Friday, September 27, 2013

The Swedish involved in corruption in Ethiopia

The Swedish involved in corruption in 

Ethiopia 

Swedfund trapped by its partner

Some Swedish investors are among the collateral damage from the recent wave of anti-


corruption arrests in Addis Ababa.

Several heads of companies are among the 54 people recently arrested and put on trial at 


the behest of the Ethiopian Ethics & Anti Corruption Commission (EACC). One of 

them is Fikru Maru, a Swede of Ethiopian descent, who is the founder and CEO of the 

Addis Cardiac Hospital (ACH). He is accused of tax evasion, illegally importing medical 

equipment and corruption of a government official. After his arrest, the investigators 

obtained permission from the Courts to freeze the bank accounts of his companies and the 

hospital. This places his partners in an awkward position, because the hospital is a joint 

venture between Fikmar Medical AB (Maru’s Swedish company), the Swedish firm Octopus 

Medical AB, the Swedish doctor Patrik Hjalmarsson and the public body Swedfund which 

had stumped up a portion of the funds to set up the venture. The hospital is already 

finding it difficult to continue functioning because its bank account has been frozen, but it 

could also be condemned to a hefty fine if Fikru Maru is found guilty.

የመንግስት የደህንነት መስሪያ ቤት ከወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት አለ

የመንግስት የደህንነት መስሪያ ቤት ከወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት አለ
original_al_amoudi_wearing_eprdf_tshirt_may_2005

መስከረም ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ፣ “ኢህአዴግን የፈተነ ወሳኝ ክስተት” በማለት የገለጸውን የሙስሊሞች እንቅስቃሴ አልሻባብ፣ አልቃይዳ ፣ ግንቦት ሰባት ፣ እና የኤርትራ መንግስት እንደሚደግፉት በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙሀን ቢገልጽም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ደግሞ የደህንነት ሀይሎች ቱጃሩን ሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲንን ከእንቅስቃሴው ጀርባ እንዳሉበት የሚጠቁም መረጃ ለመንግስት ባለስልጣናት ማቅረቡ ታውቋል።
በቅርቡ በወልድያ ከተማ የወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት አመጽ መንገድ ዘግተው ወደ ላሊበላ ፤ ሰቆጣ ፣ ደሴ እና አዲስ አበባ የሚደረጉ የትራንስፖርት ጉዞዎች እንዲስተጓጎሉ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመጹን አነሳስታችሁዋል የተባሉ 13 ታዳጊ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ የደህነነት ሐይሎች አጣራነው ባሉት መረጃ አመጹን ሼክ አላሙዲን ከጀርባ ሆነው ደግፈውታል።
የኢህአዴግ አመራር እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ የጸረ ሽብር ግብረ ሐይል በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ውይይት ካደረጉበት በኃላ ፣ በባለሀብቱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ባይቻልም በወዳጆቻቸው በኩል ምክር አንዲሰጣቸው በአቶ በረከት ስምኦን የሚመራ አንድ ቡድን መዋቀሩን ለማወቅ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ሼክ አላሙዲን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከታክስ እና ከግንባታ ጋር በተያያዘ ከመንግስት ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል። የደህንነት መስሪያ ቤት በባለሀብቱ እንቅስቃሴ ዙሪያ መረጃ እንዳገኘ ቢገልጽም፣ መረጃውን እንዴት እንዳገኘው አልታወቀም። አንዳንድ ወገኖች ግን የሼክ አላሙዲን ከህግ በላይ መሆን ያሳሳበው መንግስት፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ባለሀብቱን ለመምታት የፈጠረው ዘዴ ሊሆን ይችላል ይላሉ።
በጉዳዩ ዙሪያ ሼክ አላሙዲንን ወይም ወኪሎቻቸውን ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።
ሼህ አሊ አላሙዲን ለኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይታወቃል።

Thursday, September 26, 2013

የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው በፖሊስ እየተዋከበ ነው

የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው በፖሊስ እየተዋከበ 

ነው


ለቅስቀሳ ዛሬ ማለዳ ወደ ፈረንሳይ አካባቢ ተንቀሳቅሶ የነበረ መኪና በፖሊስ ቁጥጥር 

ስር መዋሉን መግለጻችን አይዘነጋም፡፡እውቅና ለተቸረው ሰላማዊ ሰልፍ 

የሚደረገውን ቅስቀሳ ለመቅረጽና የህዝቡን ስሜት ለመመልከት ካሜራና ላፕ ቶፕ 

በመያዝ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የተጓዘው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው 

ከሌሎቹ የተለየ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ በስፍራው የሚገኙ ምንጮቻችን 

ገልጸዋል፡፡

ፖሊሶች በሶሻል ሚዲያው ህዝቡን እየቀሰከስክና የተለያዮ ምስሎችን በመለጠፍ 

የመንግስትን ስም የምታጠፋው አንተ ነህ በማለት አሸናፊን ማዋከባቸውንና አካላዊ 

ጉሸማ እንዳደረሱበት ለማወቅ ተችሏል፡፡አሸናፊን ጨምሮ በኣሁኑ ሰዓት በፖሊስ 

ጣብያው ሰባት ሰዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

#Millionsofvoicesforfreedom #Ethiopia #UDJ

ኢሃዲግን የተፈታተነው ' የእምነት አክራሪነት ' ነው በሚል አጀንዳ ግራ የገባው ህወሐት ተሰብስቦ ግራ ሲጋባ ዋለ አሉ ::

ኢሃዲግን የተፈታተነው ' የእምነት አክራሪነት ' ነው በሚል አጀንዳ ግራ የገባው 

ህወሐት ተሰብስቦ ግራ ሲጋባ ዋለ አሉ ::


ህዝባዊ በሆኑ ድርጅቶች መንፈሳዊ ነክ ጹፎች ስ እ ሎ ች :መለጠፍ መዝሙሮች 

:የስልክ ጥሪዎችን ጨምሮ ማሰማት ፈጽሞ የተከለከለ እና እምነታዊ ማክረር ነው 

ሲሉም ኢሃዲጋዊ ህግ ደንግገው ስብሰባውን ጨረሱም ተባለ ...ጉድ በል ጎንደር 

በመሃይም ነገር


-በአደጉት አገሮች ውስጥ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሲጨፍሩ ሲያወሩ የሚውሉ የአየር 

ሚዲያዎች ልክ በ ሰንበት እለት ሁሉም ጣቢያዎች ዘፈኖቻቸውን አቁመው : 

መንፈሳዊ መዝሙር እና ስብከት እስከ ረፋዱ ላይ ሲያሰሙ ይውላሉ::


- የኢሃዲግ ማ እከላዊ ኮሚቴ አባላት እነዚህን ሚዲያዎች ቢያገኝዋቸው ምን 

ሊያደርግዋቸው እንደሚችሉ አስቡ::


*ኢትዮጵያን እየተፈታተናት ያለው ጎጣዊ እና ድርጅታዊ አክራሪነት ነው እንጂ የ 

እምነት አክራሪነት አይደለም:: ስለዚህም በመንግስት እና ህዝባዊ ቦታዎች 

በየአደባባዮች እና መ/ቤቶች ውስጥ የተለጠፉ ..የማርክስ :የሌኒን የመለስ ፎቶ 

ግራፎች ይነሱ:: ለ እነዚህ ፓጋንት የወጡ ዘፈኖቻቸውም በ ሚዲያ መሰማት 

ይቁሙ:: በ ዛሚ :ሪፖርተር FANA ETV,ebs, fm 96 ..97..98 በየግዜው 

የሚነዙ ድርጅታዊ ስብከቶች ይቁሙ ::


