Monday, March 30, 2015

እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ 28 ቀን ተቀጠረባቸው

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት የሆኑት ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ ፍቅረማሪያም አስማማውና እየሩሳሌም ተስፋው ትናንት መጋቢት 21 አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው 28 ቀን ተቀጠረባቸው፡፡ ፖሊስ እነ ብርሃኑ ተክለያሬድን ‹‹ለግንቦት 7 አባላትን መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክና ቡድኑን ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሲሄዱ ተይዘዋል›› ብሏል፡፡
ጠበቃው እነ ብርሃኑ ተ/ክለያሬድ ለግንቦት ሰባት ሲመለምሉም ሆነ አባል ሲሆኑ የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃ እንደሌለ በመግለጽ የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ፖሊስ ‹‹ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምመረምራቸው ጉዳዮች አሉ፡፡ ሌሎች የምንይዛቸው ግብረ አበሮችም አሉ፡፡ መረጃ ያጠፉብናል፡፡›› በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቆ 28 ቀን ተፈቅዶለታል፡፡ ሚያዚያ 19 ፍርድ ቤትይቀርባሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
ፖሊስ ሌሎች ሰዎች ይዘውት የተነሱትን መሳሪያ በማሳየትም እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ግንቦት ሰባትን ሊቀላቀሉ እንደነበር ለማሳየት በመረጃነት አቅርቧል፡፡ ጠበቃው በበኩላቸው ‹‹የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ምርመራ ለማድረግና መረጃዎችን ለማሰባሰብ ተጠርጣዎቹን ማሰር ተገቢ አልነበረም፡፡ ሌሎች ሰዎች የያዙትን መረጃ እነሱን ለመክሰስ መጠቀም ተገቢ አይደለም፡፡›› ሲሉ ተቃውመዋል፡፡
በሌላ በኩል ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ የታሰረበት ቤት መብራት ስለማይጠፋ አይኑ ላይ ለከፍተኛ ችግር እንዳደረሰበት ቅሬታ አቅርቧል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ለ15 ደቂቃ ፀኃይ እንዲሞቁ ከሚፈቀድላቸው ውጭ ወደ ከታሰሩበት ቤት ውጭ መውጣት እንደማይፈቀድላቸውና ቤተሰቦቻቸውም እንዲጠይቋቸው እየተደረገ አለመሆኑን በቅሬታ አቅርበዋል፡፡

በቀልድ የታጀበው ምስክሮችን የመስማት ውሎ

በቀልድ የታጀበው ምስክሮችን የመስማት ውሎ -የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ
በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት የሚቆየው የማስረጃ መስማት ውሎ ዛሬ ምስክሮችን በማስማት ተጀምሯል፡፡ በዚህም መሰረት አቃቤ ህግ ጉዳዬን ያስረዱልኛል ያላቸውን 17 ምስክሮች ያስመዘገበ ሲሆን 15ቱ በፍርድ ቤቱ ተገኝተው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ አቃቤ ህግ ችሎቱ በዝግ ችሎት አንዲሆን የጠየቀ ሲሆን ምስክሮቼ እና የቤተሰቦቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ ችሎቱ በዝግ ሊሆን ይገባል የሚለውን አቤቱታውን ጠበቆች በከፍተኛ ደረጃ ተቃውመውታል፡፡ ምስክሮቹ የጭብጥ ምስክሮች ሳይሆኑ ፍተሻን የታዘቡ የደረጃ ምስክሮች በመሆናቸው እና ስማቸውም በግልጽ ተከሳሾች ጋር ስለደረሰ ምንም አይነት የደህንነተ ስጋት የለባቸውም ከሚለው የጠበቆች ክርክር በኋላ ፍርድ ቤቱ በጉዳዬ ላይ ተወያይቶ ለመወሰን ረፍት ወስዷል፡፡ በዚህም መሰረት የአቃቤህግን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ ችሎቱ በግልጽ ሆኖ መስክሮች ምስክርነታቸውን እነዲያሰሙ ታዟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አቃቤ ህግ ያቀረባቸው ምስክሮች አነማን ላይ አንደሚመሰክሩ እና ምን አንደሚመሰክሩ በተጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱም በጠበቆቹ ስለተነሱት ነጥቦች የአቃቤ ህግን ምላሽ ጠይቋል፡፡ አቃቤ ህግም በዛሬው ዕለት የቀረቡት ምስክሮች በ2ኛ፣ በ3ኛ፣ በ5ኛ፣ በ6ኛ፣ በ7ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች ( በስድስቱ የዞን9 ጦማርያን ላይ እና በጋዜጠኛ አስማማው ላይ ) ላይ እንደሚመሰክሩ ገልጾ የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቡድን በብርበራ ያገኛቸው ማስረጃዎች ከተከሳሾች የተገኙ ስለመሆናቸው ያስረዱልኛል ሲል ምላሽ ሰጥቷል፡፡
በምላሹም መሰረት የአቃቤ ህግ ምስክሮች ምስክርነታቸው ሰጥተዋል፡፡ ምስክርነታቸው ሲሰጡ በነበረበት ወቅት የተከሳሾችን ስም አለማወቅ አንዲሁም የተከሳሾችን መልክ አለመለየት የመሳሰሉት ጉዳዬች የተስተዋሉ ሲሆን ምስክርነታቸውን የሰጡት ሰዎች ስም ዝርዝር እና የምስክርነታቸው ጭብጥ በአጭሩ አንደሚከተለው ነው ፡፡
1.ሙሉጌታ መዝገቡ ለማ - ናዝሬት ነዋሪ ነኝ መአከላዊ ምርመራ ለግል ጉዳይ ሄጄ ፓሊስ ታዛቢ ምስክር አንድሆን ጠይቆኝ በዚያ መሰረት ምስክር ሆኜ ተገኝቻለሁ፡፡ ከአቤል ከኮምፒውተሩ ላይ ጽሁፍ ሲወጣ እና ሲፈርም አይቼ እኔም ፈርሜያለሁ ፡፡ የጽሁፉን ይዘት አላነበብኩም አንዳንድ ቦታ አፍሪካ ሪቪው ኬንያ የሚል ቃል አይቻለሁ የሚል ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡
2.በለጡ አበበ ዮሴፍ ይባላሉ፡፡ እድሜያቸው 32 ሲሆን ከፍተኛው ፍርድ ቤት የካ ምድብ ሰራተኛ ናቸው፡፡ አዲስ አበባ ነዋሪ ሲሆኑ በማን ላይ ለመመስከር እንደመጡ ሲጠየቁ በስም እንደማያስታውሱት ገልጸው በአካል ግን ለይተው አሳይተዋል፡፡ መስካሪዋ በ6ኛ ተከሳሽ ዘላለም ክብረት ላይ የሚመሰክሩ ሲሆን በተለየ ስም ሲጠሩት ተስተውለዋል
"የሽብርተኝነት ጉዳይ የሚያመለክት ይመስለኛል፡፡ ወደ 70 ገጽ አማርኛና 10 ገጽ እንግሊዝኛ ጽሁፍ ተገኝቷል፡፡ ያየሁትን አይቼ ፈርሜያለሁ፡፡" ካሉ በኋላ ተከሳሹስ ፈርሟል ተብለው ሲጠየቁ መጀመሪያ አላስታውስም ቢሉም እንደገና ሲጠየቁ ግን አዎ ፈርሟል ብለዋል፡፡
3.እታፈራሁ ጌታቸው ወልዴ የሚባሉ ሲሆን እድሜያቸው 36 ነው፡፡ በመንግስት ት/ቤት በአስተዳደር ሰራተኛነት የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ ማን ላይ እንደሚመሰክሩ ሲጠየቁ ፍቃዱ እና…..(ስሙ ጠፍቶባቸው ቆይተው) እ…አጥናፉ ብለዋል፡፡ በአካል ደግሞ በፍቃዱን አሳዩ ሲባሉ አጥናፍን አሳይተዋል፡፡ የምስክርነት ቃላቸውም ማእከላዊ ምርመራ ለግል ጉዳይ ሄደው ጽሁፎች ሲታተሙ ማየታቸውንና በፍቃዱ በፍቃደኛነት ሲፈርም ማየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ስለጽሁፎቹ ሲጠየቁ "የአማርኛ ጽሑፎች ናቸው፡፡ 60 ገጽ የሚሆን ‹ወያኔ ይውደም› ምናምን የሚል ጽሑፍ አይቻለሁ፡፡ እንግሊዝኛም አለው 10 ገጽ ይሆናል፡፡ በምስል ከውጭ ሰው ጋር ሆነው የሚነጋገሩትም አይቻለሁ፡፡ ይዘቱ ግን ግር ይለኛል፡፡" ብለዋል፡፡ አጥናፍን አስመልክቶ ደግሞ ‹‹የእሱንም በዚያው መልኩ ነው ያየነው፡፡ ዕለቱም ግንቦት 16/2006 ነው፡፡ ኮምፒውተሩ ላይ የነበሩትን ጽሁፎች እዚያ ለነበሩት ሲያሳይ ነበር፡፡ ጽሑፎችን አይቻቸዋለሁ….‹የጨለማው ቀን….የጨለማው ንጉስ› የሚል አይቻለሁ፡፡ ‹ኢትዮጵያ አንድ ናት› የሚልም አይቻለሁ፡፡ ወደ 30 ገጽ ይሆናል፡፡ ሁሉም ፕሪንት ተደርጎ ሁላችንም ፈርመንበታል፡፡››ብለዋል
ሶስቱ ምስክሮች ከተሰሙ በኋላ ጠበቆች በሂደቱ ላይ አስተያየት አለን በማለት፣ ዶክመንቶቹ ፕብሊክ ዶክመንት ናቸው በአደባባይ የተጻፉ ጽሁፎቻቸው እና በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ስለሆኑ ዶክመንቶቹን ክደን አልተከራከርንም የእኛ ክርክር ዶክመንቶቹ ለወንጀል ስራ የሚበቁ አይደሉም ነውና በዚህ ጭብጥ ዙሪያ ምስክር መስማቱ ያብቃልን የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡አቃቤ ህግ በበኩሉ ሁሉም ምስክሮች አንዲሰሙልኝ እፈልጋለሁ በማለቱ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ ያስረዱልኛል ካለ ይቀጥል በማለቱ ምስክሮቹ ቀጥለዋል፡፡ ጠበቆች መስቀለኛ ጥያቄ ሳይጠይቁ ተከታዬቹ ምስክሮች መሰማታቸው ቀጥሏል፡፡
4.አራተኛው ምስክር አፈወርቅ ካሳ ይባላሉ፡፡ የግል ሰራተኛ ሲሆኑ እድሜያቸው 46 ነው፡፡‹‹ቀኑ ሚያዝያ 18/2006 ነው፡፡ የተከሳሹ አስማማው ቤት ጠዋት 3፡00 አካባቢ ሲፈተሸ ታዛቢ ነበርኩ፡፡ ጋዜጦች፣ መጽሔቶች፣ ፓስፖርት…ብዙ ወረቀቶች ላይ ‹‹አዎ የእኔ ናቸው›› እያለ ሲፈርም አይቻለሁ፡፡ እኔም ፈርሜያለሁ፡፡ ቤተሰቦቹም ቤት ውስጥ ነበሩ፡፡ አብዛኛው ያየሁት የግል መጽሄቶችን ነው፡፡ ማህተምም አይቻለሁ፡፡ ደሞ ቢሮው ሄደን ላፕቶፕ፣ ፍላሽ፣ ሲዲ፣ መጽሔቶች አይቻለሁ፡፡ ፖሊስ የሚፈልገውን እየለየ ፈርመናል፡፡ ወደቢሮው የሄድነው በመኪና ነበር፡፡ ከዛ ደግሞ አድራሻችንን ይዘው ስለነበር ሰኔ 4….አይ 14/2006 ነው መሰለኝ ከማዕከላዊ ተጠርተን ላፕቶፕ ላይ የነበረውን ስዕሎችና የእንግሊዝኛ ንግግሮች ሲወጡ አይቻለሁ፡፡ የእኔ ነው ብሎ ሲፈርም እኛ ታዛቢዎችም ፈርመናል፡፡›› ብለው ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
5.አምስተኛ ምስክር አጌና አንከና ይባላሉ፡፡ እድሜያቸው 48 ሲሆን ነዋሪነታቸው አ.አ ነው፡፡ የሚመሰክሩት ደግሞ በ3ኛ ተከሳሽ ናትናኤል ላይ ነው፡፡ የምስክርነት ቃላቸው፣ ‹‹ሰኔ 17/2006 ለግል ጉዳይ ማዕከላዊ ነበርኩ፡፡ ከቀኑ 8፡00 ታዛቢ ሁነኝ ብሎ ፖሊስ ጠይቆኝ ታዝቤያለሁ፡፡ ላፕቶፑ ላይ አማርኛ ጽሑፎች አይቻለሁ፡፡ ጽሑፎቹ የተከሳሹ ስለመሆናቸው አምኖ ሲፈርምባቸው ታዛቢዎችም ፈርመናል፡፡ ይዘቱን ግን አላነበብኩትም፤ አልተረዳሁትም፡፡ የገጹን ብዛትም አላስታውስም፡፡›› የሚል የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
6.ስድስተኛ ምስክር ገብረጨርቆስ ገብረመስቀል ይባላሉ፡፡ የ50 ዓመት የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ ምስክሩ በአስማማው ላይ ለመመስከር እንደመጡ ቢናገሩም በአካል ግን ለይተው አላወቁትም፡፡ እንዲያውም አስማማውን አሳዩ ሲባሉ አቤልን አሳይተዋል፡፡
ከፍርድ ቤቱ ውሎ በኋላ አስተያየታቸው የሰጡት የተከሳሾች ጠበቆች አቃቤ ሀግ ያቀረባቸው ምስክሮች ወረቀት ሲፈረም አየን ከማለት ውጪ ምንም አይነት ለሂደቱ ቁም ነገር ያለው ምስክርነት የሚሰጡ አይደሉም ፡፡ ተከሳሾች ተገኘባቸው የተባለው ጽሁፍ የአደባባይ ዶክመንት ከመሆኑም በላይ አልተገኘብንም ብለን ክደን አልተከራከርንም በይዘቱ ላይ ክርክር ስላልተደረገ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብም ብዙ አልጨነቅንም ብለዋል፡፡አቃቤ ሀግ የወንጀሉን የመጀመሪያ ደረጃ ጭብጥ የሚያሳዬ ምስክሮችን ያቅርብ አይቅርብ የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ የማስረጃ ማሰማት ሂደቱ ነገ ይቀጥላል፡፡
በተቃራኒው ምሳቸውን ችሎት ውስጥ የተመገቡት ሁሉም እስረኞች በጠንካራ መንፈስ ሆነው ሲጨዋወቱ እና ሲነጋገሩ ተስተውለዋል፡፡ የችሎቱ ተሳታፌዎች በምስክሮች መደናበር እየሳቁ ነበረ ሲሆን የዞን9 ወዳጆች አጋሮች ቤተሰብና ጋዜጠኞች ተገኝተዋል፡፡
የዞን 9 ማስታወሻ
የዛሬውን አስቂኝ የፍርድ ቤት ውሎ ባልተካደ ነገር ላይ ወርቃማውን የተከሳሾች ሰአትም ሆነ የፍርድ ቤቱን የስራ ሰአት ማባከኑ የሚገርም ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ችሎቱ በግልጽ አንዲካሄድ መፍቀዱን በበጉ መልኩ ተመልክተነዋል፡፡ አቃቤ ህግ ለምስክሮቹ ደህንነት ሳይሆን የራሱን መዋረድ ለመቀነስ ሲል ችሎቱን በዝግ ለማድረግ መሞከሩ ተከትሎ የመጣውም የምስክሮች መወዛገብ ግልጽ የሚያደርገው ነው ፡፡ የዞን9 ጦማርያን አና ጋዜጠኞች ላይ የቀረበባቸው ማስረጃ በተለያየ ቦታ የጻፏቸው የራሳቸው እና የሎሎች የአደባባይ ምሁራን ጽሁፎች በመሆናቸው ጽሁፉ የእኛ መሆኑ ምስክር አያሻውም ፡፡ በተደጋጋሚ እንዳልነው ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው የታሰሩት ወጣቶች ክስ የጸፉት ጽሁፍ ይዘት ላይ ነው፡፡ የታሰሩ ወዳጆቻችንን ለመፍታት አሁንም አልረፈደም ፡፡
በዚህ አጋጣሚ ፍርድ ቤት ተገኝተው አጋርነታቸውን ለሚያሳዬ የዞን9 ወዳጆች ከፍተኛ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ህገ-መንግስታዊ መብት ይከበር ፡፡
ዞን9

የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ለ10ኛ ጊዜ ተመለሰ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክትን አላስተላልፍም ብሎ መመለሱን ዛሬ መጋቢት 21/2007 ዓ.ም ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ፋና የሰማያዊ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አላስተላልፍም›› ብሎ የመለሰው፤-
• ህወሓት/ኢህአዴግ የሚባል ገዥ ፓርቲ በኢፌድሪ የመንግስት አወቃቀር ውስጥ የሌለ በመሆኑ፣
• በጎሳ ላይ የተመሰረተ የፌደራል ስርዓት የሚለው በትክክል ስላልተገለጸ፣
• ብሔር ብሔረሰቦች መሃል ተፈጠሩ ተብለው በዝርዝር የቀረቡት ጉዳዮች አንዱን ብሄር ከሌላው ብሔር ጋር እንዲጋጭ የሚያነሳሱና ግጭትን የሚያራግቡ ናቸው በሚል ነው፡፡
ሚዲያዎች የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክትን ‹‹አናስተላልፍም›› ብለው ሲመልሱ የፋናው ለ10ኛ ጊዜ ነው፡፡

The Curious Case of Zone9 Prisoners

(By Abiye Teklemariam) 
Inside the compound that hosted the old timber and mud Arada courthouse, there was the traditional melee associated with high-profile political trials – rain shelters flowing with friends and families of the defendants wearing woebegone looks; angry radical anti-status quo activists rubbing shoulders with slipshod government informants; a coterie of bored western diplomats who would rather be somewhere else; journalists too afraid to take pictures. Outside, as they often do in these circumstances, people strolled casually about their business, either ignorant of or unstirred by the politico-legal drama taking place. The courthouse itself has been witness to a significant number of these events in the last twenty two years. It is where Ethiopia’s authoritarian government that is obsessed with procedural rituals and legal theatrics customarily begins its often drawn out prosecutorial playacting against political prisoners. Indeed, the dilapidated state of the building coupled with the striking contrast between its declared and real purpose evokes a mental drawing of Chris Wiman’s “the ramshackle house on high exposed hill which sings with the wind that is steadily destroying it.”
On May 7, 2014, the victims of yet another performance were six members of a blogging collective called Zone9 and three journalists. Hand-cuffed and escorted by gun-wielding guards, the prisoners arrived at the courthouse. Many of them were well-known by those who follow and engage in Ethiopian politics for their courageous dissent and skillful use of social media networks for activism and polemics. The most popular among them, Zelalem Kibret, a young academic, often laced his political commentaries with utterly nacreous wit, eliciting grudging affection even among some whose political views had been at the end of his smackdowns.
Against this background, it is tempting to see the episode as another routine attack on dissent. But there is a difference that sets it apart from sui generis Ethiopian political trials. The Ethiopian government is the master of the mechanics of power-law repression. Its regular targets are either base activists, who can be arrested and tortured, without a squeak from international partners, or oppositionists of political influence – leaders and opinion makers in organized groups, journalists with polemics of electricity. The unceasing glare of publicity and noise of disapproval that follows each attack on the latter is worth the price of their silence.
Zone 9 bloggers do not belong to these categories. They have been avowedly, even belligerently, independent of any of the existing organized opponents of the regime. It is also hard to detect an internal strategic or ideological unity and coherence or any attempt to reach there. Collectively, they have campaigned and published irregularly. Neither could one find, beyond a broad support to democracy and equality, a clear thematic thread that connected their individual concerns. Most importantly, their arena of operation, online participatory media, remains a remote enclave in Ethiopian politics that should be carefully monitored but not yet feared. So what explains the deviation from the traditional approach?
The answer probably lies in understanding what was anticipated but did not happen in the immediate aftermath of the death of Meles Zenawi, the country’s longstanding leader.
.......
(The full text of this article written in recognition of the first anniversary of the imprisonment of Zone9 bloggers and journalists is available on 7-Kilo Magazine)

አይ ወያኔ ድንቄም ለወጥ አምጪ

 ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግም ይባላል የሀገሬ ሰው ሲተርት መቼም ነገርን ነገር አይደል የሚያነሳው ለዚህ ገፅ አንባቢዎች በሙሉ የከበረ ሰላምታዬን አቀርባለሁ ከላይ ያነሳሁትን አባባል እንዳነሳ ያደረገኝ አንድ ሌላ ጥሩ የማውቀው አንድ የራሴ ታሪክ ላጫውታቹና ወደዋናው ሀሳቤ ልግባ ፡፡

የማውቃትን የቅርብ የአክስቴን ልጅ የቤት ስራዋን ለሰው ታሰራና እራሷ እንደሰራች አድርጋ ለእናቷ ታሳይ ነበር እናቷም በልጇ ጉብዝና እየተመካች ለጎረቤትና ለዘመድ በኩራት ትናገር ነበር እየቆየች ግን እውነት መውጣት ትጀምርና ትንሿ የአክስቴ ልጅ ጉብዝናው የእሷ አለመሆኑ እናቷን ያጠራጥራት ጀመር እነቷም ይህን ለማረጋገጥ የራሷን ዘዴ መጠቀም ትጀምርና ልጄ የኔ ፍቅር አሁን የምገዛልሽን ስጦታ የምገዛው አሁን እኔ የምሰጥሽን የቤት ስራ አጠገቤ ቁጭ ብለሽ ስትሰሪ ብቻ ነው ትላታለች ልጅም ብልጣብልጥ ነበረችና ማም እስከዛሬ የገዛሽልኝ ስጦታ ከቤት ስራ በ%Eላ ነበር የአሁኑ ግን ቅድሚያ ቢሆንስ በማለት እናቷን ፈትናታለች እናም አክስቴ ልጇን አጥፊነት ወይም እራሷን አታላይ መሆን ሳይሆን የልጇን ብልጠት እንዳችበት የማስታውሰው ታሪክ ነው፡፡

መቼም የእናትና የልጅ ታሪክ ሆነ እንጂ በእኛ ወይም በእኛ ዙሪያ እንዲህ ያለ ታሪክ ዙሪያችን ቢኖር እንመለከተው ይሆን?

