Wednesday, July 31, 2013

የአዲስ አበባ ደህንነቶችና ፖሊሶች የአንድነት አባል ላይ ድብደባ ፈፀሙ

የአዲስ አበባ ደህንነቶችና ፖሊሶች የአንድነት አባል ላይ ድብደባ ፈፀሙ
=======================================
የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ አመራር አባል የሆነው ወጣት ብርሃኑ ገረፋ ትናንት ሐምሌ 22 ቀን 2005 ዓ.ም. ሳሪስ አካባቢ የፓርቲውን በራሪ ወረቀት ሲበትን በደህንነትና በ6 ፖሊሶች በህገወጥ መንገድ መታሰሩን ፓርቲው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት አስታውቋል፡፡ ወጣት ብርሃኑ በደህንነት አባሉ በመሳሪያ ሰደፍ ጀርባውንና ጭንቅላቱን ከመመታቱ በተጨማሪ ፖሊሶችም እጁን ጠምዝዘው በቦክስ ግራ ጉንጩን መመታቱ ተጠቁሟል፡፡ በእስር ቤት ውስጥ አንድ ቀን አሳድረው ካንገላቱ በኋላ ዛሬ ሐምሌ 23 ቀን 2005 ዓ.ም. በመታወቂያ ዋስ መለቀቁ ታውቋል፡፡
ወጣት ብርሃኑ የፀጥታ ኃይሎች ሲይዙት እጁን በካቴና እንደወንጀለኛ አስረው ሳሪስ አቦ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በእግር ከወሰዱት በኋላ ወደ አቃ ቃሊቲ ፖሊስ መመሪያ ወስደው ማሳደራቸው ታውቋል፡፡

No comments: