Wednesday, December 31, 2014

ሰበር ዜና ፖሊስ የደብረማርቆስ ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ ነው

• ‹‹ኢህአዴግ አይገዛንም!›› ተማሪዎቹ
ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ የደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ በትናንትናው ዕለት ኢህአዴግን የሚተቹ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ይሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ ወጥተው 20፣ 20 ሆነው በጠባብ ክፍል እንዲሰለጥኑ ከመደረጉም ባሻገር ጥያቄ የሚያነሱት ላይ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት ጥያቄ ያነሳሉ የተባሉት ተማሪዎች ስልጠና ወደሚሰጡባቸው ትምህርት ቤቶች ግቢ እንዳይገቡ ከመደረጉም ባሻገር የድብዛ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጠናውን መቃወማቸውን ተከትሎ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሰሙ የተክለሀይማኖት መልስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እርምጃውን በመቃወም ለድብዛ ተማሪዎች ድጋፍ መስጠታቸው ተገልጾአል፡፡
የሁለቱም ትምህርት ቤት ተማሪዎች በጋር በመሆን ከተማው አደባባይ ላይ በመውጣት ‹‹አህአዴግ አይገዛንም፣ ኢህአዴግ ሌባ፣...›› የመሳሰሉ መፈክሮችን በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለጻቸውን ተከትሎም ፖሊስ ተማሪዎቹን እያፈሰ ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዱ ተሰምቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ጥያቄ የሚጠይቁና ፖሊስ ተቃውሞውን አደራጅተዋል ብሎ የሚጠረጥራቸውን ተማሪዎች እየፈለገ እያሰረ መሆኑን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን በ17ቱም ወረዳዎች የሚገኙ ተማሪዎች ስልጠናውን ካልወሰዱ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ፈተና ላይ እንደማይቀመጡ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ስልጠናውን መቃወማቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
Source:Negere Ethiopia

Tuesday, December 30, 2014

በሰላማዊ ትግል የህዝብ ድምፅ የሚረጋገጠው በምርጫ ነው ብለን እናምናለን – የሰማያዊ ም/ሊቀመንበር



አቶ ስለሺ ፈይሳ የሰያማወኢ ፓርቲ ም/ሊቀመንበር ናቸው። በድርጅቱ ደንብ መሰረት፣  የምርጫ ጉዳይ ሃላፊ ናቸው። በመጪው ምርጫ ዙሪያ ከሚሊዮኖች ድምጽ ጋዜጣ ጋር ቃለ መልልስ አድርገዋል። የሚሊዮኖች ድምጽ ጋዜጣ በአንድነት ፓርቲ ኤዲቶሪያል ቦርድ ታትማ ከሕዝብ የምትሰራጭ ጋዜጣ ናት። ይች ጋዜጣ ከፍኖተ ለነጻነት ጋዜጣ በተጨማሪ ሁለተኛ ጋዜጣ መሆኗ ነው)

ሚሊዮሞች ድምጽ – የ2007 ምርጫን እንዴት እየጠበቃችሁት ትገኛላችሁ?

አቶ ሰለሺ – ምልክታችንን አሳውቀናል፤ ሰሞኑን እናረጋግጣለን፡፡ በፓርቲያችን ውስጥ ሰፊ ሥራ እየሠራን ነው፡፡ በምርጫ ጉዳይ ላይ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባላቱን አደራጅቶ የአባላቱን ጉልበት፣ ሀብትና ዕውቀትን በመጠቀም ዓመቱን ሙሉ ሰፊ
ሥራዎችን እየሠራን ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን ለየት የሚያደርገው፣ የምርጫ ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩን በምክትል ፕሬዚዳንቱ እንዲመራ በፓርቲው ደንብ ማስቀመጡ ነው፡፡በደንብ እየሰራን ነው፡፡ ንዑሳን ኮሚቴዎችን

ምርጫው ቦርድ በጊዜ ሰሌዳው መሠረት እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ ነገር ግን፣ ከምርጫው በፊት ብዙ መሠራት ያለባቸው ጉዳዮች እና መስተካከል ያለባቸው ነገሮች አሉ፡፡ ከጊዜ ሰሌዳው መፅደቅ በፊት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመነጋገር ቦርዱ ነገሮችን ማመቻቸት እንዳለበት ገልጾን ነበር፡፡ ነገር ግን ፍቃደኞች አልነበሩም፡፡ በጊዎን ሆቴል ይሄን ተቃውሞ አሰምተን፣ ስብሰባውን ረግጠን ወጥተናል፡፡ ይሄም ሆኖ የምርጫ ምልክት አስገብተናል፡፡ የምርጫ ፓርቲ ነን፡፡

በሰላማዊ ትግል የህዝብ ድምፅ የሚረጋገጠው በምርጫ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ለኢትዮጵያ የሚጠቅመው እና ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር ለማድረግ የምርጫ ሳጥን ወሳኝ ነው ብለን እናምናለን፡አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ ሲታይ፣ የምርጫ አስፈፃሚው አካልና መንግሥት ሌሎች አማራጮች ለሚያሳዩ ወገኖች በሩን የዘጉ እና ያደፈኑት ይመስላል፡፡

በፓርቲያችን አመራሮች እና አባላት ላይ በቅርቡ እንኳን የደረሰውን ድብደባ እና እስር ማየት በቂ ነው፡፡ በምርጫ ወቅት ሰዎች ድምፃቸውንና ተቃውሟቸውን ማሰማት አልቻሉም፡፡ ይሄን ይሄን ስትመለከት፣ ምን ያህል ፍትሃዊ ተዓማኒና ነፃ ምርጫ ይካሄዳል የሚለው በጣም ያሰጋናል፡፡

ምርጫ አስፈፃሚው፣ ምርጫ ቦርድ ከላይ እስከታች ድረስ ወገንተኛ የመሆኑ ጉዳይን ሙሉ በሙሉ እናምናለን፡፡ ማስረጃዎችም አሉ፡ ለህዝቡም ገልፀናል፡፡ ‹‹ምርጫ አለ፣ የለም›› የሚለው ያሰጋናል፡፡ የተሻለ የምርጫ ምህዳር የሚከፈት ከሆነ፣ በአዎንታዊ መንገድ ወስደን እንወዳደራለን፡፡ለዚህ ደግሞ በፓርቲው የምርጫ ግብረ ሀይል በኩል እየሠራን እንገኛለን፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ – ለምርጫው ምን ዓይነት ዝግጅት በማድረግ ላይ ትገኛላችሁ?

አቶ ስለሺ – ምልክታችንን አሳውቀናል፤ ሰሞኑን እናረጋግጣለን፡፡ በፓርቲያችን ውስጥ ሰፊ ሥራ እየሠራን ነው፡፡ በምርጫ ጉዳይ ላይ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባላቱን አደራጅቶ የአባላቱን ጉልበት፣ ሀብትና ዕውቀትን በመጠቀም ዓመቱን ሙሉ ሰፊ ሥራዎችን እየሠራን ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን ለየት የሚያደርገው፣ የምርጫ ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩን በምክትል ፕሬዚዳንቱ እንዲመራ በፓርቲው ደንብ ማስቀመጡ ነው፡፡በደንብ እየሰራን ነው፡፡ ንዑሳን ኮሚቴዎችን አቋቁመናል፡፡ በምርጫ ስንገባ የመጀመሪያችን ሊሆን ስለሚችል የሚያስፈልጉንን የምርጫ ሰነዶች እያዘጋጀን እንገኛለን፡፡

ለምሳሌ፣ የፓርቲው ዕጩ የመመልመያ ሰነድ፣ የፓርቲውን የሥነ-ምግባር መመሪያ እንዲሁም የፓርቲውን የታዛቢዎች መመልመያ መመሪያ እና የፓርቲው የምርጫ ወቅት የቅስቀሳ መመሪያ ሰነዶችን እየሠራን ነው፡፡ ትልቁ ሰነዳችን ደግሞ የምርጫ ማኒፌስቶ እያዘጋጀን ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ‹‹በምርጫው ምን ማግኘት አለብን?››፣ ‹‹የቱ ጋር ደካማ ነን?››፣ ‹‹የቱ ጋር ጠንካራ ነን?››፣ ‹‹የድጋፍ ቦታዎቻችንን (ደካማ እና ጠንካራ) ለመለየት ዳሰሳዊ ጥናት አድርገናል፡፡

በዚህ መሠረት በሀገሪቱ 10 የምርጫ ዞኖች በመክፈል እነዚህን የሚያስተባብሩ አምስት አምስት ሰዎች በአጠቃላይ 50 ሰው ያለበት አንድ የምርጫ ግብረ ሀይል በሀገር አቀፍ ደረጃ አቋቁመናል፡፡ ሰሞኑን በተፈጠረው ሁኔታ ነገሮች ስለተበላሻሹብን መጓተት ተፈጠረ እንጂ በቀጣይ እነዚህን የምርጫ ግብረ ሀይላት ከአዲስ አበባ እና ከክልል አምጥተን ለአንድ ሳምንት ያህል ከጥናትና ሥትራቴጂው ጋር ሴሚናር እንሰጣለን፡፡

የሚሊዮኖች ድምጽ – ህብረት ወይም ቅንጅት ሳትፈጥሩ፣ በተናጥል ተጉዛችሁ ለመንግስትነት የሚያበቃ ውጤት ማምጣት እና በሰላማዊ መንገድ ከኢህአዴግ ሥልጣን መውሰድ ትችላላችሁ?

አቶ ስለሺ –  ምርጫውን ነፃ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ ከስምንት ፓርቲዎች ጋር ትብብርን መመስረት ተችሏል፡፡ ከእነሱ ጋር እየሠራን ነው፡፡ ሌሎችም በዚህ ትብብር ውስጥ የየራሳቸው ተሳትፎ ነበራቸው፡፡ ዋና ዋናዎቹ መኢአድ እና አንድነት በራሳቸው ምክንያት ከትብብሩ ርቀዋል ብለን እናምናለን፡፡አሁንም ጥሪ እያደረግን ነው፡፡ በጋራ የህዝብ ድምፁን ለማግኘት አብረን መስራት አለብን፤ እንሰራለንም፡፡ የምርጫ ቦታን የመሻማትና ያለመሻማት ነገር ሊኖር ይችላል፤ እንደ ችግርም ሆኖ ሊገኝ ይችላል፡፡ ይሄ ችግር እንዲፈታ የቻልነውን ሁሉ እናደርጋለን፡፡

ጊዜው ሲደርስ ‹‹ማን የቱ ጋር ጠንካራ ነው?፣ የቱ ጋርስ ደካማ ነው››፣ ‹‹የተሻለ ድጋፍ የቱ ጋር ማን አለው?›› የሚለውን እያየን በትብብርና በቅንጅት ስትራቴጂ ነድፈን ለመስራት ፈቃደኞች ነን፡፡ ሁሉን ነገር በእኛ ብቻ ይሸፈናል ብለን አናምንም፡፡

መታወቅ ያለበት፣ 2002 ምርጫን አስመልክቶ ስታትስቲክስ ያወጣው መረጃ፣ መምረጥ ከሚችለውና ከተመዘገበው ህዝብ ኢህአዴግ ያገኘው 33 በመቶ ነበር፡፡ በወቅቱ የተወዳደሩ ተቃዋሚዎች ደግሞ 14 በመቶ፡፡ በድምሩ 48 በመቶውን በጋራ ይዘዋል፡፡ መምረጥ የሚችለው 52 በመቶ ሕዝብ ግን ለኢህአዴግም ሆነ ለተቃዋሚዎች ድምጽ አልሰጠም፡፡ በማንም ላይ ተስፋ እና ዕምነት አልነበረውም፡፡ በዚህ ምክንያት ራሱን ከምርጫው አግልሏል፡፡

ተቃዋሚዎች በሰፊው ከሰራን ሰፊው 52 በመቶ ዋነኛ አቅማችን ይሆናል፡፡ በሀገሪቱ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በሌሎችም ዘርፎች የዛሬ አምስት ዓመት ከነበረበት የባሰበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ሥርዓቱ እየተጠላ፣ ፖሊሲዎቹ እየተዳከሙ፣ ለኢህአዴግ ድምፅ የሰጠ ሁሉ ከእሱ እየራቀ ሊመጣ ይችላል፡፡ ሰፊ ድጋፍ የሚያደርግ ያልተነካ የመራጭ ሀይል ስላለ፣ እሱ ላይ አትኩረን እንሠራለን፡፡ በመገፋፋት እና በመበላላት ድምፅ እናጣለን ብለን አናስብም፡፡

ቢሆን እንኳ አንዱ በአንድ ቦታ ጠንካራ የድጋፍ መሠረት ካለው፣ ለእሱ እንተወዋለን እንጂ የግድ ሰማያዊ ካላመጣው ብለን አንልም፡ ይሄ ጊዜው ሲደርስ አስፈላጊ መዋቅራዊ ሁኔታዎችን በማድረግ ወይም ሥትራቴጂ በመንደፍ በዋናነት የህዝብን ድምጽ እናስጠብቃለን፡፡ ህዝብ ድምጹን እንዲሰጥና እንዲከበርለት በዋነኝነት እንሰራለን፡፡
Source; zehabesha

የኢንተርኔት እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መረጃዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር የሚያደርግ አዋጅ ተረቀቀ

ኢሳት ዜና-በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን  ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡

የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል የመረጃ መረብ አማካኝነት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም በአገር አንድነትና ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል ፣በአገር ደህንነት፣ ክብርና ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ፣የአገር ሚስጢርን የሚገልጽ ፣ አመጽና ጦርነትን የሚቀሰቅስ፣ የሰው ልጆችን ስብዕና ፣ነጻነት ወይንም ስነምግባር የሚጻረር ፣የሌሎችን እምነት የሚያንኳስስ መሆን እንደሌለበት ደንግጎአል፡፡
በተጨማሪም ሥራዎቹ ማንኛውንም የህብረሰተብ ክፍል፣ ብሔር፣ጎሳ፣ቀለም፣ጾታ፣ዘር፣ቋንቋ፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ አመጣጥ፣ ወይንም ሌላ መሰል አቋምንና ክብርን የሚነካ ወይም የሚያዋርድ፣ በህዝቦችና በሃይማኖቶች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይንም ጥላቻ የሚያስፋፋ፣ የግለሰብን ስም የሚያጠፋ፣፣ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን አመለካከት ስሜት የሚጎዳና ወደአልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ፣ የህብረሰተቡን ሞራል የሚጥስ ወይንም በሕግ የተከለከለ ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽም መሆን የለበትም ይላል፡፡
ተጠያቂነትም በተመለከተ ረቂቅ አዋጁ እንዳሰፈረው በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራም ለሚያስከትለው ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ወይም የፍትሐብሄር ጉዳት የፕሮግራሙ ሃላፊና የብሮድካስት አገልግሎት ሰጪው በአንድነት ተጠያቂ ይሆናሉ ይላል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራምን ቁጥጥርን በተመለከተ ከህብረተሰቡ በቅሬታ መልክ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመመርመር፣ተቆጣጣሪ የመመደብ ስልጣን ወደፊት ለሚቋቋመው ባለስልጣን መ/ቤት ሃላፊነቱን ይሰጣል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የቴሌቪዥንን ከአናሎግ ወደዲጂታል ሽግግርን ለማቀላጠፍና የግል ቴሌቪዥን ለመፍቀድ ይረዳል ተብሎአል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢትዮጵያ የሚዲያ ባለስልጣን የሚባል መ/ቤት ይቋቋማል፡፡
የብሮድካስት አግልግሎት የሚመራበትን ሥርዓት ለመደንገግ ከ15 ዓመታት በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 178/1991 የግል ቴሌቬዥን ጣቢያ ፈቃድ ለግል ባለሃብቶች የፈቀደ ቢሆንም ይህ ተግባራዊ ሳይሆን አዋጁ በቁጥር 533/1999 የተሻሻለ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሸሻለውም አዋጅ ቢሆን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ  የተፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ኢትዮጵያ ለዚህ ደረጃ ገና አልበቃችም በማለት አዋጁ እንዳይፈጸም እስካሁን ድረስ መከልከሉ የሚታወቅ ነው፡፡

የመሰናዶ ተማሪዎች የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሙ አሰሙ

• በሶስት ከተሞች ረብሻዎች ተነስተዋል
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቁመው እንዲወስዱ የተደረገውን የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ምንጮን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በስልጠናው ወቅት የህዝቡ አስተሳሰብ፣ የግል ሚዲያ፣ ተቃዋሚዎች ለኢትዮጵያ እድገት ጠንቅ ተደርገው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎች ይህንን አቀራረብ ተቃውመውታል፡፡ በአንጻሩ ከወራት በፊት ስልጠናውን የወሰዱት መምህራንም ዳግመኛ ስልጠናውን እየወሰዱ ቢሆንም ዝምታን መምረጣቸው ተገልጾአል፡፡
ተማሪዎቹ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ ከሆነ ለተቃዋሚዎችም ይፈቀድ፣ ለምን ለግጭት የሚጋብዙ ቅስቀሳ ትቀሰቅሳላችሁ፣ የኢህአዴግ ፖሊሲ ምሁራንንም ጭምር ለስደት የዳረገ ነው፣ ከቻይና እና ከኮሪያ የሚያስተሳስረን የታሪክም ሆነ የባህል መሰረት የለንም፣ ኢህአዴግ 23 አመት ያልተገበረውን ዴሞክራሲ ሊያስተምረን አይችልም›› የሚሉ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡
በስልጠናው ወቅት ተቃውሞዎች እየተነሱ ሲሆን በተለይም ደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ ላይ ተማሪዎቹ ‹‹ኢህአዴግ ሌላ፣ ኢህአዴግ ሌባ›› የሚል ጩኸት በማሰማታቸው ሲሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ 20፣ 20 ሆነው በየክፍሉ እንዲሰለጥኑ ተደርገዋል፡፡ በተለይ በደብረማርቆስ ከተማ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹ የካድሬ ስልጠና አንሰለጥንም በማለት መረር ያለ ተቃውሞ እያሰሙ እንደሚገኙ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
Source: Negere Ethiopia

የባህር ዳር መስዋዕትነት የማይቀረዉ ድል ዋስትና ነዉ

ወያኔ በየአመቱ ህዳር ወር መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያን ብሄር ብረሰቦች ሰብስቦ ዘፈን የሚያስዘፍንበትን በዐል ሲያከብር በተደጋጋሚ ከሚያሳማቸዉ መፈክሮች አንዱ የብሄር ብሄረሰቦች መብትና እኩልነት በህገመንግስታችን ተከበረ የሚል እጅግ በጣም አሳሳች የሆነ መፈክር ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ለይስሙላ ወረቀት ላይ ያሰፈረዉ ህገ መንግስት መግቢያዉ ላይ “እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች፤ ብህረሰቦች፤ ህዝቦች በነጻ ፍላጎታችን የህግ የበላይነትና በራሳችን ፍላጎት ላይ የተመሰረተ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብ በጋራ ለመገንባት ቆርጠን ተነስተናል” ይላል። መቼም ይህ ምንም በማያሻማ መልኩ ቁልጭ ብሎ የተቀመጠ ህገ መንግስታዊ አንቀጽ ሌላ ትርጉም ካልሰጡት በቀር የአማራንም ህዝብ ያጠቃልላል የሚል ሙሉ እምነት አለን። በዚህ ደግሞ የአማራን ክልል የማስተዳድረዉ እኔ ነኝ ባዩ ባዕዴንም የሚስማማ ይመስለናል። በተግባር ሲታይ ግን ይህ የወያኔ ህገ መንግስት ላይ ህዝብና መንግስት የሚተዳደሩበት ህግ ቀርቶ ህገ አራዊት እንኳን አይመስልም። ምክንያቱም በህገ አራዊት አሰራር ተመሳሳይ ዝሪያ ያላቸዉና በአ ያላቸዉ የዱር አራዊት ይከባበራሉ እንጂ አንዱ ሌላዉን አያጠፋም። ለምሳሌ አንበሳና አንበሳ ይረዳዳሉ ወይም አብረዉ አደን ይወጣሉ እንጂ እርስ በርስ አይተላለቁም፤ ነብርና አንበሳም ቢሆኑ በተገናኙ ቁጥር ተከባብረዉ ይተላለፋሉ እንጂ አንደ ወያኔ ብጤያቸዉን ባዩ ቁጥር አያጠቁም ወይም አይገድሉም።
ወረቀት ላይ የሰፈረዉን የወያኔ ህገ መንግስት የተመለከተ ሰዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎች መብታቸዉና ነጻነታቸዉ ተከብሮ የሚኖሩ ሊመስለዉ ይችላል። በእርግጥም ይመስላል። ምክንያቱም የወያኔ ህገ መንግስት ችግሩ አጻጻፉ ላይ ወይም ይዘቱ ላይ ሳይሆን በተግባር አተራጓጎሙ ላይ ነዉ። በ1987 ዓም የፀደቀዉ የወያኔ ህገ መንግስት በተግባር ሲታይ ብሄሮች፤ ብህረሰቦችና ህዝቦች የሚለዉ ቦታ ደብዛዉ ጠፍቶ ሁሉም ነገር ወያኔ ወይም ህወሓት በሚለዉ ቃል ተተክቷል፤ ወይም ሁሉም የአገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ተጨፍለቀዉ የትግራይ ልህቃን ወይም የህወሓት ሎሌዎችና ተላላኪዎች ሆነዋል። ለዚህ ነዉ አገራችን ኢትዮጵያ ወያኔ ያሰኘዉን የሚያዝባት የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ አንገቱን ደፍቶ የሚታዘዝባት አገር የሆነችዉ።
ሌላዉ ወያኔ ህገ መንግስቱ ዉስጥ አስፍሮ በየቀኑ እንደቤቱ ዉስጥ ምንጣፍ ከሚረግጣቸዉ ህገ መንግስታዊ አንቀጾች ዉስጥ አንዱ አንቀጽ 30 ንዑስ አንቀጽ አንድ ነዉ። ይህ አንቀጽ ማንኛዉም ሰዉ ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሠላም የመሰብሰብና ሠላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ ሙሉ መብት አለዉ ይላል። ሆኖም የዚህን አንቀጽ ሙሉ ቃል ከወያኔ የየቀኑ አረመኔነት ጋር ስናነጻጽር አንቀጹ የተጻፈበትን ወረቀት ያክል እንኳን ክብደት የለዉም። ይህንን ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ሠላማዊ ሠልፍ ባደረገባቸዉ ቦታዎች ሁሉ ወያኔ በተከታታይ በወሰዳቸዉ አረመኔያዊ እርምጃዎችና በፈጸማቸዉ ሰቆቃዎች ተመልክተናል። ለምሳሌ ባለፈዉ አመት አምቦ ዉስጥ አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ባህርዳር ዉስጥ ህገ መንግስታዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ ጥያቀያቸዉን ሠላማዊ ሰልፍ በማድረግ ያቀረቡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ህፃናት፤ ወጣቶች፤ አዋቅዎች ወንዶችና ሴቶች በአግዓዚ ነብሰ ገዳዮች ጥይት ተጨፍጭፈዋል።
ወያኔ በተደጋጋሚ ሠላም … ሠላም እያለ በአፉ ይናገር አንጂ ወያኔን ከሰላም ጋር የሚያገናኘዉም ሆነ ወያኔ ስለ ሰለም የሚያዉቀዉ ምንም ነገር የለም። እዉነቱን ለመናገር ኢትዮጵያ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፈኞችን የሚገድል፤ ሠላለማዊ ዜጋን አስሮ የሚደበድብና የሠላም መንገዶችን ሁሉ ቅርቅር አድረጎ የዘጋዉ ወያኔ ብቻ ነዉ። ሌላዉ ቀርቶ ወያኔ የሚያስበዉ፤ የሚያቅደዉና ዕቅዱን ወደ ተግባር የሚለዉጠዉ ከህዝብ ፈቃድና ፍላጎት ዉጭ ስለሆነ ልማት ብሎ የሚጀምራቸዉ ፕሮጀክቶች እንኳን የህዝብን ሠላም የሚያናጉና የሠላማዊ ዜጎችን ህይወት የሚቀጥፉ ጅምሮች ናቸዉ። ከሰሞኑ ደግሞ ባህር ዳር ዉስጥ እየታየ ያለዉ ህዝባዊ ቁጣ የዚሁ ወያኔ ልማት እያለ የቀሰቀሰዉ ህዝባዊ እሳት ዉጤት ነዉ።
ወያኔ እራሱን ልማታዊ መንግስት እያለ እየጠራ በሚወስዳቸዉ እርምጃዎች ሁሉ ከህዝብ ጋር መጋጨት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። ደቡብ ኦሞ ዉስጥ ሙርሲዎች በልማት ስም ከመሬታቸዉ ተፈናቅለዋል፤ አንፈናቅለም ብለዉ የተፋጠጡት ደግሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል። ታሪካዊዉ ዋልድባ ገዳም ዉስጥ ገዳም አለም በቃኝ ያሉ ሰዎች መኖሪያ አንጂ የእርሻ ቦታ አይደለም ብለዉ የተናገሩ መነኮሳት ቆባቸዉን አንደደፉ በቆመጥና በሰደፍ ተደብድበዋል። ጋምቤላና አፋር ዉስጥም በልማት ስም ከመሬታችን አታፈናቅሉን ብለዉ አቤቱታ ያቀረቡ ገበሬዎች ታስረዋል፤ ተግዘዋል ተገድለዋል። ለመሆኑ ወያኔ ልማት ብሎ አንድ ፕሮጀክት በጀመረ ቁጥር ህዝብን የሚያግዝና የሚገድል ከሆነ ልማቱ የሚታቀደዉ ለማነዉ? በልማቱስ ተጠቃሚ የሚሆነዉ ማነዉ?
በያዝነዉ ታህሳስ ወር መግቢያ ላይ ባህር ዳር ዉስጥ የአራት ሰላማዊ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አለም በቃኝ ብለዉ ለፈጣሪያቸዉ ያደሩትን መነኩሴ ጨምሮ ለአያሌ ሠላማዊ ዜጎች መቁሰልና መታሰር ምክንያት የሆነዉ ይሄዉ ወያኔ በልማት ስም የጀመረዉና የአካባቢዉን ህዝብ ፍላጎት ያላካተተዉ የወያኔ ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃ ነዉ። በእርግጥም አሁንም ድረስ ያልበረደዉ የባህር ዳሩ ህዝባዊ ተቃዉሞ የተቀሰቀሰዉ ወያኔ የባህር ዳርና የአካባቢዉ ህብረተሰብ የጥምቀት በዐል የሚያከብርበትንና የቤ/ክርስቲያን ንብረት የሆነዉን የቅዱስ ታቦት ማደሪያ ቦታ መንገድና ሱቅ እሰራለሁ ብሎ ማፈራረስ በመጀመሩ ነዉ።
ይህ በልማት ስም ሐይማኖታዊ የማመለኪያ ቦታን የማፈራረስና የቤ/ክርስቲያንን መሬት የመቀማት ሴራ የተዉጠነጠነዉ በወያኔ ቢሆንም የወያኔ ተላላኪ በመሆን ይህንን ከፍተኛ ወንጀል በገዛ ወገኖቹና ለጥቅሙ ቆሜያለሁ በሚለዉ ህብረተሰብ ላይ የሚያሰፈጸመዉ ግን ባዕዴን ነዉ። ባዕዴን ከዚህ ቀደምም በተከታታይ እንደታየዉ አማራዉ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በግፍ ሲባረርና ሲፈናቀል አፉን ዘግቶ የተመለከተና የአማራን ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ለወያኔ አሳልፎ የሰጠ ከሃዲ ድርጅት ነዉ። ባዕዴን ነኝ ብሎ እንደሚናገረዉ በእርግጥም ለአማራ ህዝብ መብትና ነጻነት መከበር የቆመ ድርጅት ቢሆን ኖሮ የለየለት የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነዉ ህወሓት አያገባዉ ገብቶ በአማራ ህዝብ ጉዳይ ላይ ሲፈተፍት ዝም ብሎ አይመለከትም ነበር።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ህዝብ ታሪክና አንድነት ብቻ ሳይሆን ባህሉን ፤ወጉንና ሐይማኖቱን ጭምር እንዳልነበረ ለማድረግ ያላደረጉት ነገር የለም። የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤ/ክኢርሰቲያን ጳጳስ አንስተዉ ቅዱስ መንበራቸዉን እጁ በደም ለተጨማለቀ ካድሬ በመስጠት ጥንታዊት ቤ/ክርስቲያናችንን ለሁለት አንድትከፈል አድርገዋል። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሏቸዉ ከሰሞኑ ባህርዳር ዉስጥ ህዝብ ጥምቀተ በዐል የሚያከብርበትንና የቅዱስ ታቦት ማደሪያ የሆነዉን ቦታ ከቤ/ክርስቲያን ቀምተዉ የንግድ ቦታ ለማድረግ ሞክረዋል። የእስልምና እምነት ተከታዮችን በተመለከተም ህጋዊዉን መጂሊስ አፍርሰዉ በእነሱ ፍላጎት ብቻ የሚመራ አሻንጉሊት መጂሊስ በማቋቋማቸዉ ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር የፈጠሩት ግጭት ዛሬም ድረስ እንደተቀጣጠለ ነዉ።
የወያኔ ነብሰ ገዳዮች አዲስ አበባ፤ አምቦ፤ ደቡብ ኦሞ፤ ጋምቤላ፤ አፋርና አሁን በቅርቡ ደግሞ ባ/ህርዳር ዉስጥ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የፈጸሙት አረመኔያዊ ጭፍጨፋ እነዚህ ሰዎች ስራቸዉ አገር መምራት ነዉ ወይስ ህዝበን እያደኑ መግደል ነዉ የሚያሰኝ ነዉ። በእርግጥም ወያኔ እስከዛሬ የገደላቸዉን ሰዎችና ሰዎቹን የገደለበትን ምክንያት ስንመለከት የወያኔ የሙሉ ግዜ ስራ አገር መምራት ሳይሆን ህዝብን ምክንያት እየፈከገ መጨፍጨፍ መሆኑን ያረጋግጥልናል። በተለይ በቅርቡ ባህርዳር ዉስጥ አለም በቃኝ ብለዉ ገዳም የገቡትን መነኩሴ በጥይት መትተዉ ማቁሰላቸዉን ስንመለከት ወያኔዎች የገነቡትን ዘረኛ ስርዐት ዕድሜ ለማራዘም ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ በግልጽ ያመለክታል።
አለማችን ዛሬም ብዙ ጨቋኝ መሪዎች የሚኖሩባት የአምባገነኖች መድረክ ናት፤ ሆኖም ህዝብ በተቃወማቸዉና በሠላማዊ ሠልፍ ቁጥዉን በገለጸ ቁጥር እንደ ወያኔ ያለ ምንም ማመንታት ሀዝብን በጥይት የሚጨፈጭፍ አረመኔያዊ አገዛዝ የለም። እዚህ ላይ አንድ ፍጹም ግራ የሚያጋባ ነገር አለ፤ እሱም ወያኔ ሠላማዊ ሰለፍኞችን በጥይት የሚጨፈጭፈዉ ሆን ብሎ ህዝብን የሚያስቆጡና የሚያነሳሱ ፀር ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎችን እየወሰደ ነዉ። ለምሳሌ ብዙዎቹን የወያኔ ጭፍጨፋዎች ትተን ሰሞኑን ባህርዳር ላይ የደረሰዉን እልቂት ብቻ ብንመለከት ህዝባዊ ቁጣዉ የተቀሰቀሰዉ ወያኔ ካልጠፋ ቦታ የቅዱስ ታቦት ማደሪያ የሆነዉን ቦታ አፍርሶ የሸቀጣ ሸቀጥ መሸጯ ቦታ ለማድረግ በመሞከሩ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሀይማኖቱ ሲነካ ወይም ሀይማኖታዊ ስርዐቱና ልምዱ ጣልቃ ሲገባባቸዉ እጅግ በጣም የሚቆጣና ተኝቶ የማያድር ህዝብ ነዉ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ህዝብ ቤ/ክርስቲያኑ አላግባብ ከፈረሰበትና ጥምቀት፤ ገና፤ ፋሲካ፤ ቡሄ፤ ቅዱስ ዮሐንስና ደመራን የመሳሰሉ ሀይማኖታዊ ስርዐቶቹንና ልምዶቹን በለመደበት ግዜና ቦታ እንዳያከብር ከተከለከለ፤ በከልካዮቹ ላይ መነሳት ብቻ ሳይሆን እነሱን ከማጥፋት የማይመለስ ህዝብ ነዉ። ዛሬ አገር ቤትም ሆነ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ አይኖቹን ወደ ባህር ዳር ያዞረዉና እኛም ዉቧ የባህርዳር ከተማ የወያኔ መጨረሻ የተጀመረባት ከተማ ናት ብለን አፋችንን ሞልተን የምንናገረዉ ይህንን ስለምንረዳ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔን ግፍና መከራ ከ23 አመታት በላይ ተሸክሞ ኖሯል። በእነዚህ ሃያ ሦስት አመታት ዉስጥ ሠላማዊ ኢትዮጵያዉያን በየመንገዱና በየአደባባዩ እንደ ዱር እንስሳ እየታደኑ ተገድለዋል። አዲስ አበባ፤ አምቦ፤ አዋሳ፤ደቡብ ኦሞ፤ አፋር፤ ጋምቤላ፤ አርሲ ገደብ አሳሳና ኮፈሌ ዉስጥ አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ባህር ዳር ዉስጥ የንጹህ ኢትዮጵያዉያን ደም በግፍ እንደ ጎርፍ ሲፈስ ተመለክተናል። ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን አስወግደን ኢትዮጵያን የህዝቦቿ አገር ካላደርግናት በቀር ወያኔ ስራዉ መግደል ነዉና እሱ እየገደለ እኛም የእያንዳንዳችን ተራ እስኪደርስ ድረስ ወያኔ የገደለዉን እየቀበርን መኖራችን የማይቀር ነዉ። የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ያለህ አማራጭ አንድ ብቻ ነዉ፤ እሱም ሁሌ እየሞትክና እየቀበርክ ከምትኖር ከወያኔ ጋር ፉት ለፊት ተጋፍጠህ እንዳባቶችህ የክብር ሞት ሙትና ለልጆችህና ለልጅ ልጆችህ ህይወት ሁንላቸዉ። አንተ በአንድነት ተነስተህ ፊትህን ወደ ወያኔ ካዞርክ ወያኔ እንደ ጉም በንኖ የሚጠፋ ገለባ ነዉ። ወያኔ እየረገጠ የሚገዛህና የሚገድልህ አንተኑ እንደ ሀይል በመጠቀም ነዉና ለወያኔ አልገዛም በል። ከሁሉም በላይ ደግሞ በዚህ በያዝነዉ የሞትና የሽረት አመት ወያኔን ለማስወገድ ከዉጭም ከዉስጥም በሚደረገዉ ትግል ዉስጥ ድርሻህን ተወጣ። ድል ምንግዜም ያንተ ነዉና . . . . አይዞህ፤ በርታ ዝመት!

Sunday, December 28, 2014

“We Shall Persevere, Ethiopia!”

ALEMAYEHU G MARIAM
“How important it is for us to recognize and celebrate our heroes and she-roes!”, decreed Maya Angelou, the great African American author, poet, dancer, actress and singer.
“I shall persevere!” wrote Eskinder Nega, the imprisoned and preeminent defender and hero of press freedom in Ethiopia, in a letter smuggled out of the infamous Meles Zenawi Prison in Kality, a few kilometers outside the Ethiopian capital Addis Ababa.
Eskinder was not merely writing about himself when he declared, “I shall persevere!”. He was also writing on behalf of his fellow imprisoned journalists, bloggers, human rights advocates and other political prisoners. After all, no prisoner of conscience, no political prisoner, can persevere alone. I would venture to say Eskinder was indeed writing about the quiet perseverance of ninety million of his fellow Ethiopians held captive in an open air prison that Ethiopia has become under the thumbs of a malignant thugtatorship called the Tigrean People’s Liberation Front (TPLF). Ethiopia shall persevere and prevail!
I want to ring out 2014 by celebrating my personal hero Eskinder Nega and she-ro Reeyot Alemu, and through them all of the other Ethiopian heroes and she-roes -- the prisoners of conscience in the war on press freedom in Ethiopia and the political prisoners held captive in defending freedom, the cause of free and fair elections, democratic governance and human rights advocates. In celebrating them, I proudly declare, “You have persevered as political prisoners! We have persevered! Ethiopia has persevered as one nation under the Almighty. We shall persevere until those who have coerced us into persevering can no longer persevere. Victory is guaranteed to those who persevere!”
Shakespeare wrote, “Some are born great, some achieve greatness, and some have greatness thrust upon ‘em.” I think the same can be said of heroes and she-roes. Citizens like Eskinder and Reeyot (symbolically representing all of the other prisoners of conscience in Ethiopia) have become heroes and she-roes because heroism was thrust upon them by extreme circumstances. When they met the defining moment of their lives, unlike most of us, they did not flinch or cringe. They did not grovel or beg. They did not offer to sell their souls for a few pieces of silver. They did not cut and run; they did not back down. They stood their ground. They chose to live free in prison than live in an open air prison under the rule of bush thugs.
Eskinder and Reeyot were offered their freedom if they got down on their knees, bowed down their heads, apologized and admitted their “crimes”, licked the boots of their captors and begged to be “pardoned”. It was the same “pardon” offered to so many others before them by the late Meles Zenawi and his disciples. It is the same “pardon” offered to Swedish journalists Johan Persson and Martin Schibbye who were sentenced to eleven years on bogus charges of “terrorism”.
A public confession of false guilt was the ultimate humiliation Meles exacted on his victims. He did it with the dozens of opposition leaders he jailed following the 2005 election. He did it twice to Birtukan Midekssa, the first woman political party leader in Ethiopian history. He had a cadre of pardon peddlers who went around prisons convincing innocent victims into admitting crimes they did not commit and beg Meles' pardon. Public humiliation of his adversaries gave Meles the ultimate high; it nurtured his sadistic soul wallowed in it. The offer of “pardon” for Eskinder and Reeyot still stands today. But they don’t want it. In turning down the "pardon" offer, they sent a clear message: “You can’t pardon an innocent man or woman... Take your pardon and shove it...!"
Christopher Reeve, Hollywood’s “Superman” who became a quadriplegic in an accident said, “A hero is an ordinary individual who finds the strength to persevere and endure in spite of overwhelming obstacles.” Eskinder, Reeyot and the others were ordinary citizens who found the strength to persevere and endure despite overwhelming obstacles. That’s why Eskinder, Reeyot and all Ethiopian political prisoners and prisoners of conscience are heroes and she-roes to me. They have all persevered and endured.
Courage is the stuff of which heroes and she-roes are made. Robert F. Kennedy once said, “moral courage is… the one essential, vital quality for those who seek to change a world that yields most painfully to change. Each time a person stands up for an idea, or acts to improve the lot of others, or strikes out against injustice, (s)he sends forth a tiny ripple of hope, and crossing each other from a million different centers of energy and daring, those ripples build a current that can sweep down the mightiest walls of oppression and resistance.”
Eskinder Nega, Reeyot Alemu and all of the other hero and she-ro political prisoners had true moral courage. They stood up for ideas of press freedom and free expression; for democracy and human rights. They stood up for the principle of the rule of law. They stood up to TPLF thugs. They persevered and in the process sent tiny ripples of hope to 90 million of their compatriots.
As we ring out 2014 and usher in 2015, I want all my readers to join me in celebrating, honoring and thanking Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye, Andualem Aragie, Bekele Gerba, Abubekar Ahmed, the "Zone Nine Bloggers” including Atnaf Berahane, Zelalem Kibret, Befeqadu Hailu, Abel Wabela, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Asmamaw Hailegeorgis, Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye. Let it be known that these heroes and she-roes are only the public faces of the tens of thousands of unnamed, unknown, unsung and unbowed heroes and she-roes of the Ethiopian struggle for equality, justice and dignity languishing in prisons ranked as among the absolute worst in the world. I salute them all as they persevere in the infamous Meles Zenawi Prison in Kality and other branch locations throughout Ethiopia.

