Wednesday, July 31, 2013

በደሴ ከተማ መንግስት የገደላቸውን ሼህ ኑሩን በማስመልከት

በደሴ ከተማ መንግስት የገደላቸውን ሼህ ኑሩን በማስመልከት .. ያሰራጨውን ዘጋቢ ድራማ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች በግዳጅ እንዲመለከቱት እየተደረገ መሆኑ ተጠቆመ::

በደሴ ከተማ ከሳምንታት በፊት ጭለማን ተገን በማድረግ መንግስት ያስገደላቸውን የደሴ ከተማ የአህባሽ እምነት ፊት አውራሪ የነበሩትን ሼህ ኑሩን በማስመልከት መንግስታዊው የቴሌቪዥን ጣብያ ያሰራቸውን ዘጋቢ ድራማ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች በግዳጅ እንዲመለከቱት እየተደረገ መሆኑንን ምንጮች አስታውቀዋል፡፤

መንግስት ድርጊቱን አክራሪ ሙስሊሞች ናቸው የፈጸሙት በማለት ለርካሽ ፐሮፖጋንዳ ለመጠቀም በማሰብ ዘጋቢ ፊልሙ በገለልተኛ ወገን ተዘጋጀ በማለት በኢቲቪ ማሰራጨቱ የሚታወስ ሲሆን መንግስት ያሰበውን ያህል ውጤት እንዳላስመዘገበለት ለመወቅ ተችሏል፡፡

ኢቲቪ በሚያቀርባቸው መሰረተ ቢስ ዜናዎች እና ድራማዎች የኢትዬጲያ ህዝብ የተሰላቸ እና በኢቲቪ የሚሰራጩት ዜናዎችም ሆኑ ድራማዎች ከእውነት የራቁ ስለመሆናቸው ሁሉም በመገንዘቡ መንግስት በደሴ ከተማ የሰራው ሼህ ኑራዊ ሃረካት ውጤት ሳያስመዘግብለት በመቅረቱ በደሴ ከተማ ድራማው በሲዲ በማዘጋጀት በኢህአዴግ አባለት በኩል ለሽያጭ መቅረቡ ተሰምቷል፡፡ ሲዲውንም በየቦታው እየዞሩ በማስገደድ እየሸጡ እንደሚገኙ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በተጨማሪም ድራማው በደሴ ከተማ በሚገኝ ትልቅ አስክሪን እንዲታይ የተደረገ ሲሆን በቀበሌ አዳራሾች እና በወጣት መዝናኛ ማዕከሎች ውስጥም ሳይቀር የከተማዋን ነዋሪዎች በየቤቱ በመግባት እንዲሰበሰቡ በማድረግ ድራማውን እንዲከታተሉ እያስገደዱ መሆኑ ታውቋል፡፤ 

በኢቲቪ የሚሰራጩ ዝግጅቶችን አብዛኛው ህዝብ በበውሸት በሚቀርቡት ዜናዎች እና ድራማዎች በመማረሩ መከታተል ያቆመ መሆኑን መንግስት ስለተረዳው በግዳጅ በየቀበሌው እና በወጣት መዝናኛ ማዕከላት ህዝቡን በማስገደድ የሼህ ኑራዊ ሃረካትን ድራማን ማሳየት ግድ እንደሆነበት ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በደሴ ከተማ የሚገኙ የቀበሌ ሰራተኞች መደበኛ ህዝብን የማገልገል ስራቸውን እርግፍ አድርገው

No comments: