Thursday, October 29, 2015

በአርባምንጭ በርካታ ዜጎች መታሰራቸው ታወቀ

• የሰማያዊ ፓርቲ የአርባምንጭ አስተባባሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ታስረዋል
ትናንት ጥቅምት 17/2008 ዓ.ም ከሌሊቱ 8 ሰዓት ጀምሮ በርካታ የአርባ ምንጭ ነዋሪዎች በአፈሳ እየታሰሩ መሆኑን የነገረ ኢትተጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከነዋሪዎቹ መካከል የሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አስተባባሪዎችም ታስረዋል፡፡ ከአስተባባሪዎቹ መካከል አቶ ሉሉ መሰለ፣ ባለቤታቸውና ልጃቸው ሌሊት 8 ሰዓት ላይ የታሰሩ ሲሆን ባለቤታቸውና ልጃቸው ከቀኑ 10 አካባቢ መፈታታቸውን ተገልፆአል፡፡ ከአቶ ሉሉ መሰለ በተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አስተባባሪ እና በአሁኑ ወቅት ቂሊንጦ ታስሮ የሚገኘው የአቶ በፍቃዱ አበበ እናት ወይዘሮ አልማዝ ካሳ እንዲሁም እህቱ ወይዘሮ አየለች አበበም ቤታቸው ተበርብሮ መታሰራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአቶ በፍቃዱ አበበ ቤተሰቦች መሳሪያ ከቤታችሁ ተገኝቷል ተብለው ተከሰው ፍርድ ቤት እየተመላለሱ የሚገኙ ሲሆን ወይዘሮ አየለች አበበ ቤታቸው ያልተገኘውን መረጃ ተገኝቷል ብላ እንድትፈርም መገደዷን እየታደነ የሚገኘው ወንድሟ ባንተወሰን አበበ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፆል፡፡

አርባ ምንጭ ውስጥ በአፈሳ እየታሰሩት የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ሲሆኑ ሌሎች ሰዎችም መታሰራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይ አርባ ምንጭ ከተማ 03 ቀበሌ በተለምዶ ድኩማን ሰፈር ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ነዋሪዎች አሁንም እየታሰሩ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ በከተማው በርካታ ዜጎች እንደታሰሩ የተገለፀ ሲሆን ዛሬ ጥቅምት 18/2008 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ 8 ወጣቶች መታሰራቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ ዛሬ ጥቅምት 18/2008 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከታሰሩት መካከል የማታ ወርቅ ጫንያለው፣ ውብሸት ጌታቸው፣ አምሳሉ ከበደ እና ሙሉነህ የተባሉ ዜጎች እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፖሊስና ደህንነቶች ሌሎች ዜጎችንም በመኪና እየዞሩ እየለቀሙ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

Wednesday, October 28, 2015

የወያኔው ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ለይ በግፍ የ3 አመት እስር መፍረዱን ተከትሎ ታናሽ ወንድሙ Tariku Desaleng በፌስቡክ ለይ ይሄን አሳዛኝ ማስታወሻ ጽፎልን ነበር፡፡



አሁን እማወራው ስለ ብርቱው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሳይሆን ስለ ሆደ ባሻዋና ሩህ ሩህዋ እናታችን ነው!!
ከእንቅልፌ ስነሳ ከንጋቱ 12 ሰዓት አልሞላም 70 ዓመት ያለፋት እናታችን የተመስገንን ነገር አሳለፋ ለሰጠችው ቅዱስ ሜካኤል የልጄን ነገር አደራ ልትል ሄዳለች፡፡ እናታችን ተመስገን ከታሰረበት ቀን ጅምሮ በብዙ እጥፍ አርጅታለች ነገሮቿ ሁሉ እህህ ነው መተኛት አቁማለች ሸለብ አደርጓት በነቃች ቁጥር አይ ልጄ እንዴት ሆኖ ይሆን ትላላች እንባ ባቀረዘዙ አይኖቿ እራስጌዋ ላይ የተሰቀሉትን የመድሃኔዓለም እና የቅዱስ ሚካኤል ምስል እየተመለከትች ልጄስ ማለት ከጀመረች ዛሬ 14 ቀኗ ነው ፡፡ ከንጋቱ 12፡45 ሆኗል እናቴ መታለች ነጠላዋን ሳታወልቅ ማታ ሳትተኛ ለተመስገን የሚሄድን ስንቅ የሰራችውን ለማሞቅ እየቀነሰች ነው በመሀል ተመሰገን ፣ አቢዮት .. አንተ ትንሽ ልጅ አለች እናታችን አንዳችንን ለመጥራት የሁላችንም ስም መጥራት ልምዷ ነው መብራት የለም መስልኝ እስቶቩ እንቢ አለኝ አለችኝ፡፡ ቀና ስል መብራት አለ ተነስቼ ሄድኩኝ እስቶቩን አልሰካቸውም ሰሞኑን ከቀልቧ ስላልሆነች አንደዚህ አይነት ነገር እየተደጋገመ ነው፡፡ ከምግቡ ጋር ለተመሰገን የሚሄድ ቡና ለማፍላት ጀበናዋን አንደኛው ምድጃ ላይ እየጣደች ነው ..አሳዘነችኝ.. መሄድ ያለበትን ነገሮች ካስተካካለች በኋላ ነገ ምን እንደሚፈልግ ጠይቁት በመስማማት ራሴን ነቀነኩ ነጠላዋን እያስተካከለች ዛሬ እስጢፋኖስ ይነግሳሉ መኪና ስለማላገኝ አሁን ነው እምሄደው የሱን ነገር እንዳወክ ንግረኝ እዛው ሆኜ እጠብቃለሁ አለችኝ አሰብኩት ከጀሞ እስከ አቢዬት አደባባይ ድረስ እንዴት እንደምትሄድ አብሬሽ ልሄድ ወይ አይሆንም አንተ እሱ ጋር ሂድና እሚሉትን ትነገረኛለህ ለመውጣት ስትዘጋጅ እሺ እነደማትለኝ ባውቅም ቀጠሮው እኮ ገና ከሰዓት ነው ታቦት አውጥተሽ ቤት ብተመለሺ ጥሩ ነው ምሳ በልተሽ አረፍ ትያለሽ የሱን ነገር ሳልሰማ አንዴት እበላለሁ ብላ አየችኝ አንገቴን ደፋው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ይከተልህ በልልኝ እንዳቀረቀርኩ የድምጿን መለወጥ ስሰማ ቀና ብዬ አየኋት እናቴ እያለቀሰች ነው! ምን ላድርጋት ምንስ ብላት ትፅናናለች እንባዬ መጣ አንዳታየኝ ፊቴን አዙሬ እነግረዋለሁ አልከኝ እናቴ ስትሄድ ይሰማኛል ሁል ጊዜ ቤተክርስቲያን ስትሄድ እምታስረው ነጭ ሻሽ ወንበር ላይ ተቀምጧል ሻሽ አለማሰሯን ልብ አለማለቴ ገርሞኝ ሻሹን ይዤ ስወጣ ለሀዘን ጊዜ ብቻ ካልሆነ የማታስረውን ጥቁር ሻሽ አስራ አንግቷን ደፍታ እየሄደች ሳያት አይኔ ዳር ደርሶ የነበረው አንባዬ ወረደ፡፡ አሁን ከቀኑ 9፡05 ነው ተመስገን ላይ አንባገነኖቹ 3 አመት ከፈረዱበት 5 ደቂቃ አልፏል ለናቴ ምን ብዬ ነው እምነግራት ከጠዋት ጀምሮ ቤተክርስቲያን ተቀምጣ እየጠበቀችኝ ነው ምግብ ከበላች አንድ ቀን አልፏታል ፡፡ አውቃለሁ ተሜ ከቤተሰቡ በላይ ሀገሩን እንደሚያስቀድም! አውቃለሁ ተሜ ብርቱ እንደሆነ! አውቃለሁ ተሜ ጉዞው ቀራኒዬ ድረስ አንደ ሆነ! አውቃለሁ ተሜ ድምፅ ለተነፈጉ ሰዎች ድምፅ እነደሆነ! አውቃለሁ ተሜ የዚህ ትውልድ ወካይ እንደሆነ!፡፡ ታዲያ በስተርጅና ላይ ለምትገኘው እናታችን ይሄን አንዴት ነው እማስረዳት እናታቸን ልጄ ይመጣል እያለች በተስፋ እየጠበቀች ነው….. አሳሪዎቹ ሆይ መጦሪያዋን ለነጠቃቹሀት እርጅናዋን በመከራ ለለወጣቹሁባት ተስፋዋን ላጨለመቹሁባት እናታችን ምን ብዬ አንደምንግራት ትነግሩኛላቹ !? ምስኪኗ እናታችን ሆይ ልጅሽ ለሚወዳት ሀገሩ ሲል መክፈል ያለበትን ነገር እየከፈለ ነው! አትዋሽ ላመንክብት ነገር ሙት ብለሽ ያሳደግሽው ልጅሽ ያልሽውን ነው ያደረገው!፡፡ እናታችን ሆይ በርችልን … አሁን ይሄን ልነግርሽ እየመጣሁ ነውና…

የሐይለማርያም ደሳለኝ ጅል ፖለቲካ ሕወሓት ከሚተገብረው ሐቅ የተለየ ነው::



Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) - እንደኔ ሐይለማርያም ደሳለኝ የሚናገረው ንግግር ሁሉ ጊዜውን ያላገናዘበ ሕዝብ የሚያውቀውን ጉዳይ ያልመዘነ በእውነት ላይ ያልተመሰረተ በደመነፍስ የሚናገረው የጅል ፖለቲካ ድምር ውጤት ነው::የተመከረውን እና የተባለውን ሁሉ መልሶ የሚያስተጋባ በጥቂት ቡድናዊ ማፊያዎች የሚነዳ የአገር መሪ አለ ብሎ መናገር አንድም እርግማን ሰፋ ሲልም አንገትን የሚያስደፋ ነው::ሃይለማርያም እንደ ጠ/ሚኒስትር ብንወስደው እንኳን በፖለቲካ ያልበሰለ ገና እንጭጭ በራሱ የማይተማመን ራሱን ያላገኘ ከርታታ (ፖለቲከኛ?) ነው::

በየመድረኩ ቀርቦ የሚናገረው በጭንቀት መሆኑ ያሳብቅበታል::ለጋዜጣዊ መግለጫ ሲቀርብ የሚተነፍሳቸው ትንፋሾች ሰው ሰራሽ እንደሆኑ ራሱ በራሱ ላይ ያቃጥራል::ለሚመልሳቸው መልሶች ሁሉ ሃይል የተቀላቀለ ድምጽ በማውጣት ራሱን እንደ ባለስልጣን አድርጎ ለመሳል መሞከሩ ውሸታምነቱን ይናገርበታል::ለሚጠየቀው ጥያቄ እንኳን በፊት ለፊት ይቅርና ዙሪያ ጥምጥም ለመመለስ አለመቻሉ ልምድ አልባ እና ሰነፍ መሆኑን ያሳያል::በፖለቲካው አለም ይህን ያህል አመቶ ኖሮ ለራሱ የማይገዛ ሕዝብን ማሳመን ያልቻለ በነዱት የሚሄድ ሰው ቢኖር ሃይለማርያም ነው::በፍጹም መሻሻል አይታይበትም ያው እንደተርመጠመጠ ዛሬም አለ::

በትጥቅ ትግል መንግሥት ለመቀየር እየሠሩ ያሉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ውጤት እንደማያመጡ እርግጠኞች ነን በማለት መናገሩ ምን ያህል ስለ ኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች መረጃ እንዳሌለውና አስተላልፍ ይተባለውን ጥላቻ ከማሳየቱም በላይ እርግጠኛ ነው ማለት በውስጥ አለመተማመኖች እንዳሉ ግልጽ ያደርጋል::በትጥቅ ትግል ላይ የተሰማሩ ተቃዋሚዎች ውጤት ማምጣት ካልቻሉ በመንግስት መሪዎች ዘንድ አሊያም በጠ/ሚ ዘንድ ቃላቶችን እና አትኩሮቶችን ማግኘት ቻሉ?ካለምንም ምክንያት የፍራቻ ቃላቶችን ለመተንፈስ ለምን በወያኔ በኩል ተፈለገ?የሕወሓት ፖለቲካ ችግሩ ተከታይ ጥያቄዎችን የሚያስከትሉ የላሞኛችሁ ጉዳዮችን መናገር ላይ ነው::ሕወሓት በፍርሃት ስለራደ መሰሪ እና ገዳይ ቡድን ነው::በትጥቅ ትግል ላይ የተሰማሩ ተቃዋሚዎች ምን ያህል ስጋት እንደሆኑ በገሃድ የወያኔ ድርጊቶች እና ቃላቶች እያመለከቱን ነው::

በፖለቲካ ጫና የተሽመደመዱ ዜጎች ምድር በተጭበረበረ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ለድህንነት የተዳረጉ ሕዝቦች በሞሉበት አገር ዜጎች በአስተሳሰባቸው ብቻ ተይዘው ወህኒ የሚወረወሩበት ያልታጠቁ ዜጎች እንደ ጦር ወንጀለኛ አሸባሪ ተብለው እስከሞት የሚፈረድባት ፍትህ አልባ አገር ጥቂት ባለስልጣናት ባደራጁት የዘረፋ ቡድኖች የሃገር እና ሕዝብ ሃብት በሚበዘበዝባት አገር የፖለቲካ መሪዎች እና የሃይማኖት ምሁራን ካለወንጀላቸው በሚሰቃዩባት ኢትዮጵያ ውስጥ ሃገር እየበለጸገ እያደገ ነው ማለት በሕዝብ ላይ ያለውን ንቀት ያሳያል::የሃሳብ ልዩነት ያላቸው በሰላማዊ መንገድ ያቀረቡ እስር ቤት እንደሆኑ ሃይለማርያም ዘንግቶታል::በእጁ ሊገባለት ያልቻለውን እና በዳበረ መረጃ ማንነቱን ያወቀውን ዲያስፖራውን ለማታለል ሕወሓት የማይቧጥጠው ነገር የለም::ሃይለማርያም ተመክሮ የሚዘላብደው እና ሕወሓት የምታራምደው እኩይ ተግባር የተለያዩ ናቸው::

ፍርድ ቤቱ በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ ለሶስት አካላት ትዕዛዝ እንዲሰጥ ተጠየቀ

በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ -5ኛ መዝገብ ለተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ (2ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) እና አቶ አንሙት የኔዋስ (5ኛ ተከሳሽ) በመከላከያ ምስክርነት ተጠቅሰው በነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጉዳይ የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛው ወንጀል ችሎት ለሶስት አካላት ትዕዛዝ እንዲሰጥ ተጠየቀ፡፡ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥቅምት 12/2008 ዓ.ም አቶ አንዳርጋቸው እሱ ጋር እንደሌሉ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛው ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ መግለፁ ይታወሳል፡፡

