisoners, journalists, bloggers, protest organizers among others are held there before proceeding to prison. Human Rights Watch has reported about torture, coercive interrogation methods and poor detention conditions taking place there.
Source: globalvoicesonline

Ethiopia: Country Reports on Human Rights Practices for 2014 – US Department of State

This summary is not available. Please click here to view the post.