አለበለዚያ እምነቶችን ሁሉ ከ ኢትኦጳ ምድር አጥፉና :እምነታችሁ ህ ወ አት ነው : 

ቤተ-መቅደሱም ቀበሌ ጣኦቱም መለስ ነው በሉን::

የሀይማኖት አቋም የእድገት መመዘኛ መስፈርት እንዲሆን ተወሰነ

የሀይማኖት አቋም የእድገት መመዘኛ መስፈርት እንዲሆን ተወሰነ
Bereket_simon

መስከረም ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ በረከት ስምኦን በተመራው የኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ውይይት ላይ ፣ የሀይማኖት አክራሪነት ከምርጫ 97 ቀጥሎ ከፍተኛ ፈታኝ አደጋ እንደሆነ ከተገለጸና ውይይት ከተካሄደ በሁዋላ የአገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ የሀይማኖት ጉዳይን እንደ አንድ የእድገት መመዘኛ መስፈረት እንዲተገብር ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በጉባኤው ላይ የሐይማኖት አክራሪነት የመንግስትን ተቋም በማፈራረስ እና ተከታዮቹ ነፍጥ አንስተው መስዋእት እንዲሆኑ በማነሳሳት ከፍተኛ የሆነ አደጋ ይፈጥራል ሲሉ አቶ በረከት ተናግረዋል፡
በኢትዮጵያ ታሪክ በዩዲት ጉዲት እና በግራኝ አህመድ ዘመን በከፍተኛ ሁኔታ የደረሰውን የመንግስት ውድመት ዳግመኛ ሊፈጥር የሚችል አዝማሚያ አለው ሲሉ የተናገሩት አቶ በረከት፣ ይህንን በተማረው ህብረተሰብ እየታየ ያለውን በመንግስት ላይ ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ ለመቋቋም ያስችል ዘንድ፣ በማንኛውም ሁኔታ በህዝብና በመንግስት ተቋማት ውስጥ መዝሙር ማዳመጥ ፤ የሐይማኖትን መልእክት የሚያንፀባርቁ ማንኛውንም ሃሳብ መለጠፍ ፤ መስበክ፤ የሞባይ መጥሪያ ድምጽ ማድረግ ፈጽሞ መከልከሉን ገልጸዋል።
መንግስት አክራሪነትን በአጭር ጊዜ ድምጥማጡን ሊያጠፋ የሚችለው በዚህ መንገድ ብቻ ነው ሲሉ የገለጹት አቶ በረከት፣ የኢህአዴግ ህልውና አደጋ ውስጥ የጣሉትን ሃይሎች ማፈን እና ማኛውንም መንገድ በመከተል መገደብ የሚቻለው የኢህአዴግ አባላትን በየደረጃው አሰልጥኖ ማሰተግበር እና የሐገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ ስርዓት የውጤት መመዘኛ አንድ መሰፈርት በማድረግ የሰራተኛውን ህልውና ጥያቄ ውስጥ በመክተት ነው ሲሉ አክለዋል።
የሐገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር የሀይማኖት ጉዳይን የሰራተኛው አንዱ መመዘኛ በማድረግ ለቅጥር ፤ለእድገት እና ለዝውውር መስፈርት አድርጎ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሰራ የ2006 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ ተቀርጹዋል፡፡

ወታደራዊ መኮንኖች የደሞዝ ይጨመርልን ጥያቄ አቀረቡ

ወታደራዊ መኮንኖች የደሞዝ ይጨመርልን ጥያቄ አቀረቡ

ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ካለፉት 8 ቀናት ጀምሮ ስብሰባ ላይ ሲሆኑ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ዋነኛው የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ታውቋል።
ከመቶ አለቃ በላይ ማእረግ ያላቸው ወታደራዊ መኮንኖች ስብሰባዎችን እያካሄዱ ያሉት የጄኔራሎች ስብሰባ ከወር በፊት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። በጄኔራሎቹ ስብሰባ ላይ ለሰራዊቱ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ተነስቶ የነበረ ቢሆንም፣ “ሰራዊቱ አሁን የሚያገኘው ደሞዝ ለኑሮው በቂ ነው” የሚል መልስ ከሰራዊቱ ዋና አዛዦች ተሰጥቷል።  በተሰጠው መልስ የተበሳጩት  ጄኔራል ሰአረ መኮንን ስብሰባ ረግጠው ወጥተው እንደነበር ታውቋል። ጄኔራሉን ለማረጋጋት ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ጄኔራል ሰአረ ለሰራዊቱ ደሞዝ እንዲጨመር አቋም ከያዙት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል አንዱ ናቸው።
ሰሞኑን በመካሄድ ላይ ባለው ከጄኔራል በታች ማእረግ ባላቸው መኮንኖች ስብሰባም   የደሞዝ ጭማሪና የኑሮ ውድነት ዋና አጅንዳ ሆኖ ቀርቧል።
በምስራቅ አካባቢ ባለው እዝ አንዳንድ መኮንኖች ” እኛ ቤተሰቦቻችንን ምግብ አብልተን ለማኖር አልቻልንም፣ እናንተ በሙስና በዘረፋችሁት ገንዘብ ልጆቻችሁን ውጭ አገር ልካችሁ ታስተምራላችሁ” በሚል አለቆቻቸውን በድፍረት መተቸታቸውን የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።   መኮንኖች ያቀረቡትን ጥያቄ የመደረክ መሪዎች ለመመለስ ሲቸገሩ ታይቷል።
መኮንኖቹ ስብሰባቸውን ሲጨርሱ ከተራ ወታደሮች ጋር የሚደረገው ስብሰባ ይቀጥላል ተብሎአል።
ከፍተኛ ቅሬታ እየተስተናገደበት ባለው ስብሰባ፣ ወታደሮቹ እንደ መኮንኖቹ ሁሉ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ሊያነሱ ይችላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድ ሻምበል የወለደውን ልጅ በእሳት ማቃጠሉ ታውቋል። በምስራቅ እዝ የሚገኘው ሻምበል ፈቃዱ በዳዳ ከሳምንታት በፊት በልጁ ላይ ቤንዜን በማርከፍከፍ ያቃጠለው ሲሆን፣ ልጁም ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አባቱ ደግሞ ቆስሎ ሆስፒታል ተኝቷል። ሻምበል ፈቃዱ በልጁ ላይ ይህን አሰቃቂ እርምጃ ለምን እንደወሰደ አልታወቀም።

ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሊገድብ ይችላል የተባለ መመሪያወጣ

ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሊገድብ ይችላል የተባለ መመሪያወጣ

protest 2
September 26 /2013

ከቅርብ ወራት ወዲህ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የአደባባይ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራት መጀመራቸውን ተከትሎ በኢትዮጽያ ሕገመንግስት አንቀጽ 30 መሰረት የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብትን ሊገድብ ይችላል የተባለ አዲስ መመሪያ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ማውጣቱ ተሰማ። አዲሱ መመሪያ ሰላማዊ ሰልፍ የማይደረግባቸው አካባቢዎችንና ጊዜያትን ለይቶ ያስቀምጣል።

 በዚሁ መሠረት በሃይማኖት ተቋማት፣ ሰፊ ህዝብ በሚገበያይባቸው የገበያ ቦታዎችና ህብረተሰቡ በብዛትና በስፋት በሚንቀሳቅስባቸው የስራ ቀናት እንዲሁም በስራ መግቢያና መውጫ ስዓታት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንደማይፈቀድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈሩትንና ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግናበመሰብሰብ መብት ላይ ያተኮሩትን ሀሳቦች በዝርዘር ማየቱ አስፈላጊ በመሆኑ፤ ህገ መንግስቱን በአግባቡለመተግበር የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀቱን ገልጿል።
 በውስጡም ህጉን በዝርዝር ለማስፈፀም የሚያስችሉ መመሪያዎችን ያካተተ ነው ተብሏል።
ሰላማዊ ሰልፉን የጠራው አካል ያሉበትን ሃላፊነቶችና  የፀጥታ አካላትን ሚና ምን እንደሆነ በዝርዝር ያስቀመጠ መሆኑ ታውቋል።
የመመሪያው ተልዕኮ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 30  ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ ማስፈፀምእንደመሆኑ ሁሉም ዜጋ በቅርቡ እንዲያውቅ ይደረጋል ብለዋል።
በዚሁ አንቀፅ ንዑስ ቁጥር 1 ላይ የሰፈረው ድንጋጌ ደግሞ ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋርበመሆን መሳሪያ ሳይዝ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንዳለበት ያስቀምጣል።

ከቤት ውጪ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰለማዊ ስልፎች በህዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግርእንዳይፈጥሩ ለማድረግና ሰላምን፣ ዲሞክራሲያዊ መብቶችንና የህዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱአግባብነት ያላቸው ስርአቶች ሊደነገጉ እንደሚችሉ በህገ መንግስቱ ላይ ተቀምጧል። 

የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ አዋጅ ቁጥር 31/83 ኢህአዴግ ወደሥልጣን እንደመጣከወጡ አዋጆች አንዱና ቀዳሚው ነው:: ይህንኑ መብት የሚያረጋግጥ ተጨማሪ ድንጋጌ በ 1987 አ.ምበአዋጅ ቁጥር 1/87 በጸደቀው ህገ መንግስት አንቀጽ 30 ስር ተቀምጧል:: በዚህ ሕግ መሰረት ሰላማዊሰልፍ ለማድረግ የሚፈልግ አካል ከ 48 ሰአት በፊት በአቅራቢያው ለሚገኘው የመስተዳድር አካልማሳወቅ እንዳለበት መስተዳድሩ ደግሞ የሰልፈኛውን ደህንነት የሚጠብቅ የጸጥታ ሀይል የመመደብ ግዴታየተጣለባቸው ሲሆን ሰልፉን በታቀደበት ቀን ለማካሄድ የማያስችል በቂ ምክንያት በተገኘ ጊዜመስተዳድሩ ይህንኑ በመግለጽ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ኀሳብ ማቅረብ እንደሚችል በአዋጁተመልክቷል:: በሰላማዊ መንገድ ተሰብስቦ ተቃውሞን መግለጽ ህገ መንግስታዊና ሰብአዊ መብት በመሆኑይህንን መብት የሚንድ መመሪያ የአዲስአበባ አስተዳደርም ሆነ የፌዴራሉ ም/ቤት የማውጣት በህገመንግስቱ የተሰጣቸው መብት እንደሌለ አንዳንድ የሕግ ባለሙያዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ይህ መመሪያ መውጣቱን ከአዲስአበባ ፖሊስ መረጃ ካገኘ በኋላ የፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችንና የአዲስአበባ አስተዳደር ኃላፊዎችን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር ሞክሮ እንዳልተሳካለት በይፋ መግለጹን በተለይ በግሉ መገናኛ ብዙሃን መዘገቡ ይታወሳል። የፓርቲው አመራሮች መመሪያ የወጣው የተቃዋሚዎችን በተደጋጋሚ ሰልፍ ለመውጣት የመጀመሩትን ጥረት ለማፈን ነው ማለታቸው ይታወሳል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የጠየቅናቸው አንዳንድ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች መመሪያ ወጥቷል መባሉን ከመስማት ውጪ ኮፒው ስላልደረሳቸው አስተያየት ለመስጠት እንደሚቸገሩ ተናግረዋል። ሆኖም በአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ያነበቡትና የሰሙት ዓይነት መመሪያ ወጥቶ ከሆነ ሕገመንግስታዊ መብትን የሚገድብ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም ብለዋል።

Wednesday, September 25, 2013

እኔን እሠሩኝ”



እኔን እሠሩኝ”

ነጋሶ ጊዳዳ
ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ በአንድ የታሪክ አጋጣሚ የዚህች አገር ርዕሰ-ብሔር የነበሩ ሰው ናቸው።ቢዘገይም፤ እየተጓዙበት ያለው ያረጀ ባቡር ለእርሳቸው ተስማሚ እንዳልሆነ በመገንዘብ የፖለቲካ አሰላለፋቸውን ቀየሩ። የአቋም ልዩነት በማሳየታቸው ሳቢያም፤ እርሳቸውን በችጋር ለመቅጣትና ለማንበርከክ ታስቦ በወጣ የመቅጫ ህግ ሊያገኟቸው የሚገቡትን እና ሲያገኟቸው የነበሩትን ጥቅማ ጥቅሞችና መብቶቻቸውን ተነፈጉ።(መቼም ኢህአዴግ አንድን ግለሰብ ለመቅጣት ሳይቀር ህግ ሚያወጣ ጎረምሳ መንግስት መሆኑን እናውቃለን)
ዶክተር ነጋሶን በዚያ ደረጃ ማንከራተት የኢትዮጵያን ህዝብ ከመናቅ የመነጨ ድርጊት ለመሆኑ ምንም የሚያጠራጥር ባይሆንም፤ኢትዮጵያን በምታህል ታላቅ አገር ላይ ፕሬዚዳንት የነበሩ ሰው መኖሪያ ቤትና መጓጓዣ መኪና አጥተው ሲንከራተቱ በመታየታቸው የተዋረዱት ገዥዎቹ ራሳቸው እንጂ ዶክተር ነጋሶ እንዳልሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነበር።
ለዚህም ነው ሁሌም ከተጠቃ ጎን መቆምን የሚያውቀውና በህሊና ዳኝነቱ የተመሰገነው የኢትዮጵያ ህዝብ ለዶክተር ነጋሶ ድጋፉን የገለጸላቸው። ዶክተር ነጋሶም የዋዛ አልነበሩምበና ለለመዱት ሊሞዚን ፊት ሳያሳዩት ከምዕመኑ ጋር ታክሲ ለመያዝ መጋፋቱን ለመዱ። የፈርዖን ወይንና ጮማ እንደታሰበው ሳያስገብራቸው እነሆ ላለፉት ዓመታት በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ውስጥ ታቅፈው እየታገሉ ይገኛሉ።
ብዙዎች፤በአንድ ቢሮ ውስጥ ከነበራቸው ውስን ሃላፊነት ሢሰናበቱ፤በሌላ ቦታ በሚያገኙት ከዚያ ዝቅ በሚል ቦታ ለመቀጠርና ዝቅ ብሎ ለመሥራት አቀበት ሲሆንባቸው ተመልክተናል። ከዚህ አንፃር እንደ ኢትዮጵያ ባለች አገር ፕሬዚዳንት ለነበረ ሰው ብዙም ባልጠናከሩ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ ታቅፎ ለውጥ ለማምጣት ለመታገል መወሰን፤ የሚደንቅ ነው።ዶክተር ነጋሶ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው በህይወታቸው የወሰኗቸውን እነዚህን ውሳኔዎች ሳጤን መጀመሪያ ወደ አእምሮዬ የሚመጣብኝ ጥያቄ ፦”እኚህ ሰው ወትሮውኑም እንዴት የኢህአዴግ አባል ሊሆኑ ቻሉ?” የሚል ነው። እነ አቶ ስዬ አንደነገሩንም ሆነ እኛም አንደምናውቀው ብዙዎቹ የኢህአዴግ አባላት(የዶክተር ነገሶን የኦህዴድ ጓዶች ጨምሮ) ድርጅቱን የተቀላቀሉት ፦” ለእህል ውሃ “ ነው። በዚህና በመሣሰሉት የሙስና ቅሌቶች ካልተበከሉ በጣም ጥቂት ሰዎች አንዱ ነጋሶ ናቸው። ነጋሶ፤ከድርጅታቸው ለመልቀቅ ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ሆነው ለመታገል ድፍረትና በራስ መተማመን ያገኙትም፤ ኢህአዴግ ከዚህ ጋር በተያያዘ ሊመዝባቸው የሚችል የክስ ካርድ እንደሌለው በማወቃቸውም ነው።
በተለየ መልኩ ፦“ኢህአዴግ ህገ-መንግስቱን ያክብር!” በሚል የተቃውሞ ድምፃቸው የሚታወቁት የቀድሞው ፕሬዚዳንት እና የአሁኑ የ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ዶክተር ነጋሶ እነሆ ዛሬ ፓርቲያቸው ከጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ጋር በተያያዘ የታሰሩባቸውን አባላት ለማስፈታት ወደ ጣቢያ ሄደው ራሳቸው በፖሊስ መታሰራቸውን ሰማን።
ከሳምንታት በፊት አንድነት ፓርቲ ለሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ ሲያሳውቅ -ወቅቱ ከአዲስ ዓመት ጋር ተያይዞ በዓላትና ግርግር የሚበዛበት ስለሆነ ሰልፉን ለመስከረም 19 እንዲያደርግ ፓርቲው ተጠየቀ። አንድነትም የመንግስት ጥያቄ ምክንያታዊ ነው በማለት ተቀብሎ ሰልፉን ለመስከረም 19 ለማድረግ ወሰነ። የፓርቲው አባላት የታሰሩት ለዚህ መንግስትና-አንድነት ፓርቲ ለተስማሙበት ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነው። ዶክተር ነጋሶም አባላቱ ወደታሰሩበት ወደ ሽሮ ሜዳ ፖሊስ ማዘዣ በማምራት ልጆቹ ህጋዊ በመሆናቸው እንዲፈቱ ቢጠይቁም ተቀባይነት ሳያገኙ ይቀራሉ። በመጨረሻም ፦”እነሱ ህገ-ወጥ ናቸው ከተባሉ እንዲቀሰቅሱ የላካቸው እኔ ስለሆንኩ እኔንም እሠሩኝ” አሏቸው። ፖሊሶቹም አሠሯቸው።
ለዶክተር ነጋሶ እና ለታሰሩት ወገኖች ድጋፋችንን የምንሰጠው በማዘን አይደለም። የታሰሩለትን ዓላማ ጠንክረን በማራመድ እንጂ።ከሩቅም ፣ከቅርብም ያለን ነፃነትን የተራብን ኢትዮጵያውያን ሁሉ የዶክተር ነጋሶ ፓርቲ መስከረም 19 ቀን በጠራው ሰልፍ በመሳተፍ፣ መሳተፍ ያልቻልን በሙያችንና በምንችለው መንገድ ከያለንበት ድጋፍ በመስጠት አጋርነታችንን እንግለጽ! “ጉድ ጉድ” ከማለት ባለፈ ጠንክረንና እጅ ለእጅ ተያይዘን ለተግባር እስካልተነሳን ድረስ ሁላችንም በየተራ መታሰራችን ይቀጥላል።

ሰማያዊ ፓርቲ ሕገ-መንግስት አረቀቀ

ሰማያዊ ፓርቲ ሕገ-መንግስት አረቀቀ

በረቂቅ ሕገ-መንግስቱ ላይ የውይይት መድረክ ለማዘጋጀት አቅዷል
semayawi 12



በቅርቡ የተመሰረተው የሰማያዊ ፓርቲ ‘‘የዜጎች የቃል ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ’’ በሚል መርህ ወደፊት የፖለቲካ ሥልጣን ሲይዝ የሚመራበትን አዲስ ህገመንግስት ማርቀቁን አስታወቀ። ረቂቅ ሰነዱ ላይ ምሁራንና ባለሙያዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ለሕዝብ እንደሚቀርብ ፓርቲው አስታውቋል።
የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት በአዲሱ ረቂቅ ሕገ-መንግስት ላይ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ውይይት እንደሚደረግ አስታውቀዋል። በውይይቱ ላይ ከዚህ በፊት የነበሩ ሦስት ህገ-መንግስቶች ድክመትና ጥንካሬ ምንድን ነው? አዲስ በሚረቀቀው ህገ-መንግስት ምሰሶዎች ምን ይሆናሉ፣ ስልጣንና ሕዝብን እንዴት ማገናኘት ይቻላል በሚሉ ወሳኝ ንድፈ ኀሳቦች ላይ የጠለቀ ውይይት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
‘‘የአሁኑ ሕገ-መንግስት የኢህአዴግ ፕሮግራም ቅጂ ነው’’ ያሉት ኢንጂነር ይልቃል እያረቀቁ ያሉት ሕገመንግሥት የሰነድ ዝግጅቱም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንና ምሁራን በሚያደርጉት ውይይት ከዳበረ በኋላ ለሕዝቡ ውይይት ቀርቦ ለባለሙያዎች ተመርቶ ዝርዝር ህጎች እንዲፃፉ ይደረጋል ብለዋል።
ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ የሚያካሂደው ሕዝቡን ለማነቃቃትና ለማስተማር አባላትንም ለመመልመል ቢሆንም በተጓዳኝ ፓርቲውን ለማጠናከርና ምን አይነት ስርዓት እንገነባለን የሚለውንም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ኢንጂነር ይልቃል ገልፀዋል።
ሰማያዊ ፓርቲ ሕገ-መንግስት ባለበት ሀገር ሌላ ሕገ-መንግስት ከማውጣት የሚያግደው ነገር እንደሌለ የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ ፓርቲው እያካሄደ ያለው ትግል በሕገ-መንግስት የማይመራን አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት የመተካት ስለሆነ አዲስ ህገ-መንግስት ማስፈለጉ የግድ ነው ብለዋል።
የፓርቲው ዋና አላማ በሀገሪቱ ሕጋዊ ስርዓትን መትከል በመሆኑ አሁኑ ባለው ሕግ-መንግስት በሚደረግ ምርጫ አብላጫ ወንበር ማግኘቱን ሲያረጋግጥ አዲሱን ሕገ-መንግስት ተግባራዊ ያደርጋል ብለዋል። በዚህ ሀገር ምርጫ ከተካሄደም ሰማያዊ ፓርቲ 99.6 በመቶ አብላጫ ወንበር ለማግኘት የሚያግደው ነገር እንደሌለም እርግጠኞች ነን ሲሉ አያይዘው ገልፀዋል።
ፓርቲው ከፖለቲካና ኢኮኖሚ አማራጭ ፕሮግራም በዘለለ አዲስ ህገ-መንግስት ማርቀቁ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ የፓርቲው አማራጭ ፕሮግራም የሚመነጨው ከረቀቀው ሕገ-መንግስት ነው ብለዋል። አዲሱ ህገ-መንግስት በሀገሪቱ ስለሚኖረው አጠቃላይ ስርዓትና መንግስታዊ አወቃቀር፣ የኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ የገበያ ስርዓት፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነት፣ የመሬት ፖሊሲ፣ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ ገዥ ኀሳቦች የሚመነጩት ከህገ-መንግስት እንደሆነ ገልፀዋል። የፓርቲው ፕሮግራም ከህገ-መንግስቱ የሚመነጩ ዝርዝርና ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በመሆኑ ቀዳሚውና ምሰሶው ሕገመንግስት ነው ብለዋል።
‘‘የኢትዮጵያ ችግር መጠነኛ ችግር ሳይሆን አጠቃላይ ሕጋዊ ስርዓት የመትከልና፤ የሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎችን መብት፣ ባህል፣ ታሪክን ግምት ውስጥ ያስገባ ስርዓት የማቋቋም ጉዳይ ነው’’ ያሉት ኢንጂነሩ አሁን ካለው ህገ-መንግስት ሊካተቱ የሚችሉት የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ ድንጋጌዎች እና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፈረመቻቸውን ድንጋጌዎች እንደሆኑም አስገንዝበዋል። ኢህአዴግ ለሀገር ደህንነትና ለህዝብ ጥቅም ሽፋን ከሕዝብ ነጥቆ የወሰዳቸው መብቶች በአዲሱ ህገ-መንግስት እንደሚካተቱ አመልክተዋል። ከኢህአዴግ መሠረታዊ ባህሪ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ የሕዝብን አንድነት የሚነኩ፣ የተዛባውን የፌዴራሊዝም ጉዳዮች እንደገና የሚታዩ መሆኑንም ጠቁመዋል።
አዲሱ ህገ-መንግስት በማርቀቅ ሂደት ላይ ታላላቅ ምሁራን የተሳተፉበት መሆኑን ያስረዱት ኢንጂነሩ ውይይቱ በቅርቡ የትና መቼ እንደሚደረግ ፓርቲው ያሳውቃል ብለዋል።
በተያያዘ ባለፈው ዕሁድ ፓርቲው የጠራው ሰልፍ አለመካሄዱን በተመለከተ ኢንጂነር ይልቃል ተጠይቀው ሕጋዊው ስርዓት የውሸት እንደሆነ፣ ኢህአዴግ ትልቅ የህዝብ ፍርሃት እንዳለበትና ሕዝባዊ ተቀባይነቱ ባዶ እንደሆነ የተገነዘብንበት አጋጣሚ ነበር ሲሉ መልሰዋል።
ባለፈው እሁድ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም ፓርቲው የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት በኩል ጃንሜዳ ማካሄድ እንደሚችሉ በመግለፅ በአንፃሩ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉን ለማካሄድ የጠየኩት መስቀል አደባባይ ነው በማለቱ ሰላማዊ ሰልፉ ከፓርቲው ጽ/ቤት በግምት አንድ መቶ ሜትር ከተካሄደ በኋላ ግንፍሌ ድልድይ ላይ በፖሊስ እንዲቋረጥ መደረጉ አይዘነጋም፡፡ (ሰንደቅ)

Kenya: Police Alert at Border With Ethiopia

Kenya: Police Alert at Border With Ethiopia



Security forces work to secure Westgate Mall after militants attacked.
Security has been tightened at the border of Ethiopia and Kenya following the Westgate attack. Marsabit county commissioner Isaiah Nakoru said the security apparatus in the region have been upscaled and the patrols intensified to ensure that the suspected attackers don't flee out or into the country. He said all police chiefs have been ordered to beef up their security checks and ensure no one gets in or out of the country.
Nakoru directed all lodges, hotels, bars and Public Service Vehicle operators in the region to review their security arrangements, including screening visitors. He was addressing officers at Marsabit Catholic Hall on Sunday when he presided over a forum for uniformed officers.

Nakoru said officers have been deployed in communal places such as churches to check on the security. He said adequate security measures have been put in place to avert the terrorist attack by the al Shabaab.

The former Ethiopian president Dr. Negaso Gidada has been detained



The former Ethiopian president Dr. Negaso Gidada has been 

detained this afternoon in a police station in Bole district, 

Addis Ababa.

Dr. Negaso Gidada is the chair person of the Unity for 


Democracy and Justice Party (UDJ), one of the most 

important opposition political parties working under the 

narrowest political landscape in Ethiopia.



The party has been in a peaceful struggle campaign, 

“Millions of Voices for Freedom” since 3 months ago. On the 

coming Sunday, the campaign is expected to be completed 

with public demonstration.

ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አሰረ Ethiopian former Presidant and UDJ's current Chair Man Dr. Negasso Gidada is arrested by Ethiopian government

Ethiopian former Presidant and UDJ's current Chair Man Dr. 

Negasso Gidada is arrested by Ethiopian government

አንድነት ፓርቲ መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር 

ለሚያደርገው ሰላማዊሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የማነ አሰፋ፣ዳንኤል ሙላት፣ 

ወንድምአገኝ አስፋው ፣ መሳይ ትኩ፣ አብርሀም ታደለ፣ እስማኤል ዳውድ ፣ወርቁ 

እንድሮ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን ተከትሎ ወደ ጉለሌ 

ሽሮሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ያመሩት የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ 

መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ለፖሊሶቹ “እነዚህን ልጆች ለቅስቀሳ ያሰማራሁት 

እኔ ነኝ፤ እነሱን ለቃችሁ እኔን እሰሩኝ” ብለዋል፡፡ ፖሊሶቹም “አባሎቻችሁንም 

አንለቅም እርሶም አይወጡም” በማለት የቀደሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት 

አስረዋቸዋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩት ሽሮሜዳ አካባቢ 

ሲቀሰቅሱ የታሰሩ አባላት እንዲፈቱ ለመጠየቅ ሄደው ነው 

የታሰሩት"

#Millionsofvoices

Ethiopian dictators government! Please listen


Ethiopian dictators government! Please listen if you have 

functioning ears and a processing brain.


The major concern for your victims and perhaps for any 

humane- Ethiopian citizen is your dictatorial rule, your 

boundless greed, your endless mass murder, crime against 

humanity and genocide;listennnnnnnnnn............


stop murdering your own people,stop against humanity...


We need freedommmmmm


Free all poltical prisoners in Ethiopia.


Freedommmmmmmmmmmm

አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ!


አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ!


--------------------------


የኢትዮጵያ ወጣት ሆይ! ጭቆና፣ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብት ረገጣ፣ ድህነት፣ 

ሙስና፣ ጠባብ ብሄርተኝነት፣ እስራት፣ እንደ ባይተዋር ከአገርህ መባረርና ስደት 

እንደጠናብህ ራስህም ታውቀዋለህ፡፡ 
ይህን ሁሉ የህዝቡን ችግር፣ ፍርሃት፣ በመካከላችን ያለውን መከፋፈል አይተን ዝም 

ብንለው ያለ እቅድ እንደ ፍልፈል በቆፈረው መንገድና ጎዳና ሰላማዊ ሰልፍ ማገድ፣ 

አደባባዮቻችንን መከልከል፣ መልዕክተኞቹን ማሰሩን ቀጥሎበታል፡፡


አንደኛ መብቶችህን ተቀምተሃል፣ ሁለተኛ በእምነትህ ጣልቃ ገብቶብሃል፣ ሶስተኛ 


በብሄር ከፋፍሎሃል፣ አራተኛ በአገርህ በእኩልነት መኖር አልቻልክም፣ አምስተኛ 

በሙስና አገርህ ተመዝብራለች፣ ስድስተኛ ሰንደቅ አላማህን አዋርዷል፣ሰባተኛ አገርህ 

ወደኋላ ቀርታለች… ምን ቀረህ? እውነት፤ በወጣትነት ዘመንህ ይህን ሁሉ ችግር 

እያየህ ዝም ያልህ እንደሆነ እንደ ቀደመው ጊዜ ሁሉ ባይተዋር ሆነህ ትኖራታለህ፡፡ 

አሁንም በአብዮታዊ ዴሞክራሲ እየማለ አይምርህም!


ጥሪውን እየሰማህ፣ ኑሮና ችግር፣ ጭቆና፣ ስደትና ሌሎች በርካታ ችግሮች 


እያንገበገበህ የቀረህ እንደሆነ ሰልፉ ላይ የተገኘነው ፈሪ፣ የአገር ሸክም፣ ሀሞት 

የሌለው እያልን በመሳለቅ አንምርህም፡፡ ጥሪውን የተቀበልክ እንደሆነ ግና እሁድ 

በጧት ቀደም ብለህ መስከረም 19 ወደ መስቀል አደባባይ ዝለቅ ከዛው እንገናኝ፡፡ 

33ቱ ፓርቲዎችና የተማረሩ የኢህአዴግ ካድሬዎችም ሳይቀር ከየ አቅጣጫው ወደ 

መስቀል አደባባይ ይዘምታሉ፡፡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በአደባባዩ ተገኝተው 

ድምጣቸውን ለማሰመት ቃል ኪዳን ገብተዋል፡፡ 


እስከዛው ድረስ ቸር ይግጠመን!

ደጃች ውቤ ‹‹ውቤ በረሃ›› ሠፈር ሊፈርስ ነው Dejach Webe (Webe Berha)

ደጃች ውቤ ‹‹ውቤ በረሃ›› ሠፈር ሊፈርስ ነው Dejach Webe (Webe Berha) 

ታምሩ ጽጌ, EthiopianRepoter.com
ደጃች ውቤ ሠፈር ሊፈርስ ነው
‹‹በቅርስነት ሊጠበቅ ሲገባው በድንገት ሊፈርስ ነው መባላችን አሳዝኖናል›› የአካባቢው ነዋሪዎች
‹‹በችኮላ የሚሆን ሳይሆን ተማሪዎችን ታሳቢ ያደረገ ዕቅድ ነው›› የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር
ከአዲስ አበባ ከተማ ምሥረታ ጋር ተያይዞ በቀደምትነት ከተመሠረቱ አካባቢዎች ቀዳሚነቱ የሚነገርለትና በተለምዶ ‹‹ውቤ በረሃ›› በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ደጃች ውቤ ሠፈር፣ በከፊል የሚፈርስ መሆኑ ለነዋሪዎች ተነገራቸው፡፡
በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ንዑስ ቀበሌ 05 ከጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት ወደ አፍንጮ በር በሚወስደው መንገድ በቀኝ በኩል በ11.6 ሔክታር ቦታ ላይ ያሉ ነዋሪዎች እንደሚነሱና ከ100 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው ሠፈር እንደሚፈርስ ለነዋሪዎቹ የተነገራቸው፣ መስከረም 11 ቀን 2006 ዓ.ም. በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ለግማሽ ቀን በተደረገ ውይይት ነው፡፡
ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በስተቀኝ በኩል በሚያስወጣው አስፓልት እስከ አደባባዩ ድረስ የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶች፣ የንግድ ቤቶችና የተለያዩ ቢሮዎች፣ ሆቴሎችና ምግብ ቤቶችን ጨምሮ እስከ አፍንጮ በር ድልድይ መዳረሻ ድረስ እንዲፈርሱ ምክንያት የሆነው፣ የባቡር ተርሚናልና ኃይል መስጫ ጣቢያ ሊገነባበት በመሆኑ እንደሆነ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተደረገው የግማሽ ቀን ስብሰባ እንደተነገራቸው ነዋሪዎቹ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፣ በጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አደባባይ ፊት ለፊት ከሚገኙት ንግድ ቤቶች ጀምሮ ከሦስት ሔክታር በማይበልጥ ቦታ ላይ ያሉ ነዋሪዎች እንደሚነሱ ቀድመው ተነግሯቸዋል፡፡ መስከረም 11 ቀን አስቸኳይና ድንገተኛ ስብሰባ እንዳለና ማንም ቢቀር ኃላፊነቱ የራሱ እንደሆነ በማስጠንቀቅ ነዋሪዎች እንዲገኙ ከተደረገ በኋላ፣ በሰሙት ጉዳይ እጅግ በጣም መደንገጣቸውንና ማዘናቸውን አስረድተዋል፡፡
የባቡር ተርሚናልና ኃይል መስጫ ጣቢያ ግንባታ በሚል በዳር ያሉት እንደሚነሱ በቅድሚያ ከተነገራቸው በኋላ በድንገት ‹‹የሚያስፈልገው ስምንት ሔክታር ነው፡፡ የሚቀረው 3.6 ሔክታር ተቆርጦ መቀጠል ስለሌለበት ለመልሶ ማልማት መፍረስ አለበት፡፡ ይኼ ደግሞ ተወስኖ አብቅቷል፤›› መባላቸው ተገቢ አለመሆኑንና ኅብረተሰቡን መናቅ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
በቅርስነት ተጠብቆ መኖር ሲገባው እንደ መርዶ ነጋሪ በድንገት እንደሚፈርስ መወሰኑን ለነዋሪዎች ማርዳት ማን አለብኝነት ነው የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ ከወረዳ እስከ ማዕከል ድረስ መረጃ በመጠየቅ በሁለትና በአራት ሚሊዮን ብር በቅርቡ ከሚፈርሱት ቤቶች ውስጥ የመኖሪያ ቤትና የንግድ ቤቶችን የገዙትን ለመጉዳት ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሚያስመስለውም ጠቁመዋል፡፡
ነዋሪዎቹ እንደተነገራቸው ከሆነ፣ አስተዳደሩ ሁለት አማራጮችን አስቀምጦላቸዋል፡፡ የመጀመሪያው 20 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ በመፈጸም የጋራ መኖሪያ ቤት ማግኘት ሲሆን፣ ሁለተኛው አማራጭ የቀበሌ ወይም የኪራይ ቤቶች ተዘጋጅተውላቸው ወደዚያ መግባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አስተዳደሩ አስቀምጦላችኋል የተባሉትን አማራጭ ነዋሪዎቹ ተቃውመዋል፡፡ ምክንያታቸውም መንግሥት አቅማቸውን በማወቅ 20 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ፈጽመው የኮንዶሚኒየም ቤት ባለቤት ለመሆን አምስት ዓመታትን መጠበቅ ግድ እንደሚላቸው ነግሯቸው፣ ተመዝግበው እየቆጠቡና እየጠበቁ መሆናቸውን ነው፡፡ ይኼ ሆኖ ሳለ በድንገት 20 በመቶ ክፍያ እንዲፈጽሙ መጠየቅ ተገቢ አለመሆኑን አውስተዋል፡፡
ደርግ እንኳን ‹‹ሠፈራ›› በማለት ነዋሪዎችን ከቀያቸው ሲያስነሳ ባለአንድ ፎቅ ሕንፃ ገንብቶ በማስረከብ እንደነበር የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ ‹‹ምን ያመጣሉ›› በማለት ከአራት ወር በኋላ በጥር ወር ውስጥ ለዘመናት የኖሩበት ቤት እንደሚፈርስ ማሳወቅ ተገቢ ባለመሆኑ፣ መንግሥትም ሆነ የሚመለከተው አካል ለነዋሪዎች ክብር በመስጠት ነገሩን እንዲያጤነው ጠይቀዋል፡፡
የነዋሪዎቹን ቅሬታ በመግለጽ ማብራሪያ እንዲሰጡን ያነጋገርናቸው በአራዳ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ ሙሉጌታ፣ ‹‹አስተዳደሩ ወይም መንግሥት ማንንም መጉዳትና መበደል አይፈልጉም፡፡ የደጃች ውቤ ሠፈር ነዋሪዎች ወደ ሌላ አካባቢ እንደሚዛወሩ የነገርናቸው ተማሪዎችን ታሳቢ ባደረገ መንገድ ዕቅዳችንን ነው፤›› ብለዋል፡፡
ነዋሪዎቹ በዋናነት እንዲነሱ የተነገራቸው መንግሥት እያስገነባው ላለው የቀላል ባቡር ፕሮጀክት ከሚያስፈልጉት አራት ተርሚናሎች መካከል አንዱ ፒያሳ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት በቀኝ በኩል እስከ ደጃች ውቤ ሠፈር ስምንት ሔክታር ቦታ ላይ መሆኑን አቶ ግርማ ገልጸዋል፡፡ ጫፍ ላይ ላሉ ነዋሪዎች ቀደም ብሎ የተነገራቸውና ያወቁ ቢሆንም፣ ቀሪዎቹን ማወያየትና ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ መስከረም 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ማወያየታቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ መንግሥት ድርጊቱን እየፈጸመ ያለው ቅርስን ካለመፈለግና ነዋሪዎችን ከማፈናቀል አኳያ መታየት እንደሌለበት አስገንዝበዋል፡፡
ቅርስም ሆነ ሌላ ነገር ከባቡር ተርሚናሉ ጋር የሚገናኝ ከሆነ መፍረሱ የማይቀር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ እንዲፈርስ ውሳኔ የተላፈበት ቦታ 11.6 ሔክታር መሆኑንና ለተርሚናልና ለኃይል መሙያ ስምንት ሔክታር ተወስዶ ቀሪው 3.6 ሔክታር ለመልሶ ማልማት እንደሚውል አቶ ግርማ ገልጸዋል፡፡ ከባቡር ተርሚናል የሚተርፈው 3.6 ሔክታር ቦታ የግል ይዞታ ከሆነና በፕላኑ መሠረት ለመኖሪያ ቤት ወይም ለድርጅት የሚጋብዝ ከሆነ፣ ባለይዞታዎቹ እንዲያለሙት ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው አቶ ግርማ ጠቁመዋል፡፡
‹‹ማንም ነዋሪ እንዲንገላታ አንፈልግም፡፡ በፌዴራል አዋጅ ቁጥር 455/97 መሠረት ለልማት ለሚነሱ ነዋሪዎች ሁለት አማራጮችን እናቀርብላቸዋለን፤›› ያሉት አቶ ግርማ፣ አንደኛው በቀበሌ ወይም በኪራይ ቤት የሚኖሩ ከሆነ ከስቱዲዮ እስከ ሁለት መኝታ ቤት የጋራ መኖሪያ ቤት እንዲያገኙና 20 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ እንዲፈጽሙ ማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ በሌላ ቦታ የቀበሌ ወይም የኪራይ ቤት እንዲያገኙ ማድረግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ነዋሪዎቹ የኮንዶሚኒየሙን ቅድሚያ ክፍያ መንግሥት እንዲከፍልላቸው መጠየቃቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ ጥያቄያቸው አግባብነት የሌለውና አሁን የሚኖሩት በትንሽ ክፍያ የነፃ ያህል መሆኑን፣ ቦታውና ቤቱም የመንግሥት በመሆኑ አቅም ከሌላቸው በመመርያው መሠረት በቀበሌ ቤት እንዲኖሩ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ ወደፊት በጋራ ሕንፃ ላይ መኖራቸው ስለማይቀር ያለዕጣ የማግኘት ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ መክረዋል፡፡
የግል ይዞታ ያላቸው ነዋሪዎችን ለመለየትና ለማወቅ ትክክለኛው መረጃ ገና በመሰባሰብ ላይ ቢሆንም ከ105 በላይ እንደሚሆኑ የገለጹት ኃላፊው፣ እነሱም በአዋጅና በመመርያ ቁጥር 3/2002 መሠረት ሁለት አማራጮች እንደተዘጋጁላቸው ተናግረዋል፡፡ አንደኛ አማራጭ በመንግሥት መሬት ላይ የሠሩት ቤት ካሳ ተከፍሏቸው ኮንዶሚኒየም ቤት በቅድሚያ እንዲያገኙ ማድረግ ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ ካሳ ተከፍሏቸው በመሀል ከተማ ቦታ እንደሚሰጣቸው ወይም በማስፋፊያ አካባቢ እንዲመርጡ ማድረግ መሆኑን አቶ ግርማ አብራርተዋል፡፡ ነዋሪዎቹ በዚህ ዓመት መጨረሻ ሊነሱ እንደሚችሉ የጠቆሙት ኃላፊው፣ ምናልባት ነገሮች ከተመቻቹ በጥር ወር ሊያሸጋግሯቸው እንደሚችሉ በስብሰባ ላይ እንደነገሯቸው አስረድተዋል፡፡
ከቅርስ አጠባበቅ ጋር በተያያዘ ለተነሳላቸው ጥያቄ አቶ ግርማ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹አንዳንዶቹን ከቅርስ አኳያ የምናያቸው አሉ፡፡ በመመርያው መሠረት የሚሆነው ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ያህል ዶሮ ማነቂያ አካባቢ እየተለዩ ነው፡፡ የባቡር ተርሚናሉና ኃይል መሙያው የሚሠራበት ከሆነ ግን ለድርድር አይቀርብም፡፡ ይፈርሳል፡፡ መታሰብ ያለበት ነገር ቢኖር ጊዜያዊውን ችግር ብቻ ሳይሆን ኅብረተሰቡ ወደተሻለ ሕይወት ማለፍ ስለሚኖርበት ነው፤›› ሲሉ አቶ ግርማ ገልጸዋል፡፡
በደጃች ውቤ (ውቤ በረሃ) ሠፈር ከሚፈርሱት ቤቶች መካከል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ ይኖሩበት የነበረውና ከራስ መኮንን ድልድይ በስተቀኝ በኩል የሚገኘው ዓድዋ ሆስቴል፣ የታዋቂው አኮርዲዮን ተጨዋች አቶ ፍሬው ኃይሉ ቤት፣ የኢትዮጵያ ባለውለታ የነበሩትና በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ከቱርክ መሣሪያ በመግዛት ለኢትዮጵያ ያመጡ የነበሩት አርመናዊው ሚስተር ቴራዚያን ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት፣ በቀይ ሽብር ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው አፈ ንጉሥ ተክሌ ቤት፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የነበሩት የጄነራል መልኬ ቤት፣ በደርግ ዘመን የዘመቻ መምርያ ኃላፊ የነበሩት ከበደ ስመኝ ቤት፣ በደርግ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የነበሩት አቶ ቢልልኝ ማንደፍሮ ቤት፣ የመጀመሪያው ስፖርት ቤት መሥራች ሙሉ ስፖርት ቤት፣ የመጀመሪያው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በረኛ አቶ ታደሰ ጌጤ ቤት፣ የቡድኑ መሥራችና ተጨዋች የነበሩት አቶ አየለ አትናሸ ቤት ጥቂቶቹ ሲሆኑ፣ በአጠቃላይ ከ775 በላይ ቤቶች እንደሚፈርሱ ታውቋል፡፡

Tuesday, September 24, 2013

መስቀል አደባባይ! የኢትዮጵያውያን ታህሪር?

መስቀል አደባባይ! የኢትዮጵያውያን ታህሪር?
------------------------------------------------------------------------------

ኢህአዴግ ድሮ ጀምሮ ከሚጠላው የአደባባይ ሰልፍ ራሱን አደባባዩን ወደመፍራት አፈግፍጓል፡፡ በተለይ መስቀል አደባባይ የኢትዮጵያው ታህሪር እንዳትሆን አብዛቶ ፈርቷል፡፡ ላለፉት ስምንት አመታት የሚከለከለው ራሱ ሰላማዊ ሰልፍ ነበር፡፡ ሰማያዊና አንድነት ከግንቦት ጀምሮ ያደረጓቸው ሰላማዊ ሰልፎች ላይ ኢህአዴግ ሲከላከል የሰነበተው ቀዳሚ ጉዳይ ህዝብ በብዛት እንዳይሳተፍ ነው፡፡ ለዚህም ቅስቀሳ የሚያደርጉት ወጣቶች እስካሁንም ድረስ እያሰረ ቀጥሏል፡፡ መስሪያ ቤቶችም በካድዎች ትዕዛዝ ሰላማዊ ሰልፍ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያንን ከስራቸው እያበረሩ ነው፡፡

ኢህአዴግን ያስፈራው ሌላው ጉዳይ ግን ሰላማዊ ሰልፍ የሚካሄድበት አደባባይ ነው፡፡ ቅስቀሳ የሚያደርጉትን እያሰረም ቢሆን ሰላማዊ ሰልፎችን በጠባብ ጎዳናዎች ላይ ብቻ በመወሰን ጭንቀቱን ለማቅለል ሞክሯል፡፡ 97ት ላይ ክፉኛ የደነገጠበት መስቀል አደባባይ ለድጋፍ ሰልፍ እንጅ ለሰላማዊ ሰልፍ ክልክል ሆኗል፡፡ ሰማያዊ ወደ መስቀል አደባባይ ሲያመራ ሰልፉን ረግረጋማውና ፖሊስ ህዝብ እንዳይሳተፍ ለማጎር ምቹ የሆነው ጃን ሜዳ ላይ እንዲያደርግ ‹‹አማራጭ›› አቅርቦ ነበር፡፡ ሰማያዊ መስቀል አደባባይን ኢህአዴግ ባዘጋጀለት ጃን ሜዳ ከመቀየር ይልቅ መስቀል አደባባይ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ የሚደረግበት ቀን ሩቅ እንዳልሆነ በማሰብ በክብር ወደ ቢሮው ተመልሷል፡፡

ሰላማዊ ሰልፍ የሚያስበረግገው ‹‹አብዮታዊ›› ፓርቲ አሁንም በርካታ ህዝብ እንዳይሳተፍ ቅስቀሳ የሚያደርጉትን የአንድነትን ወጣቶች ማሰሩን ቀጥሏል፡፡ ኢህአዴግ እንደፈለገ የሚጨፍርበትን አደባባይ ‹‹ግንባታ እየተካሄደበት ነው›› በሚል ለሰልፍ እንደማይፈቀድ መንቦጅቦጁን በግልጽ አሳይቷል፡፡ መቼም በሚቀጥለው አርብ የመስቀል በዓልን ‹‹ግንባታ እየተካሄደ ስለሆነ›› ልክ እንደ ጥምቀት ጃን ሜዳ አድርጉት አይልም፡፡

በእርግጥ ጉዳዩ እራሱን ነው አንድ እርምጃ እያፈገፈገበት ወዳለው ገደል የሚገፋው፡፡ ስለሆነው ለኢህአዴግ የመስቀል አደባባዩ ግንባታ የሚደናቀፈው ህዝብ ስለ ነጻነት ጮኸቱን ሲያሰማ ነው፡፡ ኢህአዴግ አምባገነንነቱን ከመቼውም በላይ እየገነባ ነው፡፡ ይህን አብዮታዊ ግንባታ ደግሞ የሚደረምሰው የወጣቶች ድምጽ መሆኑን ከግብጽ ተምሯል፡፡ የኢትዮጵያውያን ታህሪር ደግሞ መስቀል አደባባይ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ልክ እንደ ግብጾቹ 97 ላይ ሞክረው ተጨናግፎባቸዋል፡፡ ያኔ ኢህአዴግ ሰልፍን በጊዜያዊ አዋጅ፣ በኋላም በቋሚ አዋጅ ለስምንት አመት በኋላ ለማፈን ችሎ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ስለ ህግና አዋጅ እያወራ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ፈቅዶም ቢሆን ባልተጻፈ ህግ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው፡፡ አደባባዮችን ለመልቀቅ ማንገራገሩን ቀጥሏል፡፡ ልክ እንደሙባረክ!

መስቀል አደባባይ ሆይ! መቼ ይሆን ኢህአዴግ እንደሚፈራው የኢትዮጵያውያን ታህሪር የምትሆኝው?