ከ6ኛ-9ኛ ያሉት ተከሳሾች ማረሚያ ቤቱ በፈጠረው ችግር የአቶ አንዳርጋቸውን ምስክርነት ለመስማት የፍርድ ሂደታቸው እየተጓተተባቸው በመሆኑ የአቶ አንዳርጋቸው ምስክርነት ቀርቶ ብይን እንዲሰጥላቸው ሲጠይቁ 4ኛ ተከሳሽ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተህ መመሪያ ተቀብለሃል ስለተባልኩ አቶ አንዳርጋቸው መጥቶ መመስከር አለበት›› ሲል አሁንም አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡለት ጥያቄውን አቅርቦ ነበር፡፡ ከአቶ ምንዳዬ ጥላሁን በተጨማሪ 3ኛ ተከሳሽ አቶ ደናሁን ቤዛም አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲመሰክሩለት በመፈለጉ፤ እና ፍርድ ቤቱም አቶ አንዳርጋቸው ይገኙበታል ተብሎ ለታሰበው ተቋም ትዕዛዝ ለመስጠት እንዲመቸው ተከሳሾቹ እንዲጠቁሙት በገለፀው መሰረት ተከሳሾቹ ፍርድ ቤቱ ለሶስት ተቋማት ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው በደብዳቤ ጠይቀዋል፡፡

ሁለቱ ተከሳሾች ጥቅምት 15/2008 ዓ.ም ለፌደራል ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በፃፉት ደብዳቤ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዙን በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንክ ኮርፖሬት መግለጫ መስጠቱን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ መስከረም ወር 2007 ዓ.ም የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዝ፣ የእድሜ ልክና የሞት ፍርደኛ መሆናቸውን በመግለፅ የኢትዮጵያ መንግስት ፍርዱን ተፈፃሚ እንደሚያደርግ መግለፃቸውን አስታውሰዋል፡፡ በተጨማሪም በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኤምባሲ አቶ አንዳርጋቸው ዜግነታቸው እንግሊዛዊ የሆሉትን አቶ አንዳጋቸው ጉዳይ ላይ ክትትል እንደሚያደርግ በደብዳቤው አስታወስዋል፡፡

በመሆኑም ከእነዚህ ሶስት አካላት በላይ አንዳርጋቸው ፅጌ ስላሉበት ቦታ የሚያውቅ ስለሌለ ለሶስቱም አካላት አቶ አንዳርጋቸው የት እንዳሉ እንዲገልፁና አቶ አንዳርጋቸውም ምስክር እንዲሆኑላቸው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡

Source: ነገረ ኢትዮጵያ

Internet freedom falls: Freedom House

Internet freedom falls: Freedom House

WASHINGTON – Global online freedom declined for a fifth consecutive year as more governments stepped up electronic surveillance and clamped down on dissidents using blogs or social media, a survey showed Wednesday.
The annual report by non-government watchdog Freedom House said the setbacks were especially noticeable in the Middle East, reversing gains seen in the Arab Spring.
Freedom House found declines in online freedom of expression in 32 of the 65 countries assessed since June 2014, with “notable declines” in Libya, France and Ukraine.
The researchers found 61 per cent of the world’s population lives in countries where criticism of the government, military or ruling family has been subject to censorship.
And 58 per cent live in countries where bloggers or others were jailed for sharing content online on political, social and religious issues, according to the “Freedom on the Net 2015″ report.
In a new trend, many governments seeking to censor content from opponents have shifted their efforts to targeting online platforms, pressuring services like Google, Facebook and Twitter to remove content, the report said.
“Governments are increasingly pressuring individuals and the private sector to take down or delete offending content, as opposed to relying on blocking and filtering,” said Sanja Kelly, Freedom House’s project director.
“They know that average users have become more technologically savvy and are often able to circumvent state-imposed blocks.”
Freedom House said governments in 14 of the 65 countries passed laws over the past year to step up electronic surveillance.
Criticizing France
The report said online freedom took a hit in France from new restrictions on online content that could be seen as an “apology for terrorism” and from a new surveillance law.
It also noted France’s “sweeping legislation requiring telecommunications carriers and providers to, among other things, install ‘black boxes’ that enable the government to collect and analyse metadata on their networks.”
In Libya, Freedom House cited “a troubling increase in violence against bloggers, new cases of political censorship, and rising prices for Internet and mobile phone services.”
In Ukraine, the report highlighted “more prosecutions for content that was critical of the government’s policies, as well as increased violence from pro-Russian paramilitary groups against users who posted pro-Ukraine content in the eastern regions.”
The report said most countries in the Middle East and North Africa, where the emergence of the “Arab Spring” in 2010 and 2011 was aided in part by activists’ use of online social media, were cracking down on government critics.
It cited a case in Morocco where police detained 17-year old rapper Othman Atiq for three months after he criticised authorities in online videos and said other regimes in the region resorted to “public flogging” of bloggers.
Overall, 18 countries were rated as “free” online, while 28 were classified as “partly free” and 19 “not free.”
The most free among the 65 countries assessed was Iceland, followed by Estonia, Canada, Germany, Australia, the United States and Japan.
At the bottom of the list was China, worse than runners-up Syria and Iran in terms of a lack of online freedom. Cuba and Ethiopia rounded out the bottom five.
Freedom House voiced special concern in the report about laws and policies, like France’s, requiring Internet firms to keep so-called metadata, which includes the time, origin and destination of online communications.
“While acknowledging that these laws are often intended to assist law enforcement in investigating crimes or security threats, the UN Human Rights Committee, the Special Rapporteur for Freedom of Expression, and other entities have recognised that the requirements inherently infringe on the privacy rights of all in a manner that is disproportionate to the stated aim,” the report said.
“Nevertheless, many countries — including democracies — have moved to retain or expand such rules.”
Source: Addisvoice

እነ ሀብታሙ አያሌው ለጥቅምት 22 ተቀጠሩ



᎐ማረሚያ ቤት እነ ሀብታሙን አላቀረባቸውም

የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ የተበየነላቸው የአንድነት፣ የሰማያዊ እና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች ላይ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆ ጉዳያቸው በጠቅላይ ፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት አምስት ተከሳሾች ለጥቅምት 22/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡
ዛሬ ጥቅምት 17/2008 ዓ.ም የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ማረሚያ ቤት ሳያቀርባቸው በሌሉበት ቀጠሮ የተሰጣቸው የፓርቲዎች አመራሮቹ ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሽ እና አብሯቸው ይግባኝ የተጠየቀበት አብርሃም ሰለሞን ናቸው፡፡ 


የቂሊንጦ እና የቃሊቲ ማረሚያ ቤቶች እነ ሀብታሙን ፍርድ ቤት ያላቀረቡበትን ምክንያት ፍርድ ቤቱ ሲጠይቅ፣ ‹‹ቃሊቲ በፕላዝማ ይታያል ስለተባለ አላመጣናቸውም፤ ከአይ.ሲ.ቲ ጋር ተነጋግረው ነው ያስቀሯቸው›› የሚል መልስ ተሰጥቷል፡፡ ማረሚያ ቤቱ እነ ሀብታሙን ብቻ ሳይሆን በሌላ መዝገብ በተለያዩ ወንጀሎች ስር የተጠቀሱ ተከሳሾችንም አለማቅረቡ ታውቋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በበኩሉ የቃሊቲ ማረሚያ ቤትን መልስ ካደመጠ በኋላ፣ ‹‹ይሄ ቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚባል ነገር የሚሆን አይደለም፤ አቅርቧቸው ብለን አዝዘን ነበር፤ እኛ ነን የምናዝዛችሁ ወይስ ማን ነው? አሁንም ቀጣይ ቀጠሮ ላይ አቅርቧቸው›› ሲል በእነ ሀብታሙ መዝገብም በሌሎች መዝገቦችም ላይ ዛሬ ላልቀረቡ ተከሳሾች ተመሳሳይ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም እነ ሀብታሙ አያሌው ሰኞ ጥቅምት 22/2008 ዓ.ም የተጠየቀባቸው ይግባኝ ያስቀርባል ወይስ አያስቀርብም የሚለውን ብይን ቀርበው ለመስማት ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡


Source: ነገረ ኢትዮጵያ

ከሀገር እንዳይወጡ የታገዱት፤ አዛውንቱ ፖለቲከኛ



በኢዮኤል ፍሰሐ
በቀዳሚዊ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ፤ በ1951 ዓ.ም ወደ ሐረር ጦር አካዳሚ በማቅናት ለሶስት ዓመታት በዚሁ አካዳሚ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በ1954 ዓ.ም ከአካዳሚው በምክትል መቶ አለቃነት ተመረቁ፡፡ ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በአካዳሚው ውስጥ በአልጣኝነት ተመድበው ለአምስት ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በምድር ጦር ጠቅላይ መምሪያ የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹሙ ረዳት ሆነው ሰርተዋል፡፡ ቀጥሎም በምድር ጦር ጠቅላይ መምሪያ የትምህርትና ዘመቻ መምሪያ የትምህርት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል፡፡ በ1970 ዓ.ም ውጪ ጉዳይ ሚኒስተር መ/ቤት ተመድበው በጅቡቲ ለ10 ዓመታት ያህል በዲፕሎማትነት አገልግለዋል፡፡ ከጅቡቲ መልስ የመካከለኛው ምስራቅና የሰሜን አፍሪካ ዋና ክፍል ኃላፊ ሆነው ለሀገራቸው ግልጋሎት ሰጥተዋል፡፡ በ1988 ዓ.ም በገዛ ፍቃዳቸው ጡረታ የወጡ ሲሆን፤ ከዚህ ጊዜ አንስቶም በግል ስራ ላይ ተሰማርተዋል፡፡ የዚህ ሁላ ልምድ ባለቤት የትላንትናው መኮንን እና ዲፕሎማት የዛሬው ፖለቲከኛ፤ አርጋው ካብታሙ ናቸው፡፡

የሻለቃው የፖለቲካ ተሳትፎ መችና እንዴት ተጀመረ?
ሻለቃ አርጋው፣ የፖለቲካ ተሳትፎዋቸውን አሃዱ ብለው የጀመሩት በ1996 ዓ.ም መኢአድን በመቀላቀል ነው፡፡ ወደ ሰላማዊ ትግል የገቡበትን ምክንያት ሲያስረዱም፡- ‹‹አምባገነንነት በጣም ስላማረረኝና ስለከነከነኝ የተቃውሞ ፖለቲካ ጎራውን ለመቀላቀል ወሰንኩ›› ይላሉ፡፡ እንደ እሳት የሚፋጀው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ረመጥ፣ ሻለቃውን ለመጎብኘት ጊዜም አልፈጀበትም፡፡ መንግስት በዝረራ በተሸነፈበት ምርጫ 97 የቅንጅት አመራሮችን ወደ እስር ቤት ሲያግዝ፤ ወደ እስር ቤት ከተጋዙት የቅንጅቱ አመራሮች መሃል ሻለቃ አርጋው አንዱ ናቸው፡፡ በማዕከላዊ ለሁለት ወራት በጭለማ ቤት የታሰሩ ሲሆን፤ ከማዕከላዊ እንደወጡም በአለምበቃኝና ቃሊቲ ወህኒ ቤቶች ታስረዋል፡፡ ለ 1 ዓመት ከ6 ወር ያህል ከታሰሩ በኋላ የቅንጅቱ አመራሮች ከእስር ሲፈቱ ከእስር ተለቀዋል፡፡ ከወህኒ ቤት እንደወጡም በመኢአድ ውስጥ በሥራ አስፈፃሚነት የፖለቲካ ተሳትፎዋቸውን የቀጠሉ ቢሆንም፤ በፓርቲው ላይ አንዳንድ የአካሄድ ችግሮች ስላስተዋሉ፤ ፓርቲውን ለመልቀቅ እንደተገደዱ ይታወቃል፡፡ መኢአድን ለቀው አፍታም ሳይቆዩ፤ በ2002 ዓ.ም አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲን (አንድነትን) ተቀላቀሉ፡፡ ፓርቲው ለአገዛዙ ሎሌዎች ተላልፎ እስከተሰጠበት፣ ጥር 22 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ በፓርቲው ውስጥ ከተራ አባልነት እስከ ብሔራዊ ምክር ቤት ድረስ በመዝለቅ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡
ከሀገር እንዳይወጡ ስለተደረገበት ቀንና ስለቀረበላቸው ምክንያት

ሻለቃ አርጋው ካብታሙ፣ ሚያዚያ 10 ቀን 2007 ዓ.ም በሀገረ አሜሪካ የሚገኘው ልጃቸው ጋብቻ ሊፈፅም መሆኑን ተከትሎ፤ የጋብቻው ሥነ ሥርአት ላይ ለመገኘት አስፈላጊ የሚባለውን የወረቀት ሥራ አጠናቀው፤ ቦሌ ዓለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ደረሱ፡፡ በወቅቱ የያዟቸው ሻንጣዎች ወደ አውሮፕላኑ ከተጫኑ በኋላ፤ ወደ አውሮፕላኑ በማቅናት ላይ ሳሉ፤ የኢሚግሬሽንና ደህንነት መ/ቤት ሰራተኞች የሻለቃውን ፓስፖርት በመንጠቅ ከሀገር መውጣት እንደማይችሉ ገለፁላቸው፡፡ ምክንያቱን ቢጠይቁም ከኢሚግሬሽን ኃላፊዎች በኩል አንድም ምክንያት አልተሰጣቸውም፡፡ ፓስፓርታቸውን ለማግኘት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርጉም፤ ሙከራቸው አልተሳካም፡፡ የዚህ ፅሑፍ ፀሐፊ ይህን በማስመልከት ሁለት የሕግ ባለሙያዎችን አነጋግሯል፡፡ ‹‹አንድ ሰው ከሀገር እንዳይወጣ እንዴትና በምን መልኩ ይታገዳል፤ የሚያግደው አካልስ ማን ነው?›› ፣ ‹‹የኢሜግሬሽንና ደህንነት መ/ቤት አንድን ሰው ከሀገር እንዳይወጣ የማገድ ስልጣን ተሰጥቶታል ወይ?›› በሚሉት ነጥቦች ላይ የሕግ ባለሙያዎቹ አስተያየት እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

በጥብቅና ሙያ የተሰማሩት የቀድሞ አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ገበየሁ ይርዳው፣ ‹‹ፍርድ ቤት አንድን ሰው፣ ከሀገር እንዳይወጣ በተለየ ሁኔታ የሚገድብባቸው ሁኔታዎች አሉ›› ይላሉ፡፡ ይህንንም ሲያስረዱ፡- ‹‹በፍርድ ቤት ክስ የቀረበበትና በወንጀል የተጠረጠረ ሰው ለተወሰነ ጊዜ ጉዳዩ በፍርድ ቤት እስኪጣራ ድረስ ከሀገር እንዳይወጣ ይደረጋል›› በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በአንፃሩ ሻለቃ አርጋው በወንጀል የማይፈለጉ እንዲሁም ፍርድ ቤት ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ የጣለባቸው ሰው እንዳልሆኑ ይታወቃል፡፡ ፓስፖርታቸውን የተነጠቁትም ሆነ ከሀገር መውጣት እንደማይችሉ የገለፁላቸው የኢሚግሬሽንና ደህንነት መ/ቤት ሰራተኞች መሆናቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ገበየሁ ይርዳው፣ ይህንን በማስመልከት እንዲህ ይላሉ፡፡ ‹‹ኢሚግሬሽን ፍርድ ቤት አይደለም! አንድን ሰው ከሀገር እንዳይወጣ ሊያግድ የሚችለው ፍርድ ቤት ነው፡፡ ኢሚግሬሽን ይህን ካደረገ፤ ሕገመንግስታዊ መብት ጥሰት አካሂዷል ልንለው እንችላለን›› በማለት አስተያየታቸውን አጠቃለዋል፡፡
በሌላ በኩል በጥብቅና ሙያ የካበተ ልምድ ያዳበሩትና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ክሶች በመያዝ ለተከሳሾች ተከላካይ ጠበቃ በመሆን የሚቆሙት፤ ጠበቃ አምሃ መኮንን የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

‹‹በሕግ ጥበቃ የተደረገለት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ከሀገር የመውጣት፣ ወደ ሀገር የመግባት በሕገ-መንግስቱ የተረጋገጠ መብት አለው፡፡ ይሄ መብት በሕገ-መንግስቱ ላይ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አልተቀመጠለትም፡፡ በዚህና በዛ ምክንያት ወይም በልዩ ሁኔታዎች ይሄ መብት ሊገደብ ይችላል ተብሎ የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ የለም፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ፣ ኢሚግሬሽን ፓስፖርት ነጥቆ፤ አንድን ሰው ከሀገር እንዳይወጣና ወደ ሀገር እንዳይገባ ክልከላ ወይም እንቅፋት ከፈጠረ የሰውየውን፣ ከሀገር የመውጣትና ወደ ሀገር የመግባት መብት ብቻ ሳይሆን ቀጥታ ሕገ-መንግስቱን የሚጣረስ ድርጊት ነው እየፈፀመ ያለው›› በማለት አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡

ጠበቃ አምሃ፣ የኢሚግሬሽን መ/ቤት ኃላፊነት ሲያስረዱም፡- ‹‹የኢሚግሬሽንና ደህንነት መ/ቤት በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ፓስፖርት መስጠት፣ ማደስና የመሳሰሉትን ከመከወን ባለፈ ሌላ ሚና የለውም›› ይላሉ፡፡

ሻለቃ አርጋው ካብታሙ፣ ይህ ፅሁፍ ተጠናክሮ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ከኢሚግሬሽን ኃላፊዎች በኩል ከሀገር መውጣት የማይችሉበት ምክንያት እንዳልተገለፀላቸውና ፓስፖርታቸውም እንዳልተመለሰላቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የዚህ ፅሑፍ ፀሐፊ በቀጣይነት፣ ፓስፖርታቸውን እንደ ሻለቃ አርጋው የተነጠቁ፤ የቀድሞ የአንድነት ፓርቲ አባላትን፣ የሚመለከታቸውን የኢሚግሬሽን ኃላፊዎችና የተለያዩ የሕግ ባለሙያዎችን በማነጋገር ትንታኔያዊ ሐቲት (Feature Article) አዘጋጅቶ ለማቅረብ ጥረት ያደርጋል፡፡

Tuesday, October 27, 2015

‹ዞን ፱› ከትላንት እስከ ዛሬ

ይህ ጽሁፍ የዞን፱ ጦማርን አስልክቶ በቀለም ቀንድ ጋዜጣ ላይ የወጣ ነው ፡፡ አርታኢው በጠየቁን መሰረት ለዞን9 ነዋርያን ይነበብ ዘንድ እዚህ አትመነዋል፡፡

በሙሉቀን ተስፋው

ብዙዎቻችን ስለ ዞን ፱ ጦማርያን እንጅ ስለ ‹ዞን ፱› ብሎግ ያለን ግንዛቤ ውስን ሊሆን ይችላል፡፡ እንዴት ተመሰረተ? ለምን ዞን ፱ ተባለ? ጦማርያኑ ተጠራርገው ወደ እስር እስኪወርዱ ድረስ ምን አከናወኑ? ለምን ሁሉም ሊታሰሩ ቻሉ? እንዴት ተፈቱ በሚለው ላይ ዘርዘር አድርገን ለማዬት ወደድን፡፡  

በ2004ዓ.ም. ከወደ ቤሩት አንድ መጥፎ ነገር ተከሰተ፡፡ ‹ዓለም ደቻሳ› የተባለች ኢትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ተገደለች፡፡ የሚያሰሯት ሰዎች ታማ ነው የሞተች ቢሉም የሊባኖስ ቴሌቪዥን በአሰሪዎቿ በገመድ ስትጎተት የሚያሳይ ምስል ለቀቀ፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውያንን አስቆጣ፡፡የበለጠ የሚያሳዝነው ደግሞ ‹ዓለም› የሁለት ልጆች እናት ስትሆን ወደ ቤሩት የሄደችውም ገንዘብ ተበድራ ነበር፡፡ ‹ልጆቼንና ቤተሰቦችን ከችግር አድናለሁ› የሚል ተስፋን ይዛ የተጓዘችው ዓለም የተበደረችውን ገንዘብ እንኳ ሳትከፍል ሕይወቷ ማለፉ ሀዘኑን የከበደ አደረገው፡፡‹ዓለምን› ዓለም ከዳቻት፡፡ በማህበራዊ ሚዲያው በሰፊው ተራገበ፡፡
ከአስር በላይ የሆኑ ሰዎች በፌስ ቡክ ‹‹የዓለምን ቤተሰቦች ለምን አንረዳም›› የሚል እንቅስቃሴ ጀመሩ፡፡ አንዳንዶቹ በርግጥም ቀደም ሲል ጀምሮ የራሳቸው ብሎግ ነበራቸው፡፡ ብዙ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ሰው ሐሳቡን ደገፈው፡፡ ምናልባትም ማህበራዊ ሚዲያ መሬት የነካ ስራ በኢትዮጵያ የተሰራበት የመጀመሪያ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ዘመቻው ፍሬ አፈራና በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ለዓለም ደቻሳ ቤተሰቦች ድጋፍ የሚውል የገቢ ማሰባሰብ መርሐ ግብር በሚያዚያ 2004 ዓ.ም ተዘጋጀ፡፡ አዘጋጆቹ ደግሞ እኚሁ ከደርዘን በላይ የሆኑ ልጆች፡፡ ገቢማሰባሰቡ ውጤታማ ሆነና የተፈለገው ድጋፍ ለዓለም ቤተሰቦች ተሰጠ፡፡