ትላንት ለውጥ ፈላጊ ሆነው በሀገራችን ላይ የራሳቸው በሆነ መሬት ላይ የእናንተ ዲሞክራሲና መብት ተብለው ለውጥ ፍለጋ መንግስት አለን ብለው የብሶታቸውን ድምፅ ሊገልፁ ባሉ ወጣቶች ላይ የራሳችን መንግስት የምንለው ወንድሞቻችን ላይ የማስደንገጥ ወይም ሰልፍ የማባረር ሙከራ ሳይሆን ሆን ተብሎ ግንባር ግንባራቸው ላይ እንደጠላት በየመንገዱ የተደፉት ወንድሞቻችን እንዲሁም የቦንብ መጥረጊያ የሆኑ ወንድና ሴት ወገኖቻችን ታሪክ ለማዳፈን ወያኔ ዛሬ የሚያደርገው ማለባበስ ምን ይባል ይሆን? የኢትዮጵያ ህዝብ በዘርና በሀይማኖት ለያይቶ የራሱን ዕርዮት አለም ካልተቀበለ በዚህች ሀገር መብት የሌለው ስንቱ ይሆን ወገኔ ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ ሁሉም የራሱ የሆነ ነገር ይዞ የሚመጣው ነገር ይኖራል ወያኔ ግን ዙፋኑ ላይ እንደተቀመጠ ከነበረው ስርዓት ብዙም የተለየ ነገር አልነበረውም የአንዱ ጎሳ የበላይነት ነጣጥሎ የመግዛት ስርዓት ሲጠቀም ቆይቶ ዛሬ እንደ ህፃን ልጅ የኢትዮጵያን ህዝብ ለመደለል የራሱ ርዕት አለም አቀንቃኝ የሆኑትን ሰዎች ይበልጥ ሀብታም በማድረግ ኢኮኖሚ አሳደኩ እያለ በአዲስ አበባ ቋንቋ እንደሚባለው ፉገራ ወይም ሆድን በጎመን እንደመደለል ያለ ጨዋታ ብዙ አያዋጣም፡፡ ቻይናን በገፍ አስገብቶ የፉገራ ቴክኖሎጂ የሀገርን ህዝብ ያታልለዋል ባይታለልም አማራጭ የለውም፡፡ የቻይና ሸቀጥ ማራገፊያ አንተ የሰጠህው ድምፅ ብልጫ ሳይሆን እኔ የማወጣው መርህ ግብር ይገዛሀል ተብሎ የፓርቲ አባል ካልሆንክ ኢትዮጵያዊነትህ ብቻውን ትርጉም የለውም ተብሎ አፈና እና ብዝበዛ ችሎ ያለው ህዝባችን እንደዛች ትንሽ ለልጅ ያለ ብልጠት ከዚህ ፉገራ ነፃ ያወጣው ይሆን ወይስ ሁሌ ታሪክና እውነትን የሚፈርድ የኢትዮጵያ አምላክ ሁሉን አዲስ አድጎ በብሔር ማንነት ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት የሚኮራበት ኢትዮጵያዊ ስለሆነ ብቻ የሀገሩ መንግስት ዘብ የሚቆምለት ጊዜ ይመጣ ይሆን?

ያለፈ ታሪክ ያለፈ ቢሆንም ዛሬ የሚደረገው ነገር
ካለፈው ካልተማረ ይቅር እንበለው እንዳንል ዛሬም ያኑኑ የአንባገነንነቱንና እኔ ብቻ አዋቂ ነኝ ባይነቱን አገዛዝ እያስከፋው ይታያል እናም በዚህና በዚያ መደለሉ ቀርቶ ለሀገር እድገት የሚሻለውን አዳዲስ ሀሳብ ከአዲስ ሰው ለአዲስ ትውልድ በመቀበል ያረጀና እጅጅ ያለውን የወያኔ አገዛዝ ለመቀየር ወገን እንነሳ፡፡

ክብር ለኢትዮጵያ

ምንትዋብ

ጎህ መፅሔት

የወያኔ ስልጣን ጥማት ለማርካት እጅግ ጭካኔና ግፍ የተሞላበት ስርአት ከብዙዎቹ በጥቂቱ

1.የሀገሪቱን ህዝብ በጎሳ፣ በሐይማኖትና በድንበር እንዲጋጩ ማድረግ
2.የተማረውንም ሆነ ያልተማረውን በጥቅማ ጥቅም ወይም በግዴታ የፓርቲው አባል ማድረግ
-የተማረ ከሆነ ስራ ለማግኘት ወይም የስልጣን እርከን ለማሳደግ ኮንዶሚኒየም ቤቶችን ለፓርቲው አባል ለሆነ ሰው ተሻለ ዕድል በመስጠት ያልተማረውን ደግሞ በጦር ሰራዊት በማሰማራት በሕገ-መንግስቱ መሰረት ከየተኛውም ፓርቲ ነፃ መሆን አለባቸው ነገር ግን በወያኔ አገዛዝ የሀገሪቱን ህልውና ሳይሆን የወያኔን ስልጣን ጠበቃ አድርጓቸዋል ወይም የወያኔ ቃታ ሳቢ አድርጓቸዋል፡፡
3. ጭኩን ሆነ የትምህርት ስርዓት መዘርጋት
4. ፍርድ ቤቶችን መቶ በመቶ ለራሳቸው እንዲቆሙ ማድረግ
5. ፓርላማውን አሻንጉሊት ማድረግ
6. የተለያዩ የመገናኛ ቡዙሀን እንዲያሰራጩ በማድረግ እነዚህን በመሳሰሉ ትልልቅ መንገዶችን በመዘርጋት ወያኔ የስልጣን ጥማቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡
ይሄ ሁሉ ግፍ የመረረው ወጣት ዛሬ ሀገሩ ሰርቶ መኖር ሳይችል ሲቀር በስደት ላይ ይገኛል፡፡ ገሚሱ ደግሞ በጥይት ዶፍ ተበሳስቶ አልፏል፡፡
የወያኔ የጭቆና አገዛዝ መቼ ይሆን የሚያበቃው?
እኛስ መቼ ይሆን የማንሰደደው?

ሊዲያ ወልዴ ዮሐንስ
ጎህ መፅሔት

Sunday, March 29, 2015

‹‹ፖሊስ ለገዥው ፓርቲ መሳሪያ መሆን የለበትም!›› የአዲስ አበባ ሰልፈኞች

የአዲስ አበባው ሰልፈኛ አሁንም ወደ ቤተ መንግስት ለማለፍ ጥረት እያደረገ ነው! 
የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥና የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ በጋራ ‹‹በቤተ መንግስት በኩል ማለፍ አትችሉም!›› እያሉ ነው!
ሰልፈኞቹ የተለያዩ መፈክሮችን ና መዝሙር በማሰማት ላይ ናቸው!
ተከብረሽ የኖሽው በአባቶቻችን ደም፣ 
ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም! 
ያስደፈረሽ ይውደም!

ኢህአዴግ መንገድ ሊመርጥልን አይችልም!
ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ራሱን ነጻ ያውጣ!
የፖለቲካ እስኞች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈቱ፣ ጋዜጠኞች ይፈቱ፣ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ይፈቱ፣ አምባገነንነትን እንታገላለን!




 

ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ቅስቀሳ መልዕክታችን ላይ የቅድሚያ ምርመራ እየተደረገ ነው ሲሉ ከሰሱ

-ኢዴፓ ድርጊቱ ካልቆመ ራሴን ከምርጫ አገላለሁ አለ
በመጪው ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆኑ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ በምርጫ ቅስቀሳ መልዕክታቸው ላይ የቅድሚያ ምርመራ (ሳንሱር) እየተደረገ ነው ሲሉ ከሰሱ፡፡
ኢዴፓ ቅድመ ምርመራው ከተደገመ ራሴን ከምርጫ አገላለሁ ብሏል፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እስከ ግንቦት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚዘልቀው የምርጫ ቅስቀሳና ዘመቻ የጊዜ ሰሌዳ የተለያዩ መልዕክቶቻቸውን በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የሚዲያ ተቋማት ሕገ መንግሥታዊ ከለላውን በመጣስ የቅድመ ምርመራ በማድረግ መልዕክቶቻችንን አናስተላልፍም አሉን በማለት ፓርቲዎቹ ቅሬታ እያቀረቡ ነው፡፡ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 29(3) (ሀ) ላይ የቅድሚያ ምርመራ በማንኛውም መልኩ የተከለከለ እንደሆነ ይደነግጋል፡፡ 
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) መጋቢት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መግለጫ ቅስቀሳዎቹ እንዳይተላለፉ በመደረጉ፣ በምርጫ ተሳትፎው ላይ ትልቅ ተግዳሮት እንደፈጠረበት ገልጿል፡፡ 
በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትና በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) እንዳይተላለፍ የተከለከለው የቅስቀሳ ፕሮግራም ይዘት ሕግን የተፃረረ አለመሆኑንም አስምሮበታል፡፡ የሚዲያ ተቋማቱ ድርጊት ግን ሕግን የሚፃረርና በሕገ መንግሥቱ የተከለከለውን የቅድሚያ ምርመራ ያለመደረግ መብት የሚጥስ ሆኖ እንዳገኘው ፓርቲው አስገንዝቧል፡፡
‹‹በዘንድሮው ምርጫ የመወዳደሪያ ሜዳው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየጠበበ መምጣቱን የሚያሳይ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል፤›› ሲል ያሰፈረው የኢዴፓ መግለጫ፣ መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፋናና ለኢብኮ የላከው የቅስቀሳ መልዕክት እንዲስተካከል የቀረበው ጥያቄ አሳማኝ ምክንያት እንዳላካተተ አመልክቷል፡፡ 
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አክሲዮን ማኅበር እንዲሁም ኢብኮ ለኢዴፓ በጻፉት ደብዳቤ፣ ‹‹በአገሪቱ አሉ የሚባሉ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ሁሉ የኢሕአዴግ ሥልጣን መጠቀሚያና መጠበቂያ ብቻ እንዲሆኑ በማድረጉ፣ ተቋማቱ በገለልተኝነት እንዳይሠሩና ዓላማቸውን ለማሳካት የሚያስችል ነፃነት ብቻ ሳይሆን አቅምም እንዳይኖራቸው አድርጓል፤›› በማለት ኢዴፓ መልዕክት ለማስተላለፍ መሞከሩ ሕገ መንግሥቱን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅን፣ የምርጫ ሕጉን፣ የመገናኛ ብዙኃን ሕጉን፣ እንዲሁም የተቋማቸውን ኤዲቶሪያል ፖሊሲና ሌሎች ሕጎችን የሚጥስ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ በተለይ በኢብኮ የምርጫ ዴስክ ሰብሳቢ በአቶ ሰለሞን ተስፋዬ መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ተፈርሞ የወጣው የኢብኮ ደብዳቤ፣ ‹‹ይህ መልዕክት በሕገ መንግሥቱ የተቋቋሙ የዴሞክራሲ ተቋማትን ሁሉ ህልውና የሚክድና ተግባራቸውን የሚያንቋሽሽ፣ ሕዝቡ በተቋማቱ ላይ አመኔታ እንዲያጣ የሚያደርግ መልዕክት በመሆኑና ሕገ መንግሥቱን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ ምግባር ሕጉን አንቀጽ 29(1) እንዲሁም የድርጅታችንን ኤዲቶሪያል ፖሊሲ የሚፃረር ሆኖ አግኝተነዋል፤›› በማለት ገልጿል፡፡ የአዋጁ አንቀጽ 29(1) ማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ፣ የግል ዕጩ ተወዳዳሪ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅንጅት፣ ግንባር፣ ጥምረት፣ ንቅናቄ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ መሪ፣ ኃላፊ፣ ዕጩ፣ አባል፣ ወኪልና ተጠሪ የምርጫ ዘመቻውን ሰላም የሚያናጋ ወይም ግጭት የሚቆሰቁስ ወይም ስም የሚያጠፋ ወይም አመፅ የሚጋብዝ ወይም ሥጋት የሚፈጥር ንግግር ካደረገ የሥነ ምግባር ጥሰት እንደፈጸመ እንደሚቆጠር ይደነግጋል፡፡ 
ኢዴፓ በመግለጫው፣ ‹‹ለዴሞክራሲ ተቋማት ያለንን ተቆርቋሪነት ኢሕአዴግ በነፃነት እንዳይሠሩ እያደረጋቸው መሆኑን መግለጽና ተቋማቱ ለተቋቋሙለት ዓላማ ግብ መምታት ኢሕአዴግ እንቅፋት መሆኑን መግለጽን፣ እንዴት የተቋማቱን ስም ማጥፋት እንደሆነ ሊገባን አልቻለም፤›› ብሏል፡፡ 
ኢዴፓ ይህ የመብት ጥሰት የማይቆም ከሆነ ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ ከምርጫ ተሳትፎው ራሱን ሊያገል እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ የኢዴፓ የጥናትና ምርምር ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ፣ ‹‹ሐሳቦቻችንን በነፃነት ካልገለጽን ተሳትፎአችን የይስሙላ ስለሚሆን ድርጊቶቹ የሚቀጥሉ ከሆነ በምርጫው መሳተፋችን ከማጀብ ስለማይለይ ራሳችንን ከምርጫው ልናገል እንችላለን፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ አቶ ዋሲሁን ፋናና ኢብኮ አላስተናግድም ያሉት ጽሑፍ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መስተናገዱ ከክልከላው ጀርባ የግለሰቦች ፍላጎት ይኖር ይሆን እንዴ ብለው እንዲጠራጠሩ እንዳደረጋቸውም አመልክተዋል፡፡ ጉዳያቸውን ለፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አቅርበው በችግሩ ላይ ስምምነት መፈጠሩን ግን እንደ ጥሩ ምልክት ወስደውታል፡፡
በተመሳሳይ ኢብኮንና ፋናን በቅድሚያ ምርመራ ከከሰሱት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ሰማያዊና መድረክም ይገኛሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ፣ እስካሁን ፓርቲው ስምንት የተለያዩ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶች እንደተሰረዘበት ገልጸዋል፡፡ ፓርቲያቸው ሕገ መንግሥቱ በግልጽ ባሰፈረው የቅድሚያ ምርመራ ክልከላ ላይ እንደማይደራደር ያስታወቁት አቶ ዮናታን እንደ ኢብኮ፣ አዲስ ቲቪና ኤፍ ኤም 96.3 ሬዲዮ ያሉ ተቋማት መልዕክቶቹን እንዲያስተካክሉ መጠየቃቸው ሕገወጥ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ ይሁንና በጋዜጦች ላይ ግን የከፋ ችግር እስካሁን እንዳልገጠማቸው ገልጸዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ መጋቢት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢብኮ እንዲተላለፍ የላከው የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት የጎሳ ፌዴራሊዝም ለግጭት መንስዔ ነው ማለቱ፣ አንዱን ብሔር ከሌላ ብሔር የሚያጋጭ ነው በሚል ውድቅ እንደተደረገበት መግለጹ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ ‹‹የሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥርዓት/መንግሥት›› የሚለውን አጠራር እንዲያስተካክል ጥያቄ እንደቀረበለት ገልጿል፡፡ ከዚህ አስቀድሞ ኢሕአዴግ ‹‹ፖሊስን፣ ሚዲያውን፣ መከላከያ ሠራዊቱንና ደኅንነቱን ሰማያዊና ሌሎች ፓርቲዎችን ለማጥፋት ሲጠቀምባቸው ቆይቷል››፣ ‹‹ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤትና ሌሎችም ተቋማት ሕግ አክብረው አይሠሩም››፣ የሚሉትን ጨምሮ ሌሎች መልዕክቶች የአገሪቱን ሕጎች የሚፃረሩ በመሆኑ እንደማያስተናግድ ኢብኮ ለሰማያዊ በጻፈው ደብዳቤ ገልጾ ነበር፡፡ በተመሳሳይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መገናኛ ብዙኃን ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ይዘቶች የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ወደ አላስፈላጊ ግጭት ሊያመሩ የሚችሉና የሌላ ፓርቲን ስም የሚያጎድፉ በመሆናቸው፣ ለውጥ ካልተደረገ እንደማያስተናግድ ገልጾ ለሰማያዊ ፓርቲ ደብዳቤ ጽፏል፡፡
መድረክ በበኩሉ የተለያዩ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶቹ ላይ በተመሳሳይ የቅድሚያ ምርመራ እንደተደረገበት ይገልጻል፡፡ በተለይ ምርጫ ቦርድና የፍትሕ አካላት ነፃና ገለልተኛ አይደሉም በማለት ያቀረባቸው መልዕክቶች ውድቅ እንደተደረጉበት፣ የመድረክ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጥላሁን እንደሻው ገልጸዋል፡፡ 
ኢብኮ፣ ፋናና አዲስ ኤፍ ኤም እነዚህ ተቋማትና የመንግሥት ሚዲያን ነፃነት አስመልክቶ መድረክ ያቀረበው ትችት እንዲወጣ መጠየቃቸውን ጠቅሰዋል፡፡ መድረክ የፖለቲካ እስረኞች እንዳይኖሩ ያደርጋል በማለት ያቀረበው አማራጭም አሁን የፖለቲካ እስረኛ እንዳለ የሚያመለክት ስለሆነ አናስተናግድም እንደተባሉ አመልክተዋል፡፡ የኦሮሚያ መገናኛ ብዙኃንም ገዥው ፓርቲን ያለመረጃ እየተቻችሁ ነው በሚል መልዕክታቸውን ሳያስተላልፉ እንደቀሩ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ሥርዓቱን አትንኩ የሚል አዝማሚያ ነው ያለው፡፡ ሥርዓቱ ላይ የሚነካ ነገር ከሌለ የእኛ ጥቅም ምንድነው?›› ሲሉም አቶ ጥላሁን ጠይቀዋል፡፡ 
ኢዴፓ፣ ሰማያዊና መድረክን ጨምሮ በቅድሚያ ምርመራ መገናኛ ብዙኃኑን የሚከሱ ፓርቲዎች ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አቤቱታቸውን ማቅረባቸውንና ቦርዱ ምላሽ እንዳልሰጠም ተችተዋል፡፡ የቦርዱ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፣ የኢዴፓን ቅሬታ ገና ያልተመለከቱት ቢሆንም በሰማያዊና በመድረክ ላይ በሕጉ መሠረት ማስተካከያ አድርጉ ማለት ቅድሚያ ምርመራ ተደረገ የሚያስብል እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለሥልጣንና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓርቲዎቹ ጋር ባደረጉት የጋራ ውይይት አሠራሮቹ ላይ ስምምነት ተደርጓል፡፡ የሁለቱ ፓርቲዎች ጉዳይ ከዚያ ያፈነገጠ ነው፡፡ መልዕክታችን ትክክል ስለሆነ ሕጉን አይፃረርም የሚል አቋም ወስደዋል፡፡ ነገር ግን የመገናኛ ብዙኃኑ ደግሞ ኃላፊነት አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡ 
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፌስቡክ ይፋዊ ገጹ ላይ አንዳንድ ፓርቲዎች የተከለከሉ ይዘቶችን በምርጫ ቅስቀሳ እንደሚጠቀሙ የጠቀሰ ሲሆን፣ ከዚህም መካከል የምርጫ ቦርድን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፍርድ ቤቶችንና የፍትሕ አካላትን ገለልተኝነትና ነፃነት ማጣጣል፣ ብሔረሰብን ከብሔረሰብ የሚያጋጩ፣ አመፅ የሚቀሰቅሱ፣ ስም የሚያጠፉ እንደሚገኙበት ጠቅሷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝም ከመንግሥት ሚዲያ ተቋማት ጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ቆይታ ጥቂት ፓርቲዎች ሕገወጥ የቅስቀሳ ይዘት ማምጣታቸውን ያቁሙ ብለዋል፡፡  
ሪፖርተር ያነጋገራቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የሕግ ባለሙያ ግን በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠውን የቅድመ ምርመራ ክልከላን የሚፃረሩ ሕጎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የሕጎቹ ሕገ መንግሥታዊነት ላይ ጥያቄ ሳያነሱ ሕገ መንግሥቱን ብቻ በመጥቀስ መከራከር፣ በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የራሱ ችግሮች አሉት ብለዋል፡፡ 

Source: ethiopianreporter

U.S. Media Students Feature Ethiopia’s Reeyot Alemu in ‘Press Uncuffed’ Campaign

Reeyot Alemu is one in a number of journalists who have been prosecuted under the vaguely worded and broad-reaching anti-terrorism laws passed by the Ethiopian legislature in 2009. (IWMF/Getty Images)

Tadias Magazine
By Tadias Staff
Published: Sunday, March 29th, 2015
New York (TADIAS) — Students from the University of Maryland’s Philip Merrill College of Journalism and their professor — Pulitzer Prize-winning Washington Post reporter Dana Priest — have launched the Press Uncuffed campaign to raise awareness about journalists imprisoned around the world.
The campaign, which kicked off last week at the Newseum in Washington, D.C, is being conducted in partnership with the Committee to Protect Journalists (CPJ). It features jailed reporters from nine countries, including Ethiopian Reeyot Alemu, winner of the 2013 UNESCO/Guillermo Cano World Press Freedom Prize. Reeyot is currently serving a 5-year prison term under Ethiopia’s controversial terrorism law.
“These journalists were imprisoned for doing their jobs by governments fearful of a free press,” said CPJ Advocacy Director Courtney Radsch in a statement. “By recognizing these nine intrepid journalists-most of whom were jailed on anti-state or retaliatory charges-we hope to increase public pressure for their release and draw attention to the hundreds of others who have been silenced by their governments.”
In a press release CPJ added: “The journalists featured in the campaign have been imprisoned on anti-state or retaliatory charges. Two are being held without charge.”
They are: Ilham Tohti (China), Bheki Makhubu (Swaziland), Reeyot Alemu (Ethiopia), Khadija Ismayilova (Azerbaijan), Jason Rezaian (Iran), Yusuf Ruzimuradov (Uzbekistan), Mahmoud Abou Zeid Shawkan (Egypt), Ta Phong Tan (Vietnam) and Ammar Abdulrasool, (Bahrain).

source: tadias

Saturday, March 28, 2015

11 opposition leaders facing jail or death


Andargachew Tsige, death row, convicted of attempting to overthrow the government
Accused of attempting to overthrow the government, Ethiopian opposition leader Andargachew Tsige was sentenced to death in absentia in 2007. His party, Ginbot 7, seeks to end the country’s dictatorship and is Ethiopia’s largest exiled opposition movement. After Ginbot 7 was declared a terrorist organisation in the 1970s, Tsige fled and sought asylum in the UK.
While travelling to Eritrea in June 2014, Tsige disappeared during a stopover at Sana’a airport and was subsequently extradited to Ethiopia, where he remains on death row. Amnesty International has closely documented Tsige’s case, and online petitions call for his release.
the guardian

የ‹‹ነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› ዝግጅትና ቅስቀሳ ተጠንክሮ አምሽቷል


መጋቢት 20/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የ‹‹ነፃነት የፍትሓዊ ምርጫ›› ቅስቀሳ ማምሻውን በአዲስ አበባና በሌሎቹም ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በደብረታቦር ከተማ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 10 ሰዓት ቅስቀሳው በሰላም እንደተካሄደ አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ካድሬዎች የሞንታርቮውን ባለቤት አስፈራርተው ቀምተውታል፡፡ የሞንታርቮው ባለቤት ‹‹እንገድልሃለን›› ብለውኛል ብሎ እንደወሰደባቸው አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ በደሴ ከተማ ቅስቀሳው በመልካም ሁኔታ እየተካሄደ እንደሆነ በደሴ ከተማ የስብሰባው አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ በቅስቀሳው ወቅትም ህዝቡ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገልን ነው ሲሉ አስተባባሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በነገው ዕለትም ጠዋት 3 ሰዓት ጀምሮም በተለምዶ አራዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ተነስቶ ወቴ ስታዲየም እንደሚያቀና ገልጸዋል፡፡ በሌላ ዜና በአርባ ምንጭ፣ በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች ቅስቀሳው በተሳካ መንገድ እየተካሄደ እንደሚገኝ የሰልፉ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል በጅማ ከተማ የኦህዴድ ካድሬዎች የነገውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማደናቀፍ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ከታማኝ ምንጭ መረጃ እንደደረሳቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ወጣቶችን በ1ለ5 አደራጅተው ሰልፉን ለማደናቀፍ እየሰሩ እንደሆነ ደርሰንበታል ብለዋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ለነገው ሰላማዊ ሰልፍ በሰማያዊፓርቲ ጽ/ቤቶች የሚደረገው ዝግጅት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የኢህአዴግ መርዛማ ዘር በቅሎ ፍሬ አፈራለት

ባለፈው ሁለት አመት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ላይ ጥሩ ለውጥ ያየንበት ጊዜ እንደሆነ ሁላችንንም የሚያስማማ ይመስለኛል፡፡ ተጫዋቾቹ አረንጓዴ ቢጫና ቀይ የተቀላቀለበትን ማሊያ አድርገው ሜዳ ሲገቡ ስመለከት ደስታን አገኝ ነበር ምንም እንኳ በዚህ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ የቆየ ታሪካዊ ባንዲራችን ላይ የሆነ ያለቦታው የተቀመጠ ያአንድ ክልል ባህላዊ ምግብ ማለትም አንባሻ ምስል ተለጥፎበት ውበቱን ቢቀንሰውም ያን ያህል አላሳሰበኝም ነበር፡፡ ከዚያ ይልቅ እጅግ ያሳሰበኝ ነገር ለአገራችን ብሔራዊ መዝሙርና ለሀገራችን ያለን ብሄራዊ ስሜት ማነስ ነው፡፡ ታዝባችሁ ከሆነ ተጫዋቾቹ ወደ ሜዳ በገቡ ቁጥር የሀገሪቱ ብሄራዊ መዝሙር ይዘመራል፡፡ የሌሎች አገራት ተጫዋቾቹ የሀገራቸውን ብሄራዊ መዝሙር በስሜት ሲዘምሩት ተመልክቼ ቀናሁ፡፡ የኛዎቹ ተጫዋቾች ግን በካሜራ ፊት ተገትረው ከንፈራቸውን እንኳ ማንቀሳቀስ አይችሉም፡፡ ከንፈራቸውን ካንቀሳቀሱም ለመዝሙር ሳይሆን በሲዲ በሚንቆረቆረው መዝሙር መሀል የራሳቸውን ወሬ ለማስገባት ነበር፡፡ ለመዝሙር ሳይሆን ለፎቶ የቆሙ እስኪመስሉ ነው፡፡ ለምን ቢባል መዝሙሩን አያውቁትም፡፡ ለምን ቢባል ብሄራዊ መዝሙር ከሀገር ጋር ያለውን ቁርኝነት አያውቁትማ ይህ አጋጣሚ የጋራ ስሜት ብሄራዊ ክብር የሚሉት ነገሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀዘቀዙና እየጠፉ መምጣታቸውን የሚያመለክት ነው፡፡ አንዳንዶቹ ምን አልባት የደቡብ ኢትዮጵያ መዝሙርን ጠብቀው ይሆናል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ የአማራን መዝሙር ካልሆነ ሌላ ስሜት አይሰጣቸው ይሆናል፡፡ ሌሎቹ ከኦሮሚያ፣ ሌሎቹም ከጋንቤላ፣ አልያም ከቤንሻንጉል ወይም ደግሞ ከትግራይ ያልሆነ መዝሙር ምናቸውም መስሎ ላይታያቸው ይችል ይሆናል፡፡ እነ ሀይሌ፣ ደራርቱ ድል አድርገው ሲያበቁ በከፍተኛ የሀገር ወዳድ ስሜት ባንድራ አቅፈው ሲዘምሩና ሲያለቅሱ የተመለከተ አይናችን በአሁኖቹ ትውልዶች ላይ እንዲህ ባንዴ ወርዶ መመልከት እጅግ አስደንጋጭ ነው፡፡ ይህ የሚያሳየው በዘር፣ በሀይማኖት፣ በጎሳ፣ በቋንቋ ተከፋፍሎ በወያኔ ኢህአዴግ መንግስት የተዘራው ዘር ፍሬ ማፍራቱን ነው፡፡

የኢህአዴግ አላማ ትውዱን ራዕይ አልባ ማድረግ የሀገር ስሜት እንዳይኖረው ማድረግ በሀገሩ እንዳይኮራ ማድረግ እኔ ኦሮሞ እንጂ ኢትየጵያዊነት አይገባኝም፣ ጋምቤላዊ ካልሆነ ኢትዮጵያ ምንድነች፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ሀረሪ፣ ጉራጌ እንጂ ኢትዮጵያ ምትሏት ምኔ ነች የሚል ትውልድ ማፍራት ነው፡፡ እናም ተሳክቶለታል፡፡

ይህ አሁን የበቀለው ዘር ፍሬ እያፈራ ቢሆንም በጣም ስር ሰዶ መሰረቱን ከማጠናከሩ በፊት መድሃኒት ሊበጅለት ይገባል፡፡ መድሃኒቱ ደግሞ የኛው ትግል ነው፡፡ ተባብረን ሀገራችንን እናድን፡፡
Misrak Tesfay Dawit
Schluchtern

ነፃነት ያለትግል አይታሰብም

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ሁላችንም እንደምናስታውሰው ከዛሬ 22 ዓመታት በፊት እራሱን ለጭቁኑ ህዝብ አሳልፎ ለመስጠት እና በደርግ መንግስት በህዝቦች ላይ የሚያደርሰውን ጭቆናና የዲሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት ለመቅረፍ ብሶት የወለደው ኢህአዴግ ብሎ እራሱን የሰየመው ቡድን ይሄው 22 ዓመታት ሙሉ አስበውት እንደመጡት ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶችን በማስጠበቅ የህዝቦችን ችግር ከመቅረፍ ይልቅ ሀገሪቱን በግል ጥቅም እና አገዛዝ በሚያመቻቸው ብልሹ አሰራርና ፖሊሲ ቆርሰውና ከፋፍለው ሀገሪቱን ከማትወጣው አዘቅት ውስጥ እየከተቷት ይገኛሉ፡፡

ህውሀት/ወያኔ/ ባስቆጠራቸው 22 ዓመታት ውስጥ ብሄሮችና ብሄረሰቦች ተዋደውና ተከባብረው ከመኖር ይልቅ እርስ
በእርስ መጋጨት በሀገሪቱ ላይ ታይቶ የማይታወቅ የኑሮ ውድነት የሚስኪኑን ገበሬ መሬት በግድ እየተነጠቀ ለህውሃት ካድሬዎች እና ለውጭ ኢንቨስተሮች መስጠት የትምህርት ጥራት ማነስ የሙሁራንና የተማሪዎች በግድ የወያኔ ደጋፊ እንዲሆኑ ማስገደድ ያለበለዚያ የመማር ዕድል እንደማያገኝ በሚያነሱአቸው የመብት ጥያቄዎች በወያኔ ካድሬዎች እየታፈኑ ለሰው ልጆች ማሰቃያ ባዘጋጁት ማጎሪያዎች ውስጥ ፍፁም ሰብአዊነት በጎደለው ጭካኔ ስቃይ ይፈራረቅባቸዋል ብሎም በየአረብ ሀገራቱ ከመድፈር እስከ ከፎቅ መወርወር ድረስ ያለውን መከራ እየተቀበሉ ያሉት ሴቶች እህቶቻችን የመሳሰሉትን ዘርዝረን የማንጨርሳቸው መጥፎ ድርጊቶች የሀገሪቱ ገፅታዎች ሆነዋል እየሆኑም ነው፡፡ የዚህች ቅድስት ሀገር ትንሳኤ እና ሰላም የምትሹ የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሆይ ነፃነት ያለትግል በጭራሽ አይታሰብም ስለዚህም ይህች ሀገር ከጥቂት ወያኔዎች መኖሪያነት ወደ 90 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መኖሪያነት ለመቀየር መታገል የግድ ነው፡፡

ለዚሁም በኢትዮጵያ ትንሳኤ ወያኔን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሌት ተቀን ደፋ ቀና እያለ እየታገለ ካለው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ ጎን መቆም አለብን እላለሁ፡፡

ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ


Firezewed Berhanu

Friday, March 27, 2015

ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ …

በአለም ላይ ሰዎች መብታቸውን አስከብረው በነፃነት ሀሳባቸውን እንዲገልፁ እና እንዲኖሩ በአለም የተደነገገ ህግ ነው፡፡ ይህ ህግ/መብት/ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አይሰራም እረ እንደውም አይታሰብም፡፡ በእያንዳንዱ ግለሰብ የኢህአዴግ ካድሬዎችን ሳይጨምር ማለት ነው፡፡ በሀገሪቱ ፖሊሶች ወታደሮች እና ባለስልጣኖች በእየመስርያ ቤቱ በየቤቱ የሚደርስበት በደል እና የመብት እረገጣ ይህ ነው የማይባል ነው፡፡ ሰው በሰውነቱ እንኳን የማይከበርበት ሀገር ነው፡፡ ህዝብን በዘር በመከፋፈል በመጨቆን እና እርስ በእርስ በማባላት እነርሱም ስልጣናቸውን በመጠቀም በማን አለብኝነት ያሻቸውን እያደረጉ ሀገሪቱን ተቆጣጥረዋል፡፡ ታዲያ ወገን እሰከመቼ ነው በኢህአዴግ/ወያኔ/ መንግስት እና ግብረአበሮቹ ጭቆና እና የመብት እረገጣ ተንበርክከን እንደ ዜጋ በሀገራችን መብት ሳይኖረን የምንሰቃየው? እና ወገኖቼ ይህን ዘረኛና ጨካኝ አንባገነን መንግስት በጋራ ሆነን ልንታገል እና ከስር መሰረቱ ልንገረስሰው ጊዜው አሁን ነው ለዚህም ደሞ በጋራ ሆነን በፅኑ ልንታገለው ይገባል፡፡

ጎህ መፅሔት

“የስለላ ሰራተኞች መሯቸዋል፤ በጽናት የሚሰራ የለም”

የህወሃት አባል የአዲስ አበባ የደህንነት ኦፊሰር ከዳች!!
tplf spy
በኢትዮጵያ የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት መዋቅር ውስጥ ተመድበው የሚያገለግሉ የሰለላ ሰራተኞች በጽናት መስራት በማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተሰማ። ለዓመታት የስለላ ሠራተኛና የአዲስ አበባ ቀጠና ኦፊሰር የነበረች የህወሃት አባል መክዳቷ ታወቀ።
ጎልጉል ታማኝ የዜና ምንጮች አንዳሉት ድርጅቷ ህወሃትንና ታላቁን የአፈና ተቋም የስለላ ኦፊሰር የነበረችው የመክዳት ውጥኗ እውን የሆነላት ከስድስት ዓመት በኋላ ነው። በተደጋጋሚ ጊዚያት የዲፕሎማት ቪዛ እንዲሰጣት ፓስፖርቷን ለኢሚግሬሽን ብትልክም ያልተሳካላት ይህቺ የስለላ ኦፊሰር፣ በመጨረሻ የተሳካላት ስፔን አገር ለስለላ ስልጠና በማግኘቷ ነው።
አዲስ አበባ የሚገኙ ባልደረቦቿ “እርሷ ዕድለኛ ናት” በማለት ለጎልጉል ዘጋቢ እንዳሳበቁት፣ ኦፊሰሯ ስፔን አገር ከባልደረቦቿ ተለይታ ያመራችው ወደ አሜሪካ ነው። እዚያም እንደ ደረሰች እንደማትመለስ አረጋግጣለች። የትግራይ ክፍለ ሃገር ተወላጅና ታማኝ የህወሃት አባል የነበረችው የስለላ ሰራተኛ፣ ከቀበሌ ተነስታ ለከፍተኛ ሃላፊነት የበቃች ታማኝ ነበረች።
በብሔራዊ የደህንነት መዋቅር ውስጥ መሰላቸት፣ አለመተማመን፣ ጫና እንዲሁም ነጻ ሰዎች ሳይቀሩ የሚደረግባቸው ክትትል ጤና የነሳቸው ተበራክተዋል። በተለይም የህወሃት ያልተማሩ ነባር /አንጋፋ ባለሥልጣናት/ ታጋዮች የሚሰጡት ቅጥ ያጣ መመሪያና ወሬ ለቃሚዎቸ ከየመንደሩ ለብር እያሉ የሚያቀረቡት የሰላማዊ ሰዎችን ህይወት የሚያናጋ መርጃ ዕረፍት እንደነሳቸው የዜናው ምንጮች አመልክተዋል።
“በተለያዩ የሃላፊነት ደረጃ ተቀምጠው የሚያገለገሉ ባብዛኛው ደስተኛ አለመሆናቸው በገሃድ ስለሚታወቅና የመውጫው ቀዳዳ ስለተዘጋ” በሁሉም አቅጣጫ መሹለኪያ ፈላጊውና በሰላም መኖር የሚመኘው ክፍል እንደሚያይል ያመለከቱተ ዜና አቀባዮች “የኢህአዴግ ዙሪያ መለሱ ቆሽሾዋል፤ የእርስ በርስ መተማመኑም ኮስሷል” ብለዋል። በማያያዝም በርካታ አመራሮች አገር ለቅቀው መውጣት እንደማይችሉ አስታውቀዋል
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ (ሚያዚያ 2፤2006ዓም/April 10, 2014) “ከአገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣናት በጭንቀት ውስጥ ናቸው፤ “አሁን ያለው ኢህአዴግ ላዩ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል”” በሚል ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ ለአንባቢያን እንዲረዳ ከዚህ በታች በድጋሚ አትመነዋል፡፡
ኢህአዴግ በሙስና ስም የ”ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ የተከሰተው አለመተማመንና እርስ በርስ በጥርጥር የመተያየት ችግር ካድሬውን ማስጨነቁ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመፍራት የግድ ፓርቲውን መስለው እንደሚኖሩ ተገለጸ።stressed
የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ቀደም ሲል ኢህአዴግን ተሰናብተው የወጡና በተለያዩ የውጪ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ካሉ ያገኘውን መረጃ በመጥቀስ እንደዘገበው፣ የቀድሞ የትግል ጓደኞቻቸው “በደህና ጊዜ ተገላገልክ” በሚል በፓርቲው ውስጥ ችግር ስለመኖሩ እየነገሯቸው ነው። አብዛኞቹ ኢህአዴግን ተለይተው በሰላም ስለመኖር እንደሚያስቡ ነው የተሰማው።
የቤተሰቦቻቸው የወደፊት እድልና የነሱ በፍርሃትና በጭንቀት መኖር አሳዛኝ እንደሆነ የነገሩት የቀድሞ የኢህአዴግ ሰዎች “አሁን ያለው ኢህአዴግ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል” በማለት አንድ በሚኒስትር ዲኤታ ማዕረግ እያገለገለ ያለ የቀድሞ ጓደኛቸው እንደነገራቸው ገልጸዋል።
ለስራ እንኳን ካገር መውጣት የማይችሉ ባለስልጣኖች እንዳሉ ዘጋቢያችን አመልክቷል። በተቀመጡበት ሃላፊነት ወደ ውጪ የሚያስኬድ አጋጣሚ ሲኖር የሚከለከሉ እንዳሉም ያገኛቸውን መረጃዎች ጠቅሶ ዘግቧል። ለሃላፊዎቹ ደህንነት ሲባል የሚሰሩበትን ተቋምና ስም መናገር እንደማይችሉ በመጥቀስ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች “ባለስልጣኖቹ በመካከላቸው እርስ በርስ መተማማን ስለማይችሉ ችግራቸውን መወያየት እንኳን አይችሉም” ብለዋል፡፡
“በጣም የሚቀርቡኝ ጓደኞቼ ገንዘብ ወደ ውጪ እንድወስድላቸው እስከመጠየቅ ደርሰዋል” ሲሉ የገለጹት የቀድሞ የኢህአዴግ ባለስልጣን፣ ፓርቲው በሙስና ስም ያካሄደው የሽግግር ወቅት የማጥራት ርምጃ የፈጠረው ስሜት አሁን ድረስ እንዳለ ጠቁመዋል
ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ያቀኑ የቀድሞ የኢህአዴግ ሰው በማግኘት ተመሳሳይ መረጃ ያሰባሰበው ዘጋቢያችን “ኢህአዴግ በከፍተኛ የመበስበስ አደጋ ውስጥ ይገኛል። በዚህም የተነሳ ካድሬው ተዥጎርጉሯል” ሲል ሪፖርት አድርጓል። ኢህአዴግ በውስጥ ያለበትን ችግር ለማድበስበስ የአባይ ግድብ ላይ ትኩረት በመስጠት “የንቅናቄ ሃይል” በማስፋፋት ላይ እንደሆነም ጠቁሟል።
ድፍን ህዝብ የአባይ ግድብን አስመልክቶ ያለው ስሜት በበጎ መልኩ የሚታይ በመሆኑ ኢህአዴግ ይህንኑ የህዝብ ስሜት ለቅስቀሳና ለበሽታው መደበቂያ ለማድረግ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተጠቁሟል። የህጻናት ፕሮግራሞች ሳይቀሩ አባይ ላይ ያነጣጠሩ ቅስቀሳዎች እያስተላለፉ መሆናቸውን ያመለከቱት ሰው፣ “ስለ አባይ ግድብ የሚባለውና የሚሰራው ፕሮግራም ችግር የለውም። በአግባቡ ቢሰራበት ብሔራዊ ስሜት ሊገነባበትም በተቻለ ነበር። ይሁን እንጂ ዓለማው የችግር ማለባበሻ እንዲሆን መደረጉ ነው” ብለዋል።
“መለስ ኢትዮጵያን ቢወድ ኖሮ ከባድመ ጦርነት በኋላ የፈረሰውን ብሔራዊ አንድነትና መግባባት መልሶ መትከል ይቻል ነበር” በማለት የተናገሩት እኚሁ ሰው “በወቅቱ ይህንን ሃሳብ ያነሱ ሰዎች ነበሩ” ሲሉ ቁጭታቸውን ይሰነዝራሉ። በማያያዝም ኢህአዴግ የአባይን ግድብ ተንተርሶ ብሔራዊ አንድነት የሚገነባበት፣ መቀራረብና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ብሔራዊ መግባባት የሚደረስበት፣ ለወደፊቷ ኢትዮጵያ መሰረት የሚጣልበት ቢያደርገው እውነተኛው የኢትዮጵያ ህዳሴ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን በውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም ለመተካት ህዋሀቶች የሚያደርጉት ሽርጉድ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርት መቅረቡ ተሰምቷል። ይኽው ሪፖርት የቀረበላቸው ክፍሎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት የህወሃትን ከፍተኛ አመራሮች በማነጋገር ስህተት እንዳይሰሩ እየወተወቱ ነው።
source: goolgule

በፃፈው ምክንያት የታሰረ የለም ሲል የነበረው መንግስታችን ፅሁፎቻችንን እንደማስረጃ በመቁጠር ለክስ አሰናድቶታል፤



በፃፈው ምክንያት የታሰረ የለም ሲል የነበረው መንግስታችን ፅሁፎቻችንን እንደማስረጃ በመቁጠር ለክስ አሰናድቶታል፤ ለማስከሰስ የሚያበቃ ጭብጥ በውስጣቸው የያዙ ባይሆኑም ውድቅ የሚያደርግበት ፍርድ ቤት በሌለበት ይህ ለአቃቤ ሕግ የሚያሳስበው አይመስለንም፤ በተጨማሪም ምጡቅ መርማሪዎቻችን በዱላ "አብዮት ልንቀሰቅስ ነበር" ብለው ያስፈረሙን "ሕገ-መንግስቱ ተከብሮ እያለ ‹‹ሕገ-መንግስቱ ይከበር!›› በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ" የሚለው ኑዛዜኣችን እና ሌሎችን ማስረጃቸውን ከብዙ ቀናት ስርዝ ድልዝ እና ምጥ በኋላ ለአቃቤ ሕግ አስረክበዋል ፤አቃቤ ሕግም ክስ ብሎ ከተባባሪው ባልደረባዎቹ ጋር የስራ አስፈጻሚውን ትእዛዛ ሊያስፈጽም ቀጠሮ ይዘዋል፡፡ የእስከዛሬውን ታዝባችኋል በቀጣዩ ቀናት ከሰኞ ጀምሮ ከመንገድ የተሰበሰቡት ከዛን ቀን በቀር (ከተያዝንበት) አይተውን የማያውቁት ምስክሮች ቃላቸውን ያሰማሉ (እነሱም ከተገኙ) እኛም እንታዘባለን፡፡
የተመቻችሁ ከሰኞ ጀምሮ ለሶስት ቀናት ‹‹የአምባገነኖች ቀልድ በንፁሃን ወጣቶቿ ላይ›› በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መጥተው ይከታተሉ፡፡

ከምንም በላይ በጉዳዩ የእነ ዞላን ምሁራዊ ምክር ለጨቅላው ፍርድ ቤት ሲያካፍል እንሰማለን ምርጦቹንም ዞላ፣ናቲ፣ማሂ፣ኤዲ፣አቤሎ፣በፌ፣አጥኔክስ፣ ቴስ እና አስሚቲን በአካል እናያለን፡፡

ንጹሃንን ነፃ ብሎ መልቀቅ የሃሰት ውንጀላ ከመደረት እጅጉን የቀለለ ነው፡፡
ዛሬም አልረፈደም፡፡

ጋዜጠኝነትም ሆነ መጦመር ወንጀል አይደለም፡፡


Zone9

ሰማያዊ ፓርቲ በኢብኮ ከሚደረገው የምርጫ ክርክር ታገደ

• ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በኢብኮ ስቲዲዮ ከሚደረግው ቀረጻ ተባረዋል
ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ መጋቢት 18/2007 ዓ.ም ምሽት ኢብኮ ላይ ከሚቀርበው የ‹‹ግብርና እና ገጠር ልማት›› ላይ ሊያደርገው የኘበረው የምርጫ ክርክር ላይ እንዳይቀርብ መታገዱን የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ለቀረጻ ወደ ኢብኮ ስቲድዮ ባቀኑበት ወቅት የድርጅቱ ምክትል ስራ አስካሄጅ አቶ ተሻለ ‹‹ባለፈው ያላሰባችሁትን የምርጫ ክርክር እድል ሰጥተናችኋል፡፡ በመሆኑም ዛሬ መከራከር አትችሉም›› ተብለው መባረራቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በሰአብአዊ መብት ዙሪያ ኢብኮ ላይ በቀረው የምርጫ ክርክር ላይ አንድ ፓርቲ ለመቅረብ ፈቃደኛ አለመሆኑን በመገልጹ በክርክር 5 ፓርቲዎች እንዲቀርቡ የሚደረግ በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ዛሬ ምሽት በግብርና እና ገጠር ልማት ላይ የሚደረገው ክርክር ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ዕጣ የደረሰውና የፀደቀ ፕሮግራም ነው፡፡
በህገ ወጥ መንገድ ከቀረጻ ተባርሬያለሁ ያሉት ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ኢብኮ በፕሮግራም የተያዘንንን የምርጫ ክርክር ላይ እንዳንቀርብ ያደረገው እሁድ በ15 ከተሞች ሰልፎች እንዳለን ስለለሚያውቅና የዛሬው ክርክር በየ አካባቢው ያለውን ህዝብ እንዳያነቃቃ ተፈልጎ ነው›› ብለዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እስካሁን እየተደረጉት ባሉት ክርክሮች ሰማያዊ የኢህአዴግን ተግባራት እያጋለጠና ጠንካራ አማራጮችን እያቀረበ በመሆኑ ነው፡፡ ስለሆነም ኢብኮ ኢህአዴግን አግዞ ሰማያዊ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ እያደረገ ነው›› ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

Thursday, March 26, 2015

Fallacious Election of Ethiopia and Its Disasters

by Nathnael Abate M/ Norway
In most parts of our modern world democratic governments hold free, fair and regular or periodic elections to improve the administration system in their countries, thereby guaranteeing citizens the opportunity to change their leaders and to support new policies. Non democratic regimes, like a government of Ethiopia hold regular election but citizens are systematically forced in different ways to vote for them. Democratophobic government of Ethiopia holds regular and symbolic election in the name of democracy to learn new suppression techniques and to identify its supporters from non supporters. An identification of its allies along with the newly gained knowledge or technique from election will help the regime effectively to suppress critic voices and monopolize the country’s political or government power under its arms in future ruling years. Woyane of ‘Z Tigray’ regime hold periodic election not democratically to transfer government power and political authority into the hands of popularly elected or winner party but uses periodic election as instrument periodically to terrorize citizens of the country. The terrible consequences of Ethiopian elections are violations of democratic and human rights, cause of deaths for many and mass arrest. In Ethiopia elections or peaceful forms political struggles have never brought any limit to the power of ruling government, improvement in human rights situation or reform in government’s administration system. It had gone from bad to worse and from worse to worst.
The TPLF of Ethiopia symbolically holds periodic election every five years and the so-called constitution states that electoral institution to be free from any sort of government influence. However the electoral institute is not only influenced, nevertheless since its establishment it served as the survival gear of the ruling government. Article 102 of the constitution states independence of national election board to conduct in an impartial manner free and fair election in federal and state constituencies. It continues to state again that members of the board shall be appointed by the HPR upon recommendation of the prime minister. Here we can observe that the first part statement of the article clearly contradicts with the concept or notion of the second section. The first part of Article 102 tells us the election boards shall be independent and free from any form of influence. On the other hand, the second subdivision says the election boards shall be recommended by the prime minster and then later on elected by the votes of house of HPR. The prime minister is in charge of recommending his/her trusted friends or loyalists who are willing to execute whatever is ordered. The process of nomination and establishment of election board is just an appointment of the loyalists to certain position in separate suppression institute inside the circle of TPLF. The appointed officials are directly influenced by prime minster or other higher governmental bodies. This makes the country’s electoral system and process, electoral computations and vote results partial and biased. The contest and winning rooms for opposition parties are limited as well as votes are rigged by the electoral board since the election board is directly established by the Government to serve the will of government not to execute election and its process fairly. The malfunction of electoral board is an open threat to build democratic system.
In addition to the influence of National Election Board on the opposition parties and the outcome of election results, the harassment, assault, false accusation and imprisonment, severe restriction on freedom of speech, intolerance to open discussion and other negative influences of government hinders oppositionists from effective electoral computation. Oppositionists lack resources and budgets for their awareness creating campaign in nearest or most remote areas of the country. In reality power hungry TPLF doesn’t want efficacious computations of the opposition parties as result it holds back resources or finances which are allocated for the opposition political parties. Also there is campaign finance abuse by TPLF and agents, dependent electoral board and no balanced access to the media for all opposition political parties and candidates.
During the campaigns for election the importance of freedom expression is undisputable. Individuals should express their will and political opinions freely, take part in campaigning and at end elect the party that they choose and trust. In contrast, the TPLF regime has severely restricted freedom of expression and opinion, association and peaceful assembly of individuals, groups and organizations. This makes a tremendous roadblock for opposition political organizations to create awareness for public about their mission, vision and policies. Lack of open public discussion reduces the participation of citizens in their country’s socio-political affairs which in turn affects democracy building process according to an accepted international election standards and rules. In fact there exist electoral law to make the election peaceful, free, fair and democratic on the paper. But these laws are interpreted in the way they are convenient to keep the interests of TPLF. The so called Electoral Law of Ethiopia bears the following code of conduct of election and objectives. Let’s consider realities on the ground and the stated law as follow
1. To promote tolerance in a democratic electoral operation; under no circumstances TPLF and its system has tolerance in electoral process or in opposition opinions. TPLF never promoted tolerance either democracy instead every single opposition voices are systematically and openly suppressed. TPLF shoulders are not able to carry any political opinion that goes against them.
2. To foster free political campaigning and open public discussion; so far no opposition political groups had any free campaigning. Most opposition parties’ leaders and campaigners were humiliated attacked in Gondar, Wolayta, Oromia, in the capital Addis Ababa and many other parts of Ethiopia. No opposition political party is allowed holding open public discussion. The ruling minority junta is scared of allowing open public discussion. Also in the country where freedom of speech is severely restricted, it is impossible to hold open public discussion. Woyane knows well its fate, if open public discussion is held.
3. To enable the conduct of free and fair election. On this section it says any political organization including TPLF itself or private candidate must therefore respect, publicize, educate the electors and guide its candidates, representatives and supporters to respect the code and take necessary actions to realize it. But none of the listed codes are respected by the TPLF of Z Tigray and these laws are simply written on the paper to fool or attract foreign donors and to establish symbolic opposition parties which are not allowed to go beyond the stated limit.
In general the hope of removing Woyane of Z Tigray from government power and democratically transferring political power in to the hands winner political party is impossible from palpable evidence of Ethiopia’s political situation. This cumulative reason brings us to the conclusion that the outcome of Ethiopian election is predetermined. The above listed methodical fortification, open and hidden barriers are all the techniques which TPLF use to hold back opposition political organizations from effective electoral computation before election. At the time of election processing an illegal interference of TPLF government in the process of election such as vote counting and publicizing the election result is clear in addition to electoral board frauds. Both the governments’ illegal interference and election board dishonesty makes the electoral fraud to be outlawed jointly by the government and electoral body or legislation. The electoral fraud of Ethiopia includes the fabrication of electoral results, increasing the vote share of TPLF and reducing or weighing down the vote share of opposition parties.
Shortly after symbolic TPLF election ends post election terrorization of oppositionists and non allies of government starts. Government targets defenseless non-supporters, opposition parties (leaders, members and institution) and anybody who criticizes the system. Those who are found to be anti-TPLF coalition government or being in connection with opposition political parties will suspended or sacked from their jobs, dismissed from their positions, denied access to employment or other opportunities and in most cases systematically persecuted and sentenced years of imprisonment. For instance an iconic Ethiopian politician and opposition political leader Anduale Aragie was one of the victims of post election persecution by the government. Another citation is post election crackdown of government in 2005 in capital Addis Ababa during peaceful protest of the voters. The peaceful rally was interrupted by police brutality which led to death of hundreds of innocent and arrest of 1000s including figure opposition political leaders. Election 2005 was the event that led TPLF to devise a new suppression strategy to control powerful opposition politicians, journalists and political activists. After a few years later TPLF introduced the so-called anti-terrorism law to hunt down any dissents. Anti terrorism legislation enabled TPLF to arrest famous opposition figures, journalist, human rights activists and others. These Ethiopians were persecuted and imprisoned for no crime but only for holding different political opinion and view.
TPLF regime has made evident the notion that elections alone cannot establish and bring democracy in Ethiopia. To build democratic system and establish strong democratic institution in Ethiopia it is essential to remove Woyane by armed struggle either through public disobedience and all other possible ways. Without democracy’s other essential elements such as consent of the governed, constitutional limits, the protection of human, minority and democratic rights, accountability and transparency, a multiple party system, economic freedom and the rule of law elections alone cannot guarantee the freedom and democracy. It is well known that the democratic institutions in Ethiopia are very weak and elections are easily used by violent and dictator regime to monopolize government power for life long. Therefore it is essential to create unified web like network of opposition outside and inside the country by using all available measures and techniques to bring an end to long-standing dictator regime of Ethiopia.
The writer could be reached at nathanialoret@gmail.com
Facebook Nathnael Abate 
Twitter @nathysaint
Source: ecadforum

ጉዞአችን ወደ ነፃነት ነው!! መዳረሻችንም የነፃነት አደባባይ ብቻ ነው!!

pg7-logoአለማችን አንባገነን ስታስተናግድ ወያኔ የመጀመሪያው አይደለም። ዘረኛንም እንዲሁ …….. እኛም ስለነፃነት ብለን ለትግል ሰንነሳ የመጀመሪያዎቹ አይደለንም …… አለማችን እንደየዘመኑና እንደ የወቅቱ አንባገነኖች ያለ የሌለ የመሳሪያና ወታደራዊ ሀይላቸውን በመጠቀም ህዝብን በፍርሀት አሸማቀውና ረግጠው ለመግዛት ሲውተረተሩ በተደጋጋሚ ታይተዋል። በዚያው ልክ ህዝባዊ ሀይልና መመከት ተስኗቸው ሲንኮታኮቱ በተደጋጋሚ የታየ ወደፊትም አናባገነኖች እስከተከሰቱ ድረስ በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገው መቀመቅ ሲወርዱ መታየቱ አይቀሬ ነው ። ህዝብ የወደደውን አስተዳዳሪ እንጂ ረግጦ ሊገዛው የሚፈልገውና አንባገነን ተቀብሎ አያውቅም ፤ዛሬም አልተቀበለም ፤ ነገም አይቀበልም ። ይህን በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በተደጋጋሚና በጉልህ የሚታይ ግዙፍ እውነት መቼም ተቀብለውና ከታሪክ ተምረው ስለማያውቁ አሳፋሪው ውድቀታቸው በተደጋጋሚ ሲታይ አለ።
ሀገራችን የአለማችን አካል እንደመሆኗ አንባገነኖች ተፈራርቀውባታል። አንባገነኖችም በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገውባ ታል። ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ትልቅ ወታደራዊ ሀይል የነበረው የትናንቱ ደርግ እንደ እንቧይ ካብ ሲናድ ተመልክተናል። አንባገነኖችመናገር እንጂ መስማት የማ ችሉ፤ ማየት እንጂ ማስተዋል የተሳናቸው በመሆናቸው እነሆ ዛሬም የወያኔ ዘረኛው ቡድን ህዝባ ላነሳው የነፃነትና የፍትህ ጥያቄ ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል በጠራራ ጸሀይ በማሰለፍ መቼውንም ያልተቻለ ውን ህዝብን በሀይል አሸማቆ ለመግዛት መከራውን ሲያይ ይስተዋላል። ለዚህም ነው ….. ከሌላው የሀገራችን ክልሎች ከፍ ባለ ሁኔታ የህዝባዊ እንቢተኝነት እየታየ ባለበት ጎንደርና አካባቢው በሰራዊት ማጥለቅለቅ የተያያዘው።
ለሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችና ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች የሚሰጡት ምላሾች እስር፤ አፈናና ግድያ ከሆነ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ማስከተሉ አይቀሬ ነው። በእስር ፤በአፈናና በግድያ እንዲሁም በሰራዊት ሀይል ህዝብን በማሸማቀቅ በስልጣን መቆየት የሚቻል ቢሆን ደርግም ከቤተ-መንግስት ባልወጣ፤ ወያኔም ዛሬ ከቤተ-መንግስቱ ባልተንፈልለሰ ነበር። ይህ ደግሞ ሊያስተምር በተገባ ነበር።
እስከ ዛሬ የትኛውም አንባገነን ስርአት በሚተማመንበት የወታደራዊ ሀይል አማካይነት የመንኮታኮቻቸውን ሰአት በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት የቻለ እንደሌለ ሁሉ ወያኔም ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል ሲያርመሰምስ ውሎ ቢያድር ውድ ቀቱን በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት እንደማይችል በተለይ እንቢ ለነፃነቴ፤ እንቢ ለሀገሬ… ብለን ለትግል የተነሳን ሀይሎች በመረ ዳት፤ ይበልጡኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይበልጥ እያሰፋን የጀመርነውን የነፃነት ጉዞ ከነፃነታችን አደባባይ ለማድረስ ሌት ተቀን የመስራት ሀላፊነታችናና መወጣት ይገባናል።
በጎንደር የሚታየውን የአልገዛም ባይነት ትንቅንቅ በሌሎች ክልሎችም በማቀጣጠል፤ በደብረወርቅ የታየውን የመምህራን የስራ ማቆም አድማ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማስፋት፤ እንደ ድምፃችን ይሰማ ሁሉ ተቃውሞን ወደ እንቢተኝነት በማሸጋ ገር …… ወዘተ የነፃነታችንን ቀን ለማቅረብ መከፈል የሚገባውን መክፈል ይገባናል።
በደርግ ል የተነሳው እንቢተኝነት እያየለ ሲመጣ ያሰለፈው ሰራዊት ወያኔን አጅቦ የደርግን ቀብር እንደቆፈረለት ሁሉ ዛሬም በወያኔ ላይ እየተቀጣጠለ የሚገኘው ህዝባዊ እንቢተኝነት እየጠነከረ በመጣ ቁጥር የደረደረው ሰራዊት የወያኔን ቀብር ቆፋሪ ከመሆኑ እንደማኢመለስ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን በመማር ነፃነታችንን ለማስከበር የጀመርነውን የእንቢተኝነት ትግል በ መ ላው የሀገራችን ክፍሎች በማስፋትና በማቀጣጠል አይቀሬውን የወ ኔ ቀብር ለማቅረብ በአንድነት የነፃነት ጉዞውን እንቀ ላቀል። የጀመርነው የነፃነት ጉዞ መቆሚያው የነፃነታችን አደባባይ መሆኑን በተግባር ከምናሳይበት ወቅት ላይ እንገኛለንና በአንድነት እንነሳ!!!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!