Friday, December 26, 2014

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ይፋ አደረገ

∙በ15 ከተሞች በተመሳሳይ ሰዓት ሰልፎች ይደረጋሉ
የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ዛሬ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ አድርጓል፡፡ ትብብሩ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብሩን በህዳር ወር በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ማከናወኑ የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩ ደግሞ ለ2 ወራት የሚቆይ እንደሚሆን ተገልጹዋል፡፡
የትብብሩ አመራሮች በሰማያዊ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት በሁለተኛ ዙር የትብብሩ መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት በ15 የሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ላይ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ይደረጋሉ፤ በአዲስ አበባ፣ በሀዋሳ፣ በባህር ዳርና በአዳማ ደግሞ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደሚደረጉ የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት (ኢ/ር) በመግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡
‹‹የመግባቢያ ሰነዳችንና የጥናት ሪፖርታችንን እንዲሁም ከመጀመሪያው ዙር ያገኘውን ተሞክሮ በሠረት በማድረግ ይህን የሁለተኛ ዙር የሁለት ወር ዕቅድ (ከታህሳስ 16 እስከ የካቲት 15 /2007) አውጥቶ በቀዳሚነት ለዋነኛ ባለቤቶቹና ፈጻሚዎቹ ኢትዮጵያዊያን ሲያቀርብ እንደመጀመሪያው ዙር ከጎኑ እንደሚቆሙ ሙሉ እምነት በማሳደር ነው›› ያለው መግለጫው፣ በትብብሩ በኩል በአመራር ከፊት ቆመው ትግሉን ለመምራት ዝግጁነትና ቁርጠኝነት መኖሩን አስረድተዋል፡፡
‹‹የያዝነው የትግል መንገድ ሠላማዊና ህገ-መንግሥታዊ ብቻና ብቻ፣ መጓጓዣችን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ መድረሻችን መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ እንዲሁም በጉዞኣችን ላይ የቱንም ያህል አረመኔያዊ የኃይል እርምጃ ይወሰድብን፣ ትግሉ የቱንም ዓይነት ዋጋና መስዋዕትነት ይጠይቅ ከጅምሩ ያለመስዋዕትነት ድል የለም ብለን ተነስተናልና ከያዝነው ዓላማ ኢንች የማናፈገፍግና ለቃላችን በጽናት የምንቆም መሆኑን ዳግም እናረጋግጣለን›› ብሏል ትብብሩ በመግለጫው፡፡
እቅዱ የመጀመሪያው ዙር ቀጣይ መሆኑን ያተተው የትብብሩ መግለጫ፣ ‹‹ዓላማችን የምርጫ ሁኔታዎች ባልተሟሉበትና የመራጩ ህዝብ ነጻነት በሌለበት ስለምርጫ መናገር አስቸጋሪ ነው፣ እነዚህ በሌሉበት አማራጭ የምርጫ ኃሳቦች በህዝብ ውስጥ ሊንሸራሸሩም ሆነ አማራጭ ኃሳባችንን ከህዝብ ማድረስ አይቻልም፣ ሚናችንም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አማራጭ ሆኖ መቅረብ ሣይሆን የህወኃት/ኢህአዴግ አጃቢነትና የሀገር ሃብት በአላስፈላጊ መንገድ የማባከን ሥራ ተባባሪነት የዘለለ አይሆንም ከሚል የመነጨ ነው›› ሲል አቋሙን አሳውቋል፡፡ ነጻነት በሌለበት ተጨባጭ ሁኔታ ምርጫ ቧልት ነው ሲልም አክሏል መግለጫው፡፡
ሁለተኛ ዙር ፕሮግራም ዕቅዱ እንደባለፈው ተደጋጋፊ፣ ተመጋጋቢና ተከታታይ ሦስት ዋና ዋና ተግባራትና በሥራቸው አስራ አራት ዝርዝር ተግባራት ማካተቱም ተመልክቷል፡፡ እነዚህ በትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ጥልቅና ዝርዝር ውይይት ተደርጎባቸው የጸደቁ ዋና ዋና ተግባራትም፡-
1. የአባላትና የትብብሩ አቅም ግንባታ፡- የትብብሩን አባላት አብሮነት ማጠናከርና የጋራ ዓላማውን የማስፈጸም አቅም ማጎልበት፤
2. የህዝብ ግንኙነት ተግባራት፡- የህዝብ ተደራሽነት ማስፋትና ዓላማ ማስተዋወቅ፣
3. የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች ማመቻቸት፡- በአዲስ አበባና የተመረጡ ከተሞች አራት የአዳራሽ/አደባባይ የህዝብ ውይይት፤ በአዲስ አበባና በተመረጡ አስራ አምስት የክልል ከተሞች በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን፤ የሚያጠቃልሉ ናቸው፡፡
የትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ተግባራቱን በጊዜ ሠሌዳ በማስቀመጥ ለነዚህ ተግባራት ማስፈጸሚያ የብር 1,215, 000.00 (አንድ ሚሊየን ሁለት መቶ አስራ አምስት ሺህ ) በጀት ማጽደቁንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ትብብሩ ለያዘው ሠላማዊና ህገ-መንግሥታዊ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ትግል በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ ሌሎች ትብብሩን ያልተቀላቀሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ትብብሩን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
Source: Negere ethiopia

ወያኔ ባህርዳር ላይ የተደረገውን ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የሚቃወም የድጋፍ ሰልፍ ሊጠራ ነው

በሰልፉ የማይገኝ ቅጣት ይጠብቀዋል ተብሏል
ወያኔ በአማራ ክልል አስተዳደር ባህር ዳር ከተማ የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሆነውን የታቦት ማደሪያ ለመንገድና ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች መስሪያ እንዲነጠቅ ማዘዙን ተከትሎ በባህር ዳር ቀደም ሲል የተካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ የሚቃወም የድጋፍ ሰልፍ ሊጠራ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡
መንግስት ታህሳስ 9/2007 ዓ.ም የተደረገውን ህዝባዊ ተቃውሞ የ‹‹ፀረ ሰላም ኃይሎች እጅ እንዳለበት›› በመግለጽ ‹‹ህገ-ወጥ ሰልፍ›› ማለቱ የሚታወስ ሲሆን ባህር ዳር ከተማ የሚገኙት የቀበሌ ካድሬዎች የተደረገውን ህዝባዊ ተቃውሞ የሚቃወም የድጋፍ ሰልፍ ለማድረግ እያስተባበሩ እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ የቀበሌ ካድሬዎች በየ ቤቱ እየሄዱ የነዋሪዎችን ስም በመመዝገብ በሰልፉ የማይሳተፍ ሰው ቅጣት እንደሚጠብቀው እያስጠነቀቁ እንደሆነ ተገልጾአል፡፡ የድጋፍ ሰልፉ ታህሳስ 21 ወይንም 22 ቀን 2007 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ ይታሰባል፡፡
source. negere ethiopia

Thursday, December 25, 2014

ከታህሳስ 10 ቀን 2007 የአዲስ አበባና ባህርዳር አመጾች ምን እንማራለን?

ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. አዲስ አበባ እና ባህርዳር በዓይነታቸው ልዩ የሆኑ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን አስተናግደዋል። በአዲስ አበባ ሙስሊም ወገኖቻችን ከህወሓት ሰላዮች እይታ ውጭ በተደራጀ መንገድ በኑር መስኪድ ያደረጉት ተቃውሞ ቢያንስ ሶስት ቁም ነገሮችን አስገንዝቧል። እነዚህ ሶስት ነገሮች፣ (1ኛ) ምላሽ እስካላገኘ ድረስ የመብት ማስከበር ትግል በአፈና ተዳፍኖ እንደማይጠፋ፣ (2ኛ) ጽናት ካለ የወያኔ አፈናን የሚቋቋም ድርጅትና ተግባቦት መፍጠር እንደሚቻል፣ እና (3ኛ) ሙስሊሙን በተመለከተ የህወሓት አንድ-ለአምስት አደረጃጀት መፍረሱ ናቸው። ይህ ድል የሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ሙስሊም ያልሆኑ ኢትዮጵያዊያንም የሚጋሩት የጋራ ድል ነው። በተለይም የወያኔ አንድ-ለአምስት አደረጃጀት የሚናድ መሆኑ በተግባር ማሳየታቸው እና የህወሓት ሰላዮች ሳይሰሙ ተቃውሞዓቸውን አደራጅተው ተግባራዊ ማድረጋቸው የሚደነቅ ነው።
በዚሁ ዕለት በባህርዳር የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ከሕዝብ ጋር ሳይመክር በልማት ስም ያሻውን የሚያደርገውን እብሪተኛን ለመቃወም በአጭር ጊዜና በፍጥነት ተሰባስበው ቁጣቸው ማሰማት ችለዋል። በባህር ዳር ሕዝብ ልብ ውስጥ ለዓመታት ሲብሰለሰል የቆየውን የበደል ስሜት በዚህ አጋጣሚ ገንፍሎ ወጥቷል። በተለይም የወያኔ “ምርጥ ባርያ” መሆኑ የሚስፈነጥዘው ብአዴን በአማራ ሕዝብ ምን ያህል የተጠላና የተናቀ መሆኑ እንዲያውቅ ተደርጓል። ሆኖም ግን፣ ማናቸውንም ዓይነት ተቃውሞ የማያስተናዱት ህወሓትና ባርያው ብአዴን በባዶ እጁ ለተቃውሞ በወጣው ሕዝብ ላይ የጥይት ናዳ እንዲያወርድ ሠራዊታቸውን በማዘዛቸው እና ይህን ዘግኛኝ ትዕዛዝ የሚያስፈጽም ሠራዊት ያለ በመሆኑ ብዙ አዛውንት፣ ጎልማሶችና ወጣቶችን ለሞትና ለአካል ጉዳት ተዳርገዋል። የህወሓትና የብአዴን ሠራዊት ከዱላና ከገዳይ ጥይት ሌላ አንዳችም የአድማ መበተን እውቀት የሌለው መሆኑን የሚያሳዝን ነው፤ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ እንዲተኩስ ሲታዘዝ የሚተኩስ መሆኑም የሚያሳፍር ነው። በባህርዳር ከተፈፀመውም የኢትዮጵያ ሕዝብ (1ኛ) ሕዝባዊ አብዮት እንዲህ በደንብ ሳይታሰብበትም ሊቀሰቀስ የሚችል መሆኑ፣ (2ኛ)ህወሓት ሕዝብ አምርሮ ሲነሳበበት የሚደነግጥና የሚርበተበት ፈሪ መሆኑ፣ እና (3ኛ) በፈሪነቱ ምክንያትም በባዶ እጃቸው በወጡ አዛውንትና ህፃናት ጭምር የተኩስ እሩምታ ከመክፈት የማይመለስ መሆኑን አስተውሏል ብለን እናምናለን።
ህወሓትንና አገልጋዮቹን ከስልጣን ለማባረር በአዲስ አበባ እና ባህርዳር የተደረጉትን ማቀናጀት ግዴታ ነው። በሌላ አነጋገር የባህር ዳሩ ሕዝባዊ አመጽ አዲስ አበባ ኑር መስጊድ በታየው ዓይነት ብልሃት፣ ድርጅት እና ዲሲፕሊን ተመርቶ ቢሆን ኖሮ በባህር ዳር የተጫረው የነፃነት እሳት በመላው አገሪቷ ተቀጣጥሎ ዛሬ የምንገኝበት ሁኔታ ከታህሳስ 10 ከነበረው ፈጽሞ የተለየ በሆነ ነበር። ለወደፊቱም ማድረግ የሚኖርብን ይህ ነው። ሙስሊምና ክርስቲያኑ ተደጋግፎ አንዱ ዘንድ የጎደለው በሌላው አካክሶ የሁላችንም ጠላት የሆነውን ህወሓትን ከነ አገልጋዮቹ ከሥልጣን ማስወገድ የሁላችንም የጋራ ግዴታ ነው። ጠመንጃው የፍርሃቱ መሸሸጊያ ያደረገው ህወሓትም ጠመንጃውን የሚያስጥል መላ እና ዱላ መዘጋጀት ይኖርበታል። ህወሓትንና አጫፋሪዎቹን ከሥልጣን ለማባረር በጠንካራ ድርጅት፣ ዲሲፕሊንና ብልሃት የሚመራ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽ ቅንጅት ሊኖር እንደሚገባ የታህሳስ 10 ቀን 2007 ትልቁ ትምህርት ነው። በዚህ ዕለት የህወሓትን ወደ ጠመንጃ የመሮጥ ወራዳ ባህርይን የሚያስቆም ኃይል የማደራጀት አስፈላጊነትም ጉልህ ሆኖ ወጥቷል። ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባና ባህርዳር የተፈፀሙትን አገናኝቶ ያነበበ ማንኛውም ሰው የሁለገብ ትግል ስልት ምንነትና አዋጭነት በገሃድ ይረዳል፤ ወደዚያ እያመራን መሆኑንም ይገነዛባል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዓርብ ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. በባህርዳር ከተማ በርካታ ወገኖቻችን ሕይወታቸውን ያጡ በመሆናቸው የተሰማውን ጥልቅ ሀዘንና ቁጭትእየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል። እንደዚሁም በዚሁ ዕለት በህወሓትና ብአዴን ሠራዊቶች ጥይት ለቆሰላችሁና ለተደበደባችሁ ወገኖቻችን ሁሉ ህመማችሁ ህመማችን፤ በእናንንተ ላይ የደረሰው በደል በሁላችንም ላይ የደረሰ መሆኑን እንድትረዱልን እንፈልጋለን። እንዲህ ዓይነቱ በደል እንዲያበቃ ደግሞ ህወሓት፣ ብአዴን እና በየክልሉ ያሉት አጋፋሪዎቹ ከሥልጣን መወገድ እንዳለባቸው ያለጥርጥር እናምናለን። ህወሓት እና አጫፋሪዎቹን ከሥልጣን ለማባረር ደግሞ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ከሕዝባዊ አመጽ ጋር ማዳቀል ስለሚኖርብን በሁሉም ረገድ ዝግጅቶቻችን አጠናቀን ለወሳኙ ፍልምያ እንነሳ።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የአውሮፓ ህብረት ቀጣዩ ምርጫን (ምርጫ 2007) እዳይታዘብ ተከለከለ።

በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግስት የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ሚሽን ራሱ ባጋጠመው የበጀት እጥርት ምክንያት ምርጫውን መታዝብ አልችልም ብሎ እንደቀረ በጠ/ ሚኒስቴሩ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የተነገረው ውሸት መሆኑ ተረጋግጧል።
የችግሩ መንስኤ የ28 ለጋሽ ሃገሮች ስብስብ (Development Assistance Group) ለሰባቱ ራሳቸውን ዲሞክራሲያዊ ተቋማት ብለው ለሚጠሩት በUNDP በኩል ይሰጡ የነበረውን ከ40 ሚሊዮን ዶላር በላይ የአቅም ግንባታ ገንዘብ በማቆማቸው ምክንያት የኢትዮጵያ መንግስት ተበሳጭቶ ነው።
እርዳታው የቆመበት ምክንያት ተቋማቱ የገዢው ፓርቲ ቅኝ እጅ ሆነው ከመስራት አልፈው የሰብዓዊ መብት እንዲጣስና ዲሞክራሲያዊ አሰራር እንዲፈርስ በማድረጋቸው መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም ለጋሽ ሃገሮች የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞች ታስረው ምርጫ ማካሄድ የገንዘብ እርዳታውን ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ በማስገባቱ መሆኑ ታውቋል።
በአፋኝነትና በኢ-ዲሞክራሲያዊነታቸው እርዳታ የተከለከሉት ተቋማት እነዚህ ናቸው:-
1) የተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ)
2) የፈዴሬሽን ም/ቤት
3) የኢፌዲሪ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
4) የኢፌዲሪ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን
5) የኢፌዲሪ ፀረ ሙስና ኮሚሽን
6) የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ እና
7) ምርጫ ቦርድ ናቸው

Wednesday, December 24, 2014

የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡
hlicopterከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡
አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡
ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን ፀጋ ብርሃን ግደይ ጋር በኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር የዘወትር የልምምድ በረራ ለማድረግ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ድሬዳዋ ከሚገኘው የአየር ኃይል ቤዝ እንደተነሱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋና አብራሪው ከአጭር ጊዜ በረራ በኋላ የበረራ ከፍታውን በመቀነስ ወደ ኤርትራ በማቅናት ሔሊኮፕተሩን አሰብ ማሳረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ተዋጊ ሔሊኮፕተሩን ዋና አብራሪው ይዞ ወደ ኤርትራ መኮብለሉን አምኗል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ዋና አብራሪው ቴክኒሺያኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን አስታውቋል፡፡
ሔሊኮፕተሩ ባለፈው ዓርብ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ጀምሮ በመደበኛ የሥልጠና ልምምድ ላይ እንደነበር ጠቅሶ፣ ሔሊኮፕተሩ ከግንኙነት ውጪ በመሆኑ ሠራዊቱ በአካባቢው ማኅበረሰብና አጋሮች ለተከታታይ ቀናት ፍለጋ ሲደረግለት መቆየቱን አትቷል፡፡ ‹‹ሆኖም ሔሊኮፕተሩ በከሀዲው ዋና አብራሪ አማካይነት ቴክኒሻንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፤›› ብሏል፡፡ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች ዋና አብራሪው የሔሊኮፕተሩ አዛዥ በመሆኑ የትም ወስዶ ሊያሳርፈው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
‹‹ረዳት አብራሪው ጀማሪ ነው፡፡ የበረራ ቴክኒሺያኑ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን መከታተል ነው፡፡ ዋና አብራሪው ረዳት አብራሪውና ቴክኒሺያኑ እያወቁም ወይም ያለነሱ ዕውቅና የፈለገበት ወስዶ ሊያሳርፍ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው መክረማቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር መትረየስና ተወንጫፊ ሮኬቶች የተገጠሙለት ዘመናዊ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ነው፡፡ ከኋላው ስምንት ወታደሮችን ወይም ሁለት የቁስለኛ አልጋዎችን መያዝ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኤምአይ 17 እና ኤምአይ 8 የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ሲኖሩት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸው በደርግ ጊዜ የተገዙ ኤምአይ 24 ሔሊኮፕተሮችን ነበር፡፡ በግንቦት 1990 ዓ.ም. የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲጀመር አሥር ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተሮች የተገዙ ሲሆን፣ በጦርነቱ ወቅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡
የ1997 ዓ.ም. ሦስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ ሁለት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች (ሻምበል አብዮት እና ሻምበል በኃይሉ) አንድ ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ይዘው ወደ ጐረቤት አገር ጂቡቲ መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ ብዙም ሳይቆይ የጂቡቲ መንግሥት አብራሪዎቹን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግሥት የሰጠ ሲሆን ሔሊኮፕተሩንም መልሷል፡፡ አብራሪዎቹ የጦር ፍርድ ቤት ቀርበው በአሁኑ ወቅት በእስር እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ወቅት በቤላሩስ በሥልጠና ላይ የነበሩ ሰባት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኤስዩ 27 ተዋጊ ጀት አብራሪዎች ከድተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ አብራሪዎቹ በተለያዩ የምዕራብ አገሮች ጥገኝነት ማግኘታቸው ይነገራል፡፡
ቀደም ሲል ሻምበል ተሾመ ተንኮሉ የተባለ የአየር ኃይል ባልደረባ በ1995 ዓ.ም. ኤል 39 የተሰኘ የመለማመጃና ቀላል የውጊያ አውሮፕላን ለልምምድ በረራ ከመቀሌ ቤዝ ይዞ እንደተነሳ ወደ ኤርትራ ኮብልሎ ነበር፡፡
እስከ ማክሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት ድረስ የኤርትራ መንግሥት ስለተጠለፈው ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጠም፡፡

በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ

∙ተከሳሾቹ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል
∙‹‹ለማን አቤት ይባላል?›› ሀብታሙ አያሌው
በላይ ማናዬ
ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተሟልተው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል፡፡
ችሎቱ የተሰየመው ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ወቅት ተከሳሾች በቀረበባቸው የሽብር ክስ ላይ የሰጡትን መልስ በተመለከተ 7ኛ ተከሳሽ መልስ በዕለቱ ባለማቅረባቸው አሟልተው እንዲቀርቡ ነበር፡፡ በተጨማሪም ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ስለነበር ይህን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ በታዘዘው መሰረት ማብራሪያውን ለመስማት ነበር፡፡
የተከሳሾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በጥየቃ ወቅት በተለየ መዝገብ ይመዘገባሉ የተባለውን አቤቱታ በተመለከተ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በደብዳቤ መልስ መስጠቱ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ‹‹ማረሚያ ቤቱ በሰጠው መልስ እስረኞች ከሌሎች በተለየ የደረሰባቸው ችግር የለም›› ማለቱን ገልጾ ይህንኑ መልስ ሙሉ ለሙሉ መቀበሉን አስታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በዛሬው የችሎቱ ውሎ ላይ ተከሳሾች ለየት ያለ አቤቱታ በጠበቆቻቸው በኩል አቅርበዋል፡፡ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለችሎቱ እንዳስረዱት ደንበኞቻቸው ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ አቶ ተማም አባቡልጉ በታህሳስ 12 ለ13 ቀን 2007 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት ስምንት ሰዓት ጀምሮ ደንበኞቻቸው ላይ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የግል ማስታወሻዎቻቸው፣ ገንዘብ እና በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ እያዘጋጁት የነበረው መቃወሚያና መከራከሪያ ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡
‹‹ደንበኞቼ ላይ እየተደረገ ያለው ጉዳይ ለህይወታቸውም የሚያሰጋቸው ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ በሌሊት ፍተሻ ያደረጉባቸው ሰዎች ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ‹ህገ-ወጥ› ተግባራት ሲፈጽሙባቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስና የደህንነት አባላት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ደንበኞቼ ያውቋቸዋል፡፡ ስለሆነም ፍተሻው የተከናወነው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አልነበረም ማለት ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው የተለየ የስም ዝርዝር ተይዞ ከሌሎች በተለየ መልኩ ነው፡፡ ለአብነት ደንበኞቼ አቶ አብርሃ ደስታና በሌላ የክስ መዝገብ የተከሰሰው አብዱራዛቅ አክመድ ላይ የሆነው ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ነው፡፡ ፍተሻው ስለት ነገር አልያም ሌላ ህገ-ወጥ ቁሳቁስ ለመያዝ የተደረገ አለመሆኑን ከተወሰዱት ንብረቶች ማየት ይቻላል›› ሲሉ አቶ ተማም ለፍርድ ቤቱ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመውን ድርጊት አስረድተዋል፡፡
ይህን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ ‹‹ማረሚያ ቤቱ መንግስት ዜጎች ታንጸው እንዲወጡ ያሰራው ነው፡፡ ይህን አሰራር ለመጠበቅም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የተለያዩ ስራዎችን ሊሰራ ይችላል፡፡ እየቀረበ ያለው አቤቱታም ከዚህ አኳያ መታየት ያለበት ነው›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ከህግ አንጻር ያስረዱ ሲሆን፣ ‹‹በመሰረቱ ፍተሻ ሊካሄድ መቻሉ ላይ አይደለም አቤቱታው፡፡ የተካሄደው ፍተሻ ግን ህገ-ወጥ ነው፤ ምክንያቱም ፍተሻው የተከናወነበት ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ባለው ጊዜ ሳይሆን ሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ፍተሻው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አይደለም የተከናወነው፡፡ በደህንነቶችና የፌደራል ፖሊሶች ነው ፍተሻው የተደረገው፡፡ ይህም ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎቱም ሆነ ብቃቱ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ ይህን መሰል ድርጊት የፈጸሙት አካላትና በማን ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ምርመራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም በተጨማሪ ከደንበኞቻቸው ላይ በፍተሻው ወቅት የተወሰዱባቸው ንብረቶችና ማስታወሻዎች እንዲመለሱላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ‹‹የተለየ ከፍተኛ በደል ደርሶብኛል›› በሚል ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ዕድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው የነበሩት 3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ የጠየቁት የመናገር እድል ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡
በጠበቆቹ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታን በተመለከተ ችሎቱ አስተያየት የሰጠ ሲሆን በተለይ ጠበቃ ተማም አቤቱታውን ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎትም ብቃትም የለውም›› ያሉት አገላለጽ ተገቢ ስላልሆነ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በቃል የገለጹት የመሐል ዳኛው፣ ‹‹እንዲህ አይነት አገላለጽ ማረሚያ ቤቱ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ እንዳይሆን…›› በማለት ሌላ አስገራሚ መነጋገሪያ ከፍተዋል፡፡
ይህን የዳኛውን ንግግር ተከትሎ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የመናገር እድል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ ለአጭር ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ እናም፣ ‹‹እርስዎ እያሉት ያለው ነገር ተገቢ አይደለም፡፡ በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይህንን ስጋቴን ለችሎት እያስረዳሁ ነው፡፡ ግን እርስዎ ‹የበቀል እርምጃ› እንዲወሰድብን ማሳሰቢያ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ በእርግጥ አሁንም የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድብን ማረጋገጫ የለንም፡፡ እሺ ለማን አቤት ይባላል? የደረሰብንን በደል ለፍርድ ቤት ከማስረዳት ውጭ ለማን አቤት እንላለን….አሁን እኮ ፍርድ ቤቱ ከማረሚያ ቤቱ ጋር መወገኑን ነው እያየን ያለነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የእኛን አቤቱታ እየሰማ አይደለም፡፡ ከፍርድ ቤት ውጭ ለማን አቤት እንበል?›› ሲል አቤቱታውን በስሜት ውስጥ ሆኖ አስረድቷል፡፡
የሀብታሙን ንግግር አዳምጠው አንደኛ ዳኛ ‹‹እኛ ሳንሆን ህጉ ነው ይህን እንድንል የሚያደርገን›› በማለት አጭር መልስ ሰጥተዋል፡፡
በዚህ መልኩ ቀጥሎ የዋለው ችሎት በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የማየት ስልጣን አለው ወይስ የለውም በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት፣ እና መደበኛ ክሱን ለማየት ለታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተጥቷል፡፡

ዳኛው ጠበቃ ተማምን አስጠነቀቁ



እነ ሀብታሙ አያለው ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የዛሬ ቀጠሯቸው መቃወሚያ ለማቅረብ የነበረ ቢሆንም ታህሳስ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በደረሰባቸው ድርጊት ፍርድ ቤቱ ሌላ ቀጠሮ ለመስጠት ተገዷል፡፡ በለቱ ሌሊት 8፡00 ላይ የእስር ቤቱ የስራ ባልደረባ ያልሆኑ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ለዛሬው ቀጧሯቸው የሚሆን የመቃወሚያና የመከራከሪያ ሰነዶቻቸውን ወስደውባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ገንዘባቸው እንደተወሰደባቸው ጠበቃቸው ተማም አባቡልጉ ተናግረዋል፡፡
ጠበቃው በገለጹት መሰረት “የተካሄደው ብርበራ ሳይሆን ዝርፊያ ነው” ያሉ ሲሆን “እስር ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ብቃት የለውም” በማለታቸው የለቱ ዳኛ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡ 
አስተያየት ሰጪዎች እንደተናገሩት ከሆነ ስርዓቱ ይህን የወንበዴ ድርጊት ለመፈፀም የተገደደው አንዲት ጠብ የምትል መረጃ ባለማቅረቡ በዛሬው ቀጠሮ በደንብ እንዳይከራከሩ ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቶታ ስጋት እንዳላቸው ገልፀው “አቤቶታችንን ለዚህ ፍርድ ቤት በማቅረባችን በቀል እርምጃ ይወሰድብናል፣ ደህንነት ስሜት አይሰማንም” ብሏል፡፡ ፍርድ ቤቱም እስር ቤቱ ታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም መልስ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ሰጥል፡፡
እነ ሀብታሙ አያሌው፣ አብረሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሽበሽ፣ የሺዋስ አሰፋ ከሀምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ቤት እየተሰቃዩ ነው፡፡

የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ ; አስመራ የገቡት ፓይለቶች ከቤተ መንግስቱ ወደ ሆቴል ተዘዋወሩ

‪- የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ
– መጭውን ውህደት የሚያሳፈጽሙ የአርበኞች ግንባር አባላት ከአውሮፓ እና አውስትራሊያ ተወከሉ

hlicopter
ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው:- አርብ እለት ከድሬዳዋ ተነስተው በደቡባዊ ኤርትራ አሰብ ዘልቀው የገቡት የወያኔው አየር ሃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሺያኖች በደህና ሁኔታ ውስጥ ሲገኙ በኤርትራ የአየር ክልል የተቀበላቸው እና በ1987 አመተምህረት በወያኔ እና የደርግ መኮንኖች የሰለጠነው የሻእቢያ ኮማንዶ ጦር አጅቧቸው ወደ አስመራ ቤተመንግስት ከገቡ በኋላ በቤተ መንግስቱ ውስጥ ለሁለት ቀን በእንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ ቆይተው ወደ ሆቴል መዘዋወራቸውን ከአስመራ የተገኙ ምንጮች ጠቁመዋል::
በቤተ መንግስት ቆይታቸው አስፈላጊ ጥያቄዎች እና ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከደምህት ጦር ጋር በመቀላቀል እየተገነባ ባለው ዘመናዊ አየር ሃይል ውስጥ አገልግሎት እንዲሰጡ የተጠየቁ መሆኑን ምንጮቹ ሲናገሩ አብራሪዎቹ ግን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ፍላጎቱ እንዳላቸው እና አውሮፓ ሆነው ትግሉን መርዳት እንደሚችሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል::አብራሪዎቹ እጃቸውን የሰጡትም ሆነ የተቀላቀሉት ከኤርትራ መንግስት ጋር እንጂ ከሌላ አካል ጋር እንዳልሆነ ምንጮቹ አረጋግጠዋል::
ከደብረዘይት አየር ሃይል አከባቢ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በድሬዳዋ ያለው የአየር ሃይል ካምፕ ሃላፊዎች ላይ ከፍተኛ ግምገማ ተደርጓል::በዚህም መሰረት የሃገሪት የአየር ክልል ሳይቀር ከራዳር ውጪ ነው የሚል ጉዳይ ተነስቶ መነጋገሪያ እና መገማገሚያ ሆንዋል::እርስ በርስ መወነጃጀል እንኳን ባልተደፈረበት ግምገማ ላይ እያንዳንዱ መኮንን ሃላፊነቱን ወስዶ ዋጋ ሊከፊል ዪገባዋል ሲሉ ከፍተኛ አዛዦች በቁጣ ተናግረዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ በመጪዎቹ ሳምንት በሚካሄደው የግንቦት ሰባት እና የአርበኞች ግንባር ውህደት ላይ እስካሁን ወኪል ያላከው የአርበኞች ግንባር አንድ ሰው ከአውሮፓ አንድ ሰው ከአውስትራሊያ በመምረጥ ለእህደት ስብሰባው ማስትላለፉን ምንጮቹ ተናግረዋል::የተመረጡት አስመራ እንደደረሱ በውህደቱ ዙሪያ ንግግር እንደሚጀመር እና የፊርማው ውህደት እንደሚጸድቅ ኮሎኔል ፍጹምን ዋቢ ያደረጉ ምንጮች ጠቁመዋል::
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

Tuesday, December 23, 2014


Hijacked Ethiopian attack helicopter landed in Eritrea

ESAT News
The Ethiopian Defense Force has admitted that Ethiopian Air Force pilots have defected to Eritrea flying a helicopter while ESAT’s Air Force sources have said that the Ethiopian Air Force had lately stopped the search for the two pilots and a technician, who disappeared since Friday. The Ethiopian Defense said in a statement that was read on Ethiopian state television that the “traitor” pilot of the helicopter forced the assistant and the technician to fly to Eritrea.
ESAT learned that the search for the defecting pilots stopped after the Air Force confirmed that the pilots had intended to defect and had safely landed in an “unspecified place”.
ESAT broke the News on Saturday that the defecting pilots were two however; new reports from the Ethiopian Air Force indicate that the missing crew were three namely Captain Samuel Ghidey, Lieutenant Bililign Mekonen and technician Tesagbirhan Gidey.
ESAT’s efforts to speak to Brigadier Mashu Hagos, Deputy Head of the Ethiopian Air Force were unsuccessful; however, ESAT attempted to speak with Colonel Abebe Teka, who is believed to be the shadow leader of the Air Force and Deployments. When informed that we were calling him from ESAT, Colonel Abebe asked “did they (the defecting pilots) phone you?” ESAT’s journalist tried to explain that we were calling him after receiving information about their defection, the Colonel shouted “shut up” and hanged the phone up.
ESAT will continue updating about the ongoing issue.

World’s worst jailers – Ethiopia ranked the 4th – CPJ

More than 200 journalists are imprisoned for their work for the third consecutive year, reflecting a global surge in authoritarianism. China is the world’s worst jailer of journalists in 2014. A CPJ special report by Shazdeh Omari
The Committee to Protect Journalists identified 220 journalists in jail around the world in 2014, an increase of nine from 2013. The tally marks the second-highest number of journalists in jail since CPJ began taking an annual census of imprisoned journalists in 1990, and highlights a resurgence of authoritarian governments in countries such as China, Ethiopia, Burma, and Egypt.
China’s use of anti-state charges and Iran’s revolving door policy in imprisoning reporters, bloggers, editors, and photographers earned the two countries the dubious distinction of being the world’s worst and second worst jailers of journalists, respectively. Together, China and Iran are holding a third of journalists jailed globally—despite speculation that new leaders who took the reins in each country in 2013 might implement liberal reforms.
The 44 journalists in Chinese jails are a jump from 32 the previous year, and reflect the pressure that President Xi Jinping has exerted on media, lawyers, dissidents, and academics to toe the government line. In addition to jailing journalists, Beijing has issued restrictive new rules about what can be covered and denied visas to international journalists. Coverage of ethnic minority issues continues to be sensitive; almost half of those jailed are Tibetan or Uighur, including academic and blogger Ilham Tohti and seven students imprisoned for working on his website, Uighurbiz. Twenty-nine of the journalists behind bars in China were held on anti-state charges. (Read detailed accounts of each imprisoned journalist here.)
The administration of Iranian President Hassan Rouhani has also maintained repressive measures against the press. This year, Iranian authorities were holding 30 journalists in jail, down from 35 in 2013 and a record high of 45 in 2012. CPJ’s 2014 International Press Freedom Award winner Siamak Ghaderi was released from prison in July, but that same month, Iranian authorities jailed Jason Rezaian, a Washington Post reporter. By late 2014, the government had still not disclosed the reason for Rezaian’s arrest or the nature of charges against him.
The list of the top 10 worst jailers of journalists was rounded out by Eritrea, Ethiopia, Vietnam, Syria, Egypt, Burma, Azerbaijan, and Turkey. The prison census accounts only for journalists in government custody and does not include those in the captivity of nonstate groups. For example, CPJ estimates that approximately 20 journalists are missing in Syria, many of whom are believed held by the militant group Islamic State.
Turkey, which was the world’s worst jailer in 2012 and 2013, released dozens of journalists this year, bringing to seven the number of journalists behind bars on the date of CPJ’s census. However, on December 14, Turkey detained several more journalists—along with television producers, scriptwriters, and police officers—and accused them of conspiring against the Turkish state, according to news reports. The detentions were born of a political struggle between President Recep Tayyip Erdoğan and the ruling party and the movement led by U.S.-based cleric Fethullah Gülen, and included the editor-in-chief of one of Turkey’s largest dailies, Zaman, which is aligned with Gülen.
In Eritrea, which has consistently ranked among the world’s worst jailers and is ranked third this year, authorities are holding 23 journalists, all without charge, and have refused to disclose the prisoners’ health or whereabouts. In 2014, CPJ conducted a fresh investigation into the status of long-held prisoners in the extremely repressive country; the probe led to the addition or removal of a handful of cases but yielded little information about many of those long jailed.
A state crackdown on independent publications and bloggers in Ethiopia this year more than doubled the number of journalists imprisoned to 17 from seven the previous year, and prompted several journalists to flee into exile, according to CPJ research.
For the first time since 2011, Burma had journalists in jail on the date of CPJ’s census: at least 10 were imprisoned, all on anti-state charges. In July, five staff members of the Unity weekly news journal were sentenced to 10 years in prison each under the 1923 Official Secrets Act. Rather than reforming draconian and outdated security laws, President Thein Sein’s government is using the laws to imprison journalists.
In Azerbaijan, authorities were jailing nine journalists, up one from the previous year. Amid a crackdown on traditional media, some activists took to social networking sites in an attempt to give the public an alternative to state media. CPJ’s list does not include at least four activists imprisoned in Azerbaijan this year for creating and managing Facebook groups on which they and others posted a mix of commentary and news articles about human rights abuses and allegations of widespread corruption.
Egypt more than doubled its number of journalists behind bars to at least 12, including three journalists from the international network Al-Jazeera.
In recent years, journalist jailings in the Americas have become increasingly rare, with one documented in each 2012 and 2013. This year, the region has two: a Cuban blogger was sentenced to five years in prison in retaliation for his critical blog, and in Mexico, an independent journalist and activist for Mayan causes has been charged with sedition.
Other trends and details that emerged in CPJ’s research include:
The 220 journalists jailed around the world compares with the 211 CPJ documented behind bars in 2013. The 2014 tally ranks the second highest behind 2012, when CPJ documented 232 journalists jailed in relation to their work.
Worldwide, 132 journalists, or 60 percent, were jailed on anti-state charges such as subversion or terrorism­. That is far higher than any other type of charge, such as defamation or insult, but roughly in line with the proportion of anti-state charges in previous years.
Twenty percent, or 45, of the journalists imprisoned globally were being held with no charge disclosed.
Online journalists accounted for more than half, or 119, of the imprisoned journalists. Eighty-three worked in print, 15 in radio, and 14 in television.
Roughly one-third, or 67, of the journalists in jail around the world were freelancers, around the same proportion as in 2013.
The number of prisoners rose in Eritrea, Ethiopia, China, Bangladesh, Thailand, Azerbaijan, Bahrain, Egypt, Israel and the Occupied Palestinian Territories, and Saudi Arabia.
Countries that appeared on the 2014 prison census after jailing no journalists in the 2013 survey were Cameroon, Swaziland, Mexico, Cuba, Burma, and Belarus.
CPJ defines journalists as people who cover the news or comment on public affairs in media, including print, photographs, radio, television, and online. In its annual prison census, CPJ includes only those journalists who it has confirmed have been imprisoned in relation to their work.
CPJ believes that journalists should not be imprisoned for doing their jobs. The organization has sent letters expressing its serious concerns to each country that has imprisoned a journalist. In the past year, CPJ advocacy led to the early release of at least 41 imprisoned journalists worldwide.
CPJ’s list is a snapshot of those incarcerated at 12:01 a.m. on December 1, 2014. It does not include the many journalists imprisoned and released throughout the year; accounts of those cases can be found at www.cpj.org. Journalists remain on CPJ’s list until the organization determines with reasonable certainty that they have been released or have died in custody.
Journalists who either disappear or are abducted by nonstate entities such as criminal gangs or militant groups are not included on the prison census. Their cases are classified as “missing” or “abducted.”
Source: CPJ