ከአዘጋጆቹ ጥቂት የሚሆኑ ልጆች ለምን ይህ ሆነ? የሚል ጥያቄ አንስተው በሰፊው ተወያዩ፡፡ የሥርዓቱ ብልሹነት ዜጎችን ለዚህ እንደሚዳርጋቸው ለማወቅ ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ አማካሪም ቀጥረውም ማስጠናት የሚጠይቅ አልነበረም፡፡ ከብላቴናዎቹ የእሳቤ አድማስ በላይም አልሆነም፡፡ለሁሉም ግልጽ የሆነ ነገር ነው፡፡ ሥርዓቱ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እኩል የሆነች፣ ዜጎች በአገራቸው ሰርተው የሚያድጉበት መንገድ ዝግ የሆነባት፤ ዜጎቿ በሰው ሀገር እንደ ዓለም ደቻሳ ኢሰብዓዊ በሆነ መልኩ ሲገደሉ እንኳ መጠየቅ የማይችል እንደሆነ ለማወቅ የመጠቀ አእምሮ ባለቤት መሆን አይጠይቅም፡፡ ግልጽና ግልጽ ፍንትው ብሎ የሚታይ እውነታ ነው፡፡
ብላቴናዎቹ የችግሩን ምንጭስ አወቅን፤ ከዚህ በኋላ ምንድን ነው ማድረግ የምንችለው? የሚል ወሳኝ ጥያቄ አነሱ፡፡ የዚህን ጥያቄ መልስ ማገኘት ቀላል ነው፤ ግን መስዋትነት ይጠይቃል፡፡ ለዚያውም የወጣትነት የጌጥ ዘመንን የሚበላ መስዋትነት፡፡ መስዋትነቱ ወንጀል ስለሆነ አይደለም-ግን በአፋኝ ሥርዓት ውስጥ ለመብት ቦታ የለም፡፡ ሀገራችን የጋራ እናድርጋት፤ ስለሚያገባን ስለሀገራችን እንነጋገር፤ አማራጭ ሐሳብ እናቅርብ ማለት ያስወነጅላል፡፡ በሞት ፍርድ አሊያም በእድሜ ልክ እስራት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡ የማን ደፋሮች ናቸው ፈርዖንን የሚናገሩ? በፈርዖን ላይ ማነው ከቶ ምላሱን የሚያነሳ? እንደሙሴ ኮልታፋ ለመሆን ካልሆነ በስተቀር? ያስብላል፡፡ ለፈርዖን የሰው ልጆች ደምናስቃይ የሰርግና የምላሽ ያክል ይጥሙታል፡፡ የጨቋኝነት ባህሪው ይኸው ነውና፡፡
ብላቴናዎቹግን ይህን አስበው ፈርተው ወደ ኋላ አላፈገፈጉም፡፡ የዓለምን ቤተሰቦች ለመርዳት ዝግጅቱን ካስተባበሩት 5 ልጆች፣ ፌስ ቡክ ላይ በንቃት ይከታተሉ ከነበሩት ደግሞ 4 ልጆች ሲደመሩ 9 ያክል ልጆች ሆነው የ‹አክቲቪዝም› ሥራ ለመስራት ዝግጅታቸውን አጠናቀቁ፡፡የፖለቲካ እስረኞችን በፕሮግራም ለመጠየቅ የእቅዳቸው አካል አደረጉት፡፡ በፌስ ቡክ፣ ቲዊተርና በየነ መረብ ዘመቻ ጀመሩ፡፡ በ2005ዓ.ም. ከእለታት በአንደኛው ቀን ‹ርዕዮት አለሙን› ለመጠየቅ 9 ሆነው ቃሊቲ ወረዱ፡፡ ርዕዮት አለሙ ጋር እያወሩ አንዲት ‹አሸባሪ› ሴት ‹‹እንዴት ናችሁ ዞን ፱ኞች?›› አለቻቸው፡፡ ስሟ ሒሩት ክፍሌ ይባላል፤ በግንቦት 7 አባልነት ቃሊቲ የወረደች ‹አሸባሪ ሴት› ናት፡፡ ብላቴናዎቹ ግራ ገባቸው፤ ‹ይህች ሴት እብድ ናት እንዴ?› ሳይሉ አይቀሩም፡፡ በእርግጥ በጠባብ አጥር ውስጥ ከብዙ ቶርቸርጋር መኖር ሊያሳብድ እንደሚችል ግልጽ ነው፡፡ ባሕታዊ እንዳይሏት ቃሊቲ ገዳም አይደለም፡፡

ርዕዮት አለሙ ብዙ እንዲጨነቁ አልፈቀደችም፡፡ በዝርዝር የ‹አሸባሪዋን ሴት› ንግግር ተረጎመችላቸው፡፡ ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ ቃሊቲ ማረሚያቤት በስምንት ዞን የተከፋፈለ ነው፡፡ ለካ የቃሊቲ ታሳሪዎች እኛን ከማረሚያ ቤቱ አጥር ውጭ የምንኖረውን ዜጎችን ‹ዞን ፱ኞች› እያሉ ነው የሚጠሩን፡፡ ስለዚህ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥ አንድ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ‹ልማታዊው አርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝ› ቢያዘጋጅ እንዲሁም ለተወዳዳሪዎቹ ‹‹ሰፊውና ብዙ እስረኛ ያለበት ዞን የትኛው ነው?›› ብሎ ቢጠይቅ መልሱ ‹‹ዞን ፱››የሚል ይሆናል፡፡ ሚስጥሩ ግልጽ ነው፤ በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሁሉም ዜጋ እስረኛ ነው፤ ሁሉም ዜጋ የፈርዖን ግዞተኛ ነው፡፡

በበየነመረብ ለሚያደርጉት ዝግጅት ማን እንበለው? እያሉ ሲያነሱ ከብላቴኖቹ አንዱ ጆማኔክስ ‹የአሸባሪዋን ሴት› ቃል ‹‹ለምን ዞን ፱አንለውም?›› የሚል ሐሳብ አቀረበ፤ በሙሉ ድምጽ ጸደቀ (እንደ ኢህአዴግ ፓርላማ እንዳትሉ አደራ)፡፡ ብላቴኖቹ ‹‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!›› የሚል መሪ ቃል ይዘው ዘመቻቸው ጀመሩ፡፡ ዘመቻው ፍጹም ሰላማዊ፣ ብዕር እንጅ ጥይት ያልያዘ፣ ሰላምን እንጅ ጥፋትንያልሻተ፣ በፊትም በኋላውም ምንም ኮልኮሌ የሌለው ነበር፡፡

ልጆቹ በጋራ ‹‹የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ›› የሚል በጋራ ስለሀገራችን እንነጋገር፤ የጋራ ትርክት እንፈለግ የሚል ይዘት ያለው ጽሁፍ ጻፉ፡፡ድረ ገጹ በተከፈተ በ15ኛ ቀኑ ሀገር ውስጥ ያሉ ሰዎች እንዳያዩት ታገደ፡፡ ለፈርዖን ምን ይሳነዋል? ጌታውን አመስግኖ ማደር ያለበትን ምስኪን ሕዝብ ስለምን የእነዚህን ብላቴኖች ወግ ያነባል? በቃ ተከለከለ፡፡ ያም ሆኖ አራት ተከታታይ የበየነ መረብ ዘመቻዎች ተካሄዱ፡፡አንደኛው ሕገ መንግሥቱ የጸደቀበትን 18ኛ ዓመት በዓል ሲዘከር ‹‹ሕገ መንግሥቱ ይከበር›› ያልተከበሩ የሕገ መንግሥቱን አንቀጾች ዘርዝረው ተቹ፡፡ ‹‹ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት አሁኑኑ ለሁሉም!›› በማለት አንቀጽ 29ን መሰረት በማድረግ ዘመቻውን ደገሙት፡፡ሦስተኛም ‹‹የሰላማዊ ሰልፍ መብታችን ይመለስ!›› ሲሉ ሠለሱት፡፡ 4ተኛም ‹‹ኢትዮጵያዊ ሕልም ኑ አብረን እናልም!›› ሲሉ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡

የልጆቹ ድምጽ ቀልቃላ ነበር፤ ብዙ ርቀት ብዙ በጣም ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ የሚሰማ፡፡ እንቅልፍ የሚቀሰቅስ ድምጽ! ፈርዖንን የማያስተኛ፡፡እነዚህ ነገረኞች ‹‹የዞን ፱ ዐመታዊ መጽሐፍ›› ብለው በነጻ አደሉ፡፡ አዲስ ራዕይ በገንዘብ በሚቸበቸብበት አገር በነጻ አንብቡብሎ መስጠት ምን ይሉታል? ግን ሆነ፡፡ መጽሐፉ በደረ ገጻቸው በነጻ ተለቀቀ፡፡

ከዚህ በኋላ ፈርዖን ትዕግዙ አለቀ፡፡ በመጀመሪያ በጓደኞቻቸው ማስፈራሪያ ተላከባቸው፡፡ ‹ፈርዖን አምርሯል፤ ከዚህ በኋላ ውርድ ከራሴ›ተባሉ፡፡ በ2006 ዓ.ም. ሁለቱን ብላቴኖች ከመላእክት የፈጠኑ ደህንነቶች ጠርተው ‹‹ስለምን አትሰሙም? ጌቶቻችን ስለምን ታስደነብራላችሁ? ካላረፋችሁ ቀሳፊ መልኣክ እንልካለን›› አሏቸው፡፡

መደናገጥ ተፈጠረ፡፡ ልጆቹ አሁንም ጠየቁ- የሠራነው ወንጀል ምንድን ነው? አሉ፡፡ መልሱ ግን ምንም ነው፡፡ ሙሴስ ቢያንስ ወገኖቹን ለማዳን የሌላ ሰው ሕይወት አጥፍቶ ነው የተሰደደ፤ እኛ ግን ምንም አልሰራንም፡፡ ስለዚህ የጌቶች ንዴት እስኪበርድ እንጠብቅና እንቀጥል ሲሉ መከሩ፡፡ ያም ሆኖ ምርጫ 2007 እየቀረበ መጣ፡፡ ይህ ምርጫ ዝም ብሎ መሆን የለበትም፤ ምንም እንኳ ጌቶች ባይወዱትም ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ሕዝብ የማንቃት ሥራ እንጀምር አሉ- በምክር ቤታቸው፡፡ የነዚህ ልጆች ምክር ቤት 547 ወንበር ላይ ከተጎለቱ ሰዎች በላይ ማነቃቃት የሚችል ከቶ ምን አይነት ታምር ቢሆን ነው? ያስብላል፡፡
በሚያዚያ2006 ዓ.ም በብሎጋቸው ምርጫ 2007ን በተመለከተ በሰፊው እንደሚሰሩ ባበሰሩ በሳምንቱ ከሚያዚያም በ17ኛው ቀን ከፈርዖን ዘንድ የጥፋት መልእክተኞች 9 ልጆችን ለቃቅመው ወሰዱ፡፡ ስድስቱ ከጦማርያን ወገን ሲሆኑ ሦስቱ ደግሞ ሐሳባቸውን የሚደገፉ ጋዜጠኞች(ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይሉና ኤዶም ካሳዬ) የጥፋት መልእክተኞች ሰለባ ሆኑ፡፡ ከጦማርያኑ ሦስቱ ደግሞ ከጥፋት ውሃ እንዲድኑ እግዚአብሔር ስለፈቀደ ከነነዌ ወጥተው ነበር፡፡ ለወሬ ነጋሪ ሶልያና ሽመልስ፣ ጆማኔክስ ካሳዬና እንዳልካቸው ኃ/ሚካኤል ቀሩ፡፡ ‹ሙሴም ከምድያም ምድር የተመለሰው ፈርዖን እንደማይጎዳው ባወቀ ጊዜ ነው፤ እኛም የፈርዖን ብርታት እስኪደክም ወደ ነነዌ አንመለስም› ብለው ይመስላል እንደወጡ ቀሩ፡፡

የታሰሩት ግን የእድሜያቸው 84 ቀን በማዕከላዊ አለፈ፤ አንዲት አራስ ሴት ልጇን ወልዳ ክርስትና አስነስታ እንግዶቿን ሸኝታ ወደ ባሏ የምትመለስበትን ጊዜ ያክል፡፡ 75 ቀናት ግን በጨለማ ክፍል ውስጥ ፀሀይ የማታውቀው ሀገር - ማዕካላዊ ሳይቤሪያ፡፡ በሳይቤሪያ ጥፊና በትር የእለትምግባቸው ሆኖ ስድብ እንደ ምርቃት እየቆጠሩት ቶርቸር ከፈጣሪ የተላከላቸው መና ሆኖ፣ ከባድ ስፖርት እየሰሩ ያን ያክል ጊዜ ቆዩ እንጅ እንደ አራስ አጥሚት እየጠጡ ገንፎ እየሰለቀጡ አልነበረም፡፡

በ2006 ሐምሌ በገባ 11ኛው ቀን ሲሆን ክስ ተፈጠረባቸው፡፡ ሲያንስ 15 ዓመት በእስር በሚያቆየው ሲበዛ ደግሞ ከመሬት በሚስወግደው በሐሙራቢ ሕግ ጨካኝ አንቀጽ ‹ሽብር ማነሳሳት፣ ለማነሳሳት ማሰብ፣ ማሴር…› በሚለው ተወንጅለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ‹‹የቀለም አቢዮት ለማስነሳትአስባችኋል›› አሏቸው፡፡ ምስክሮች ቀረቡ፡፡ ሠልስቱ ደቂቃን በናቡከደነፆር ዙፋን በቀረቡ ጊዜ ምስክሮቹ የተናገሩትን የመሰለ ነበር፡፡እነዚያ ምስክሮችስ ቢያነስ ለቆመው ምስል እንደማይሰግዱ ያውቃሉ፡፡ አለመስገድም ወንጀል የሆነበት ዘመን ነበር፡፡

ፍርዱ እየተጓተተ አንድ አመት አለፈ፡፡ እድሜም እንደዋዛ ቆጠረ፡፡ የጓጉለት ምርጫ ድራማ በቃሊቲ ሆነው አለፈ፡፡ በየጊዜው ፍርድ ቤት ይመላለሳሉ ግን ምንም ውሳኔ የለም፡፡ ምርጫ ካለፈ በኋላ ለብይን ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተያዘ፡፡ ቀደም ብሎ ግንሐምሌ 1 ቀን 2007 ዓ.ም ክሱ ተቋርጦ 5ቱ ልጆች ማለትም በክስ መዝገብ 4ኛ ተከሳሽ ማህሌት ፋንታሁንና 6ኛ ተከሳሽ ዘላለም ክብረት (ሁለቱም ጦማርያን) እንዲሁም 8ኛ ተከሳሽ አስማማው ኃ/ጊወርጊስ፣ 9ኛ ተከሳሽ ኤዶም ካሳየና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋለም ወልደየስ(ሁሉም ጋዜጠኞች) ወጡ፡፡

ጥቅምት5 ቀን 2007 ዓ.ም. ደግሞ ከአንድ ዓመት ከአምስት ወር በኋላ 1ኛ ተከሳሽ ሶልያና፣ 3ኛ ተከሳሽ ናትናኤል፣ 5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ እና 7ኛ ተከሳሽ አቤል በነጻ ተሰናበቱ፡፡ 2ኛው ተከሳሽ በፍቃዱ ኃይሉ ጽሑፎችህ ሽብር ያነሳሳሉ ተብሎ ተለይቶ ቀረ፡፡ የበፍቃዱ ክስ ወደ ወንጀል ተቀይሮ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 257/ ሀ ከአስር ቀን እስከ 6 ወር እስር ሊያስቀጣ በሚችል ወንጀል ተቀየረ፡፡ ምንም እንኳ የተከሰሰበት ወንጀል ሊያስቀጣ የሚችለውን ሦስት እጥፍ በእስር ቢያሳልፍም በ20000 ብር (ሃያ ሽህ ብር) ዋስ ከ544 ቀናት በኋላ በቂሊንጦ የተሰጠውን የሊዝ ቦታ ለተረኛ አስረክቦ ወጥቷል፡፡ 

ዞን ፱ኞች በአንድ ዓመት ከ5 ወር ጊዜ ውስጥ 39 ጊዜ ፍርድቤት ተመላልሰዋል፡፡ በፈቃዱ ለ40ኛ ጊዜ የፊታችን ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡
በጨረሻም አልን ‹‹ኢትዮጵያዊ ህልም ኑ አብረን እናልም!››