ሴት ጦማሪያን በተደጋጋሚ ሲያቀርቡት የነበረው አቤቱታ ውድቅ ተደረገ

318a893f13f5573daf0e70cc6261182f_L
ተጻፈ በ  ታምሩ ጽጌ
‹‹በቂ ማስረጃ አቅርበን አላቀረባችሁም መባሉ ተገቢ አይደለም›› ጠበቃ አመሐ መኰንን
በተጠረጠሩበት የሽብርተኝነት ወንጀል በሚያዝያ ወር 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ የተመሠረተባቸውና ዋስትና ተከልክለው በማረሚያ ቤት የሚገኙት ሴት ጦማሪያን ማኅሌት ፋንታሁንና ኤዶም ካሳዬ፣ ከአያያዝ ጋር በተገናኘ
በማረሚያ ቤቱ ችግር እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ያቀርቡት የነበረው አቤቱታ፣ ‹‹በማስረጃ የተደገፈ አይደለም፤›› ተብሎ መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በተሰጠ ብይን ውድቅ ተደረገ፡፡
በማረሚያ ቤት የሚገኝ ማንኛውም ታራሚና ተጠርጣሪ የሚደረግለትን ወይም የተፈቀደለትን መብት እነሱ መነፈጋቸውን ክሱን እያየው ላለው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛውን ወንጀል ችሎት አመልክተዋል፡፡ ጦማሪያኑ እንዳስረዱት፣ ከእናትና ከአባታቸው በስተቀር ሌላ ሰው እንዳይጠይቃቸው ተከልክለዋል፡፡ እነሱም ቢሆኑ የሌሎቹ ታራሚና ተጠርጣሪ ቤተሰቦች በማይመጡበት ሰዓት ቀርበው ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ እንዲያነጋግሯቸው መደረጉን አስረድተዋል፡፡
ሽብርተኛ መሆናቸው በፍርድ ቤት ተጣርቶና ተረጋግጦ ፍርድ ሳይሰጥባቸው እንደ አሸባሪ መቆጠራቸው፣ በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን ንፁኅ ሆነው የመገመት መብታቸውን የሚያሳጣ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዳይቀላቀሉ መደረጋቸውንና ሌሎችንም ደርሰውብናል የሚሏቸውን ችግሮች በቃላቸውና በጽሑፍ ማቅረባቸውን ጠበቃቸው አቶ አመሐ መኰንን ገልጸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በሰጠው ብይን ያቀረቡት አቤቱታ ተደጋጋሚ ቢሆንም በማስረጃ ያልተደገፈ መሆኑን ገልጾ፣ አቤቱታውን እንዳልተቀበለው በማስታወቅ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት የተለያዩ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኃላፊዎች እየቀረቡ ለፍርድ ቤቱ ማብራሪያ መስጠታቸውን ያስታወሱት ጠበቃ አመሐ፣ በተለይ አንድ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ቀርበው በመነጋገር ችግሩን እንደሚፈቱት በመናገራቸው፣ ማረሚያ ቤት ድረስ በመሄድ አምስት ሰዓታት የፈጀ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በመስማማታቸው፣ ጦማሪያን ማኅሌት ፋንታሁንና ኤዶም ካሳዬ የፈለጉትን ያህል ጠያቂ ማስመዝገብ እንደሚችሉና በሌሎችም ችግሮች ላይ ተስማምተውም እንደነበር አክለዋል፡፡ ነገር ግን ተግባራዊ ማድረግ ባለመቻላቸው ጦማሪያኑ በድጋሚ ‹‹ችግራችን ሊሻሻል አልቻለም›› በማለት ለፍርድ ቤቱ ማመልከታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ማስረጃ አልቀረበም በማለት የተሰጠው ብይንም ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሙስና አሳነባሪዎችና ሻርኮች !!! ግርማ ካሳ

በዘጠና ሰባት አዲስ ዜና የምትሰኘዋ ነጻ ጋዜጣ ላይ የትምህርት ሚኒስቴሯ ገነት ዘዉዴ፣ የዉሃ ሃብት ሚኒስትሩ ሽፈራው ጃርሶ እና የከተማ ልማት ሚኒስተሩ ሃይሌ አሰግዴ ሶስት ትላልቅ ፎቆች እንደነበራቸው  ፎቶዎችን ዋቢ በማድረግ ዘግባ ነበር።
ያለፈውን ትተን ወደ አሁን ስንመለስ ደግሞ አይን ባወጣ መልኩ ከፍተኛ የሆነ የስልጣን መባለግን እያየን ነው። በአዲስ አበባ ቦሌ መድሃኔአም ፊት ለፊትና በቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጎን፣ የሚሰሩትና የተሰሩት ከአራተኛ ፎቅ ጀመሮ ያሉ ሕንጻዎች 90% በላይ የሆኑቱ፣ የሕወሃት ጀነራሎችና ባለስልጣናት ንብረት እንደሆኑ ይነገራል። በስምቸው፣ አሊያም በቤተሰባቸው ስም ያሰሩት ወይም የገዙት።
ለምሳሌ የሚከተሉትን ፎቶዎች ይመልከቱ። እነዚህ ፎቆች የሕወሃት ጀነራሎች እያሰሯቸው የነበረ አሁን ያለቁ ፎቆች ናቸው። እነዚህ ጀነራሎች ገንዘቡን ከየት አምጥተው ነው እንደዚህ አይነት ፎቅ የሚሰሩት የሚል መሰረታዊ ጥያቄ ይጠየቃል። መልሱን ለተመልካች መተዉ የሚሻል ይመስለኛል።
ሌላው ኢትዮጵያዊ በጠኔ እየተቃጠለ፤ ኢትዮጵያዊያን የኮንዶሚኒየም እጣ ዉስጥ ለመግባት ከአስር አመት በላይ እየጠበቁ፣ አምስት ሚሊዮን ህዝብ በምትኖርባት ከተማ በምርጫ ሰሞን ለፖለቲክ ተብሎ ጥራት በሌላው ሁኔት ጥቂት ሺዎች ኮንዶሚኒየም ብቻ እየተሰሩ፣ የኑሮ ዉድነት ሽቅብ ወደ ላይ እየተመዘገዘገ እነዚህ የሕወሃት ጀነራሎች ፎቆቻቸውን በአንዴ፣ ቢዝነሶቻቸን በአንዴ ገንብተው መጨረሳቸው፣ ያንን ያህል ወጭ የማወጣት አቅም ማግኘታቸው ተደባብሶ የሚያልፍ ነገር አይደለም። ኢትዮጵያ በርግጥ ለጥቂቶች ገነት ለብዙሃኑ ግን ገሃነም መሆኗን የሚያሳይ ነው እነዚህ ጀነራሎችና ሕወሃቶች፣ ወይም ከሕወሃቶች ጋር ትስስር ያላቸው፣ እላይ እየደረሱ (ሰርተው ቢሆን እሺህ ግን ሰርቀዉና መዝብረው) ሌላው ተምሮም፣ ጥሮም ግሮም፣ ኑሮን መግፋት ሲያቅተው ማየት በርግጥ እንደ ሕዝብ መውደቃችንን እና መዋረዳችንን የሚያሳይ ነው።
ይሄንን ስንል ፈጥረን እያወራን እንዳልሆነ ይታወቅልን። የምትመለከቷቸው ፎቶዎች ይመስክሩ። ሕሊና ያለውም ራሱን ይጠይቅ። ይሄ የስልጣን መባለግና የሕዝብን ንብረት መመዝበር፣ ህዝብን መናቅ አይደለምን ? ይሄ መንግስታዊ፣ ወያኔያዊ ሌብነትና ሙስና አይደለምን ? የሚያስቀው የማይታዘዙላቸውን ወይንም ጥያቄ መጠየቅ የጀመሩትን፣ ትናንሽ አሳዎችን በሙስና ስም እያጠመዱ፣ «ሙስና፣ ሙስና» ይሉናል። ሆኖም የሙስና አሳነባሪዎችና ሻርኮች እነርሱ ራሳቸው እንደሆኑ ግን የሚገነቧቸው ፎቆች ይመሰክራሉ።
እነዚህ ጀነራሎች እንደው በዛ ቢባል የሚከፈላቸው 10 ሺህ ብር ነው። የወር ደሞዛቸውንም እንዳለ ቢያጠራቅሙ በአመት ወደ 120 ሺህ፣ በሃያ አመት ደግሞ ወደ 2 ሚሊዮን ብር ቢሆን ነው። ምግብ፣ ልብስ፣ የመኪና ነዳጅ፣ ለልጆች የሚያስፈልጉ ወጨዎች አሉ። አሁን ባለው የኑሮ ዉድነት አንድ ኩንታ ጤፍ 2400 ብር ነው። ስለዚህ። ለአስቤዛ የሚወጣው ወጭ ቀላል አይሆንም። ግማሹን ደሞዛቸው አጥፍተው ግማሹን አጠራቅመው ነው ብንል እንኳን ሊኖራቸው የሚችለው ከአንድ ሚሊዮን ብር አይበልጥም። ታዲያ 40 50 ሚሊዮን ብር ከየት አምጥተውት ነው ?
ተበድረው ነው የሚል ክርክር ሊነሳ ይችላል። ፎቶዎቹ ላይ የታየዉን ትንሹን የባጫ ደበሌን ፎቅ እንመልከት። እንደው በጣም ሃሪፍ ባንክ ተገኘና 12 ሚሊዮን ዶላር 3.0 % ወለድ በሰላሳ አመት ከፍሎ ለመጨረስ ብድር ተወስደ ቢባል እንኳን፣ ባጫ ደበሌ በወር 50 ሺህ ብር መክፈል ይኖርበታል።
የጀነራል ወዲ አሸብርን 55 ሚሊዮን ብር ፎቅ ከወሰድን ደጎ፣ ወዲ አሽብር ወርሃዊ ክፍያ 210 ሺህ ብር በወር ነው የሚሆነው።
ማንም ፕሮፌሽናል ባንክ ከወርሃዊ ገቢያችን 40% በላይ ያለው ብድር አያበድርም። ባጫ ደበሌና ወዲ አሸብር 10 ሺህ ብር ይከፈላቸው ከነበረ፣ ሊበደሩ የሚችሉት የወር ክፍያው 4 ሺህ ብር የሚሆን ብድር ብቻ ነው። ታዲያ 50 ሺሃና 210 ሺህ ወርሃዊ ክፍያ መክፈል የሚጠይቅ ብድር ሊያበድር የሚችል ባንክ የት ይገኛል ?
እንግዲህ ያለ ምንም ጥርጥር፣ እነዚህ ጀነራሎችና የሕወሃት ባለስልጣናት ስልጣናቸውን፣ የያዙት ጠመንጃ ተጠቅመው ከሕዝቡ የዘረፉት ገንዘብ ለመሆኑ ማንም ያወቀዋል።