ፍርድ ቤቱ የሰማያዊ አባልን የክስ መከላከያ ውድቅ አደረገ



ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ተዘጋጅቶ ለነበረው የአዳር ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቅስቀሳ በራሪ ወረቅት ሲበትን ለእስር የተዳረገው የሰማያዊ ፓርቲ አባል በፌደራል አቃቤ ህግ ለቀረበበት ክስ ያቀረበው መቃወሚያ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደረገ፡፡
ዛሬ ታህሳስ 14/2007 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መናገሻ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት የቀረበው አቶ ሲሳይ ዘርፉ ‹‹…‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ› ለመላው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ሁሉ….ተብሎ የተጻፈበት በራሪ ወረቀቶች ለህብረተሰቡ ሲያከፋፍል እጅ ከፈንጅ በመያዙ በፈጸመው የሐሰት ወሬን በማውራት ህዝቡን ማነሳሳት ወንጀል…›› በፌደራል አቃቤ ህግ መከሰሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህን ክስ ለመቃወም ያቀረበው የጽሑፍ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ውድቅ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም አቃቤ ህግ በተከሳሽ ላይ ምስክሮቹን አቅርቦ ለታህሳስ 23 ቀን 2007 ዓ.ም እንዲያሰማ ተፈቅዶለታል፡፡
ተከሳሹ አቶ ሲሳይ ዘርፉ ለቀረበበት ክስ በጽሑፍ መከላከያው ላይ፣ ‹‹…መረጃ ማሰራጨት ህገ-መንግስታዊ መብቴ ነው፤ ያሰራጨሁት መረጃም የሐሰት ወሬ ሳይሆን በህግ ተመዝግበው ሰላማዊ ትግል እያደረጉ ያሉ ፓርቲዎች ያዘጋጁትን መረጃ ነው…›› በማለት አስፍሮ በነጻ እንዲያሰናብተው ፍርድ ቤቱን ጠይቆ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ ‹‹የመንግስትን ስም ማጥፋት በወንጀል ያስጠይቃል...›› በሚል ከአቃቤ ህግ የቀረበለትን ሀሳብ ተቀብሎ ተከሳሹ አቶ ሲሳይ ላይ ምስክሮች እንዲሰሙበት በይኗል፡፡
አቶ ሲሳይ ዘርፉ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለበት ዕለት ጀምሮ ዋስትናው ተነፍጎ ቀደም ብሎ በፖሊስ ጣቢያና አሁን ደግሞ ቂሊንጦ እስር ቤት በእስር ላይ ይገኛል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ሰማያዊ ፓርቲ በአቶ ሲሳይ ዘርፉ የዋስትና ጉዳይ ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቅ አስታውቋል፡፡
Source: Negere ethiopia

ሞትን ሸሽቶ ተራ ሞት ከመሞት ከገዳዮች ጋር ተፋልሞ በክብር መሞት የኢትዮጵያዊነት ምልክት ነዉ

ወጣቱ ትዉልድ በየትኛዉም አገር ወይም ህብረተሰብ ዉስጥ በአገር ልማት’፤ በመሰረታዊ ተቋሞች ግንባታና አገርን በመከላከል ስራዎች ላይ የተሸከመዉ ኃላፊነት ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የበለጠ ነዉ። እንደ ኢትዮጵያ አይነት ዘረኛ አምባገነኖች በነገሱበት አገር ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት አገራዊ አደራና ሀላፊነቶች በተጨማሪ ወጣቱ ትዉልድ እራሱንና ወገኖቹን ከዘረተኝነትና ከአምባገነንነት አላቅቆ በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት የመገነባት ተጨማሪ ሀላፊነት አለበት። ወጣቱ ትዉልድ የኢትዮጵያን አገራዊ ራዕይ የተሸከመ ደከመኝን የማያዉቅ ተከታታይነት ያለዉ የማይነጥፍ የህይወት ምንጭ ነዉ። በእርግጥም ወጣትነት የህይወት ህልምና ፊቺዉ አብረዉ የሚገለጹበት የእድሜ ክልል ነዉ። ወጣቱ ደግሞ ራዕይ ተሸካሚ ብቻ ሳይሆን የተሸከመዉን ራዕይ እዉን ሆኖ ለማየትና ለማሳየት ብቃቱ፤ ችሎታዉና ፍላጎቱ ያለዉ መበአካሉም በመንፈሱን ጠንካራ የሆነ የህብረተሰብ ክፍል ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያ በአለም ታሪክ ዉስጥ እንደ አገር ተመዝግባ በኖረችባቸዉ ረጂም አመታት ዉስጥ የየዘመኑ ወጣት ለእናት አገሩ ሠላም፤ ብልጽግናና የግዛት አንድነት መከበር ይህ ነዉ ተብሎ በቃላት ሊነገር የማይችል ትልቅ መስዋዕትነት ከፍሏል ዛሬም እየከፈለ ነዉ። ትናንት በአባቶቻችን ዘመን የአገራቸዉን ዳር ድንበር በጠላት አናስደፍርም ብለዉ ጫካዉንና ዱሩን ቤታቸዉ ያደረጉ በላይ ዘለቀን፤ አብዲሳ አጋንና ጃገማ ኬሎን የመሳሰሉ ወጣቶች ነበሩን። በ1970ዎቹ ደግሞ ሰዉ በላዉን የደርግ ስርዐት ፊት ለፊት ተጋፍጠዉ ለእናት አገራቸዉ ኢትዮጵያ የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ነበሩ። ዛሬም ዘረኛዉን የወያኔ ስርዐት ለማስወገድና አገራቸዉ ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር ለማድረግ በየቀኑ የአካልና የሕይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉ ኢትዮጵያዉያን ወጣቶች ቁጥር በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ለምሳሌ በ1997 ዓም የህዝብ ድምጽ ይከበር ብለዉ በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ያቀረቡ ከሁለት መቶ በላይ ወጣቶች የጦር ሜዳ መሳሪያ ከታጠቁ አግዓዚ ነብሰ ገዳዮች ጋር ባዶ እጃቸዉን ተጋፍጠዉ በክብር ተሰዉተዋል።
ከላይ ከፍ ሲል አጽንኦት ሰጠተን እንደገለጽነዉ ወጣቱ ትዉልድ የህብረተሰብ አንቀሳቃሽ ሞተር ነዉ። ሀኖም ሞተር ከራሱ ዉጭ ሌሎችን ማንቀሳቀስ የሚችለዉ መጀመሪያ እሱ እራሱ መንቀሳቀስ ሲችል ነዉ። የኢትዮጵያም ሆነ የማንኛዉም አገር ወጣት ሞተር ሆኖ የሚኖርበትን ህብረተሰብ ማንቀሳቀስ እንዲችል ከፍተኛ የመንግስትና የሁሉም ህብረተሰብ ያላሰለሰ ድጋፍ ያስፈልገዋል። ከሁሉም በላይ ደግሞ ወጣቱ በነጻነት መንቀሳቀስ የሚችልበት የፖለቲካ፤የማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ድባብ ያስፈልገዋል። እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም የሚያሳዝነንና የሚያሳስበን ጉዳይ አለ፤ እሱም የኢትዮጵያ ወጣት የእድገት ሞተር ሆኖ አገሩን የሚያንቀሳቅስበት ቀርቶ እሱ እራሱም የነጻነት አየር የተነፈሰበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። በተለይ በወያኔ ስርዐት ዉስጥ ከልጅነት ወደ ወጣትነት የተሸጋገረዉ ኢትዮጵያዊ ሁሉ አገር፤ አንድነትና ኢትዮጵያዊነት ከሚባሉ ትልላቅ ብሄራዊ እሴቶች ጋር እንዳይተዋወቅ ተደርጎ ያደገ ወጣት ነዉ።
የዛሬዉ ዘመን ኢትዮጵያዊ ወጣት በጻፈ ቁጥር የሚደበደብ፤ ባነበበ ቁጥር የሚጋዝ፤ ተናግሮ ሀሳቡን በገለጸ ቁጥር ደግሞ ከየመንገዱ እየተለቀመ የት እንደደረሰ እንኳን ሳይታወቅ ደብዛዉ የሚጠፋ ቀን የጨለመበት ወጣት ነዉ። ባጠቃላይ ወያኔ ስልጣን ይዞ በቆየባቸዉ ባለፉት ሃያ ሦስት አመታት ዉስጥ የኢትዮጵያ ወጣት የአባቶቹን ታሪክ እንዳያዉቅና ከዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ሳይተዋወቅ ድቅድቅ ጨለማ ዉስጥ እንዲኖር ተደርጓል። የኢትዮጵያ ወጣት ከመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ተዋዉቆ እራሱን ካደራጀና ከጓደኞቹ ጋር ባሰኘዉ ግዜ ሁሉ ከተገናኘ በአገሩ የፖለተካና ማህበራዊ መድረኮች ላይ የሚጫወተዉን ሚና ወያኔ ስለሚረዳ የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ከወሰዳቸዉ እርምጃዎች አንዱና ዋነኛዉ ወጣቱ ህብረተሰብ ከመረጃ ቴክኖሎጂ ጋር ያለዉን የቅርብ ግኑኝነት መስበር ነዉ። ይህ ፀረ አገርና ፀረ ዕድገት እርምጃ ደግሞ ወጣቱን ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ አገራችን ኢትዮጵያ በመረጃ ቴክኖሎጂ ዕድገትና ስርጭት የአለማችን የመጨረሻዋ ጭራ አገር እንድትሆን አድርጓታል። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያን ወጣት አማራጭ አሳጥቶ ከዚህ ቀደም ታይቶም ተሰምቶም በማያዉቅ ፍጥነትና ብዛት አገሩን እየጣለ እንዲሰደድ አድርጎታል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎችም አለም አቀፍና አህጉራዊ ድርጅቶች ያደረጉት ጥናት በግልጽ እንደሚያመለክተዉ ምሁሩና ወጣቱ ትዉልድ በከፍተኛ ቁጥር ከሚሰደድባቸዉ አገሮች ዉስጥ ኢትዮጵያ በዓለዉ ዉስጥ ቀዳሚዉን ቦታ የያዘች አገር ናት። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን አኮኖሚ የአፍሪካ የዕድገት ምልክት አድርገነዋል እያሉ ቢፏልሉም ይህ አሳደግነዉ የሚሉት ኤኮኖሚ ስራ አልባ ኤኮኖሚ በመሆኑ የራሱን አገር መገንባት የነበረበት ኢትዮጵያዊ ወጣት ወንድ ሴት ሳይል እጅግ በጣም በሚያስፈራ ፍጥነት አገሩን እየለቀቀ በመዉጣት ላይ ነዉ።
ዛሬ በዘለም ዙሪያ ከደቡብ ኮሪያ እስከ አዉስትራሊያ፤ ከሳዑዲ አረቢያ እስከ ካናዳ በየአህጉሩ፤ በየአገሩና በየደሴቱ ላይ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች የሌሉበት አገር የለም። በ1970ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ የደርግን ጭፍጨፋ እየሸሸ ከአገሩ መሰደድ የጀመረዉ ኢትዮጵያዊ ወጣት ዛሬም ከ37 አመታት በኋላ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ የለየለት ነብሰ ገዳይ አገፈዛዝ በመሆኑ የኢትዮጵያ ወጣት አሁንም አገሩን እየለቀቀ በመዉጣት ላይ ነዉ። የስደት ጉዞ ብርድና ቁር፤ ሀሩርና ንዳድ፤ እንዲሁም ህመም፤ ቁስልና ሞት የተቀላቀሉት ለወገንም ለባዳም የማይመኙት እጅግ በጣም አደገኛ ጉዞ ነዉ። ስደት ጉዞዉ ብቻ ሳይሆን ስደተኞች በስደት የሚኖሩበት አገርም ቢሆን ለአካልም ለመንፈስም የማይመች ቦታ ነዉ። ሴቶች እህቶቸቻችን በየቀኑ ወደ አረብ አገር የሚጎርፉት አካለቸዉ ላይ የፈላ ዉኃ እንደሚደፋ፤ ከፎቅ ላይ እንደሚወረወሩና በአረብ ጎረምሳ በየቀኑ እንደሚደፈሩ እያወቁ ነዉ ከወያኔ ጋር ከመኖር ስደት ይሻላል ብለዉ አገራቸዉን ለቅቀዉ የሚሰደዱት። ወንዶች ወንድሞፐቻችንም ቢሆኑ የሰሃራን በረሃና የቀይ ባህርን የመከራ ጉዞ ቆርጠዉ የሚገበቡበት ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ ብለዉ ነዉ እንጂ በየበረሃዉና በየባህሩ ላይ እንደወጣ የቀረዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር እጅግ በጣም ብዙ እንደሆነ ሳያዉቁት ቀርተዉ አይለደም። ለመሆኑ ኢትዮጵያዉያን ይህንነ ሁሉ ቸግርና ጣጣ እያወቁ ወነድ፤ሴት፤ ወጣት አዛዉንት፤ ሳራተኛና ገበሬ ሳይል ሁሉም በጅምላ እትብታቸዉ የተቀበረበትን አገር እየለቀቁ የሚሰደዱት ለምንድነዉ?
ኢትዮጵያዉያን የሚሰደዱት ወያኔን እየጠሉ ነዉ ወይም የወየኔ ዘረኝነት፤ ከፋትና ጥላቻ እንገፍግፏቸዉ ነዉ ብለዉ የሚገምቱ ብዙ ኢትዮጵያዉያን ሰዎች ሊኖሩ ይቻላል። በጥቅሉ ሲታይ ግምታቸዉ ትክክለኛ ግምት ነዉ፤ የወያኔ ዘረኝነትና ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ብዙ ኢትዮጵዉያንን አንገፍግፏል፤ አበሳጭቷል ወይም አስቆጥቷል። ሆኖም ሰዎች ስለተቆጡና ስለተንገፈገፉ ብቻ እንደ ምፅአት አገራቸዉን እየለቀቁ አይወጡም። ኢትዮጵያዉያን አገራቸዉን እየለቀቁ የሚወጡት ከወያኔ እስር፤ ድብደባና ግድያ ለማምለጥ ነዉ ብለን መገመትም እንችላለን። ትክክለለኛ ግምት ነዉ። ግን ስንቱ ኢትዮጵያዊ ነዉ ኬንያ፤ ማላዊ፤ ሞዛምቢክ፤ ግብፅ’ የመንና ሊቢያ ድረስ ሲንከራተት በየመንገዱ እየሞተ ለቀብር እንኳን የማይበቃዉ? ደግሞም የሰዉ ልጅ ባህሪይ የሚያሳድደዉንና የሚገድለዉን እየገደለ መሞት ነዉ እንጂ ሞትን እየሸሰ ጣረ ሞት ዉስጥ መግባት አይደለም። እዉነቱን ለመናገር የኢትዮጵያ ወጣት አገሩን በገፍ እየለቀቀ የሚሰደደዉ የወያኔ ዘረኞች ተስፋዉን ስለገደሉበትና የወደፊቱን ስላጨለሙበት ነዉ።
ተስፋ የሰዉ ልጆች የመኖር ዋስትና ነዉ። እኛ ሰዎች እየከፋንም ቢሆን ደስ እንዳለዉ ሰዉ የምንኖረዉ ይኖረናል፤ ይመቸናል ወይም ክፉዉ ቀን አልፎ መልካም ቀን ይመጣል በሚል ተስፋ ነዉ።ተስፋ የሞተ ቀን ለምን እንደምንኖር ስለማናዉቅ አገር ጥለን መሰደድ ብቻ ሳይሆን ከዚህም የከፋ ብዙ ነገር ማድረግ እንችላለን። ወያኔ ስልጣን ይዞ የቆየባቸዉን ያለፉት ሓያ ሦስት አመታትን ትተን ከ2000 እስከ 2007 ያሉትን ሰባት አመታት ብቻ ስንመለከት ማላዊ ሀይቅ ወስጥ፤ ሰሃራ በረሃ ዉስጥ፤ ኤደን ባህረ ሰላጠና ባቢኤል መንደብ ዉስጥ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ኢትዮጵያዊ የአዉሬ ስራት ሆኖ ቀርቷል። ነፃነትና የተሻለ ኑሮ እናገኛለን ብለዉ በኮንቴነር ተጭነዉ ወደ ደቡብ አፍሪካ ይጓዙ የኘበሩ ከ50 በላይ ኢትዮጵያዉያን በእግራቸዉ እየተራመዱ ከገቡበት ኮነቴነር እሬሳቸዉ እየተጎተተ ወጥቷል።
ስደትንና እየተሰደደ ደብዛዉ የሚጠፋዉን ኢትዮጵያዊ በተመለከተ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ ለጆሮ የሚከብዱ ዜናዎችን ሰምቷል። ባፈዉ ህዳር ወር ማለቂያ ላይ ከወደ የመን የተሰማዉ ዜና ግን ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ብቻ ሳይሆን ለምን ኢትዮጵያዊ ሆኜ ተፈጠርኩ የሚያሰኝ ነዉ። አገራቸዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ ተስፋቸዉን ያጨለመባቸዉ አያሌ ኢትዮጵያዉያን እንደ ዜጋ የሚመለከታቸዉና የት ገቡ ወይም የት ደረሱ የሚል መንግስት ስለሌላቸዉ ለቀበር እንኳን ሳይበቁ ቀይ ባህር ዉጧቸዉ ቀርቷል። ለወትሮዉ ለኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ብዙም ግድ የሌለዉ የየመን መንግስት እንኳን ሰብዓዊነት ቆርቁሮት ቀይ ባህር እንደዋጠ ያስቀራችዉን ኢትዮጵያዉያን አስከሬን ፍለጋ ጀልባና መርከብ ሲያሰማራ፤ 99 በመቶ ኢትዮጵያዉያን መረጡኝ የሚለዉ የወያኔ አገዛዝ ግን የራሱ ዜጎች ሞት የተመቸዉ ይመስል ሰምቶ እንዳልሰማ ተመልካች መሆኑ አልበቃ ብሎት በተላላኪዉ ጠ/ሚኒስተር በኃ/ማሪያም ደሳለኝ አማካይነት ጭራሽ በአለም ዙሪያ የሚገኙ ስደተኞችን ሲዘልፍና ሲያጥላላ ከርሟል። አሜሪካ፤ አዉሮፓና መካከለኛዉ ምስራቅ ዉስጥ በየጋዜጣዉ በየቴሌቪዥኑና በማህበራዉ ሜድያዉ የአንድ ሳምንት የመወያያ አርዕስት ሆኖ የከረመዉ የኢትዮጵያዉያኑ እልቀት አገራቸዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ግን ለይስሙላ እንኳን ስማቸዉ አልተነሳም።
አዎ እኛ ኢትዮጵያዉያን የትም እንኑር የት በህይወታችን ቆመንም ሆነ ሞተን ዜጎቼ ብሎ የሚቆረቆረልንና ለወገንና ለአገር ልጅ የሚደረገዉን ልዩ እንክብካቤ የሚየደርግልን መነሰግስ/ት የለንም። አልፎ አልፎ የወያኔ ባለስልጣኖች አዉሮፓና አሜሪካ ሲመጡ በየኤምባሲዉና በሚስጢር በሚያዙ ሆቴሎች ለዉይይት የሚጋብዙት ታማኝ ሎሌዎቻቸዉንና የአንድ አካባቢ ተወላጅ የሆኑ ሰዎችን ነዉ እንጂ ብዛት ያለዉን ሌላዉን ኢትዮጵያዊ የት ወደቀ ብለዉ እንኳን አይጠይቁም። እንዲያዉም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ከጠ/ሚ ኃ/ማሪያም ደሳለኝን ጨምሮ ሁሉም የወያኔ ባለስልጣኖች በዉጭ አገሮች የሚኖረዉን ኢትዮጵያዊ እንደ ባዕድ መመልከና መዝለፍ ጀምረዋል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገሮች እኛ ኢትዮጵያዉያን ተገናኝተን እርስ በርስ ካልመከርንና ችግሮቻችንን በጋራ እኛዉ ካልፋታን እንደ ዜጋ የሚንከባከብልን ቀርቶ እንደ ሰብዓዊ ፍጡር የሚመለከተንም እንደሌለን ነዉ። ይህንን ደግሞ ባለፈዉ አመት ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ አሁን በቀርቡ ደግሞ የመን ዉስጥ በግልጽ አይተናል። ወገኖፐቻችን የሆኑ ኢትዮጵያዉያን የመን እንገባለን ብለዉ ቀይ ባህር ዉስጥ የአሳ ሲሳይ ሆነዉ ሲቀሩ በጠ/ሚኒስቴርነት ስም የወያኔ ተላላኪ የሆነዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ጭራሽ በአለም ዙሪያ የሱን እርግጫ፤ እስርና የጅምላ ግድያ ሸሽተዉ የተሰደዱ ሲትዮጵያዉያንን እጅግ በጣም አስነዋሪና አስጸያፊ በሆነ መለኩ ሲዘልፋቸዉ ተሰምቷል። የሚገርመዉ ባለፈዉ ህዳር ወር ማለቂያ ላይ ቀይ ባህር ዉስጥ ሰጥመዉ ካለቁት ከሰባ በላይ ወገኖቻችን ዉስጥ ገሚሶቹ ባለፈዉ አመት ከሳዑዲ ተባርረዉ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱና እነ ቴዎድሮስ አድሃኖም ኢትዮጵያ ለዜጎቿ የማታደርጉወ ምንም ነገር የለም ብለዉ የተናገሩላቸዉ ሰዎች ናቸዉ።
ባጠቃላይ እኛ ኢትዮጵያዉያን አገራችን ዉስጥ ተዋርደናል፤ በስደት በምንኖርባቸዉ አገሮች ዉስጥም ተዋርደናል። አገር ዉስጥ ወያኔ እንዳሻዉ ያስረናል፤ ይደበድበናል ይገድለናል። ይህንን ጠልተን ከአገራችን ስንሰደድ ደግሞ በየበረሃዉና በየባህሩ ላይ ክብርና ወግ ላለዉ ቀብር እንኳን ሳንበቃ እንደወጣን እንቀራል። ካሁን በኋላ እንደ ህዝብ መብታችንና ነጻነታችን ተከብሮ አንደ አገር ደግሞ አንድነታችንና ዳር ድንበራችን ተጠብቆ ለመኖር የምንፈልግ ከሆነ አማራጩ አገራችንን አንደ ምጽዐት ለቅቀን መዉጣት ሳይሆን ለዚህ ሁሉ ዉርደትና መከራ ከዳረጉን ዘረኞች ጋር ፊት ለፊት መግጠምና ይለየለት ማለት ብቻ ነዉ። ወያኔ የሚፈጽምብን ሰቆቃ እንዲቆም፤ አስርና ግድያዉ አክትሞ ስደት እንዲያበቃ ብቸኛዉ አማራጭ እነዚህ ነገሮች ሲፈጸሙ መግለጫ ማዉጣትና ከንፈር መምጠጥ ብቻ ሳይሆን የችግሮቻችንን ምንጭ ማድረቅ ነዉ፤ ወይም ዘረኛዉን የወያኔ አገዛዝና እሱ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት ነቃቅለን ማስወገድ ብቻ ነዉ። በዜግነታችን ተከብረንና በገዛ አገራችን ኮርተን መኖር የምንችለዉ ይህንን ስናደርግ ብቻ ነዉ።