አበቃሁ

(ይህጽሁፍ የተዘጋጀው ከእስር የወጡ የዞን 9 ጦማርያን ጋር በተደረገ ውይይት ነው፡፡)

Source: Zone9

British Man On Death Row In Ethiopia Asks Government To “Bury Me In England”

Andargachew Tsege with his wife Yemi and their three children. Supplied
A British man currently on death row in Ethiopia has asked the UK ambassador to make sure that he is buried in England during a meeting that highlighted serious concerns over the handling of his case and his treatment in prison.
BuzzFeed News has seen a redacted copy of notes written by ambassador Greg Dorey of his meeting with Andargachew Tsege, 59, at Kality prison near Addis Ababa on 15 October.
Tsege, a father of three from north London, was snatched by Ethiopian security forces at an airport in Yemen last June while he was waiting for a flight to Eritrea. He was taken to Ethiopia having been sentenced to death in his absence for allegedly plotting a coup and planning to kill Ethiopian officials, allegations he denies.
Campaigners claim the real reason he faces execution is that he fell out with former prime minister Meles Zenawi after exposing government corruption.
Dorey writes in his notes that Tsege told him his status in Kality Prison was odd, “since he had no ‘warrant number’ (i.e. prisoner number), so he was ‘not even in the system’”.
Nothing had been said to Tsege about charges against him, Dorey writes, and so a formal charge sheet had been demanded. “He had only heard on radio, TV and the internet about previous charges against him,” Dorey says, “and had the right to know why he was in prison.”
The notes continue: “At this point he became a little more emotional. He said he would ‘take his own measures … I will not allow myself to be debased and dehumanised’ (no further details).”
The ambassador’s notes conclude:
I asked if he had messages for the family. He said “Hello, be brave”. He did not want “complications”. Finally, he asked us to ensure he was “buried in England” – it was important for children to know where their parent/s ended up. I said I would come and see him in a month. He commented that I had said that last time and then had been unable to visit until now, but he fully realised that was not my fault. I said I had been given a high-level promise that a visit in a month would be possible.
Supplied
Supplied
 
Tsege told the ambassador he was sleeping in a small cell with three other people and had not been outside the prison at any point. He said he was occasionally being visited by his 90-year-old father and his stepmother.
He said he picked up news from listening to other inmates’ TVs, and expressed surprise that his MP, Jeremy Corbyn, was now leader of the Labour party – “interesting, obviously the party is moving to the Left”.
He spoke at length to the ambassador about his political views. Dorey’s notes read:
He [said he was] was a prisoner of political masters but they were not applying the relevant regulations properly to him. Yet he was one of their friendliest critics, who understood them better than anyone and they shouldn’t demean him. He had served the regime in the past whole-heartedly and left it on principle. Some problems had since been resolved, others were still real…
When they had beaten and insulted him before in 2005 he had had no reason to go into opposition politics and was not even a member of the opposition – nor had he supported them. And actually Meles himself had said Ethiopia needed a “good opposition”. He had only spoken about politics by peaceful means.
Source: BuzzFeed News Reporter 

The Zone 9 Bloggers are Free: but Ethiopia Still Thinks Digital Security is Terrorism

The last of the Zone 9 Bloggers are finally free from jail, after nearly 18 months of detention for simply speaking out online. All the bloggers were acquitted of terrorism charges by the Ethiopian courts; one blogger, Befeqadu Hailu was found guilty of a single charge of "inciting violence" as a result of a confession made during his detention. He was released on bail last Wednesday. Given the time he has already served, he is unlikely to return to jail.
The victory of the bloggers over these baseless accusations of terrorism is a relief to everyone concerned: their friends, family, and their extended network of supporters around the world. However, it will not undo the months each of them unjustly spent in jail, in often horrendous conditions, isolated from their family and friends.
While Zone 9 bloggers are free, the Ethiopian government's continues to threaten and incarcerate journalists and online speakers. According the Committee to Protect Journalists, 57 media professionals have fled Ethiopia in the last five years. All of Ethiopia's commercial free press has been shuttered. Online, exiled media, and local citizen journalists have taken up some of its responsibilities but at great personal risk. Exiles are harassed and spied on, as our ongoing case Kidane v. Ethiopia demonstrates. Domestic writers continue to be accused of terrorism and thrown in jail for their work, including the journalist Eskinder Nega who on Friday spent his 15000th day in prison, four years into an 18 year jail sentence.
Befekadu Hailu goes online after 544 days in jail. Ⓒ Merfe Qulf, used with permission.
Diplomatic pressure from Ethiopia's allies, including the United States, played its part in the Zone 9 case. But these campaigns are reactive, and can only help speakers who are well-known outside the country. What broader commitment could Ethiopia's allies and business partners advocate for in Ethiopia, that could concretely make a difference to free expression in that country?
In the Zone 9 case, the heart of the prosecution revolved around Ethiopia's Anti-Terrorism Proclamation of 2009. This law presents the harshest of penalties (each blogger faced up to ten years imprisonment) for the vaguest of offenses.
Ethiopia's allies could certainly pressure the Desalegn regime to roll back the law. Unfortunately, the political cove—indeed the very mode—for the Anti-Terrorism Declaration comes from the domestic policies of those same countries. Teddy Workneh, a fellow at the University of Oregon, observes that Ethiopa's anti-terrorism laws, which include broad definitions of terrorist support and weak protections against pervasive surveillance, borrow their structure from other post-911 laws in Europe and the Americas. That means that without legal reform of their own anti-terrorism legislation at home, countries like the United States can only weakly urge Ethiopia to "to refrain from using its Anti-Terrorism Proclamation as a mechanism to curb the free exchange of ideas," rather than reject it outright.
There is, however, one step that every country critical of Ethiopia's treatment of Internet users and journalists could take. Prosecutors in the Zone 9 case used the bloggers' possession of digital security manuals, including guides to using encryption to protect communications, as evidence that they were involved in terrorist activities. International government organizations like the United Nations, the OSCE, as well as the U.S. State department have all stated that encryption and secure communications are vital to free expression, or offered or funded digital security trainings to journalists.
Foreign governments that support these initiatives need to make it clear to allies like Ethiopia that the use of encryption and efforts to improve the security of one's communications are not indicators of terrorist intent, but part and parcel of the modern journalist's (or blogger's) toolkit.
They could begin now by raising this matter in another case now passing through the Ethiopian courts: that of Zelalem Workagegne, Yonatan Wolde, Abraham Solomon, and Bahiru Degu. According to their colleagues, these Ethiopians are being detained on terrorism charges primarily because of an invitation they received to take part in a digital security training session outside of Ethiopia.
Ethiopian prosecutors are trying to turn the responsible practices of any journalist, blogger or concerned Internet user into evidence of terrorism. The international community needs to step forward and make clear that this case, and others like it, are as unacceptable as any other attack on the Ethiopian media. The Zone 9 Bloggers are free, but no more Ethiopians should face the ridiculous accusations simply for caring to protect their own online communications.
Source: Home

New fears for British father kidnapped to Ethiopia

A British father of three who has been held for 16 months in incommunicado detention in Ethiopia has suggested he may die in prison.
Andargarchew 'Andy' Tsesge, whose British partner and children live in London, was abducted at an airport in Yemen in June 2014 and rendered unlawfully to Ethiopia. He spent a year in secret detention, and was subjected to months of ‘interrogations’, before being recently moved to a prison that has previously been described as a ‘gulag.’ Andy is a prominent critic of Ethiopia’s ruling party, and has received an in absentia death sentence on charges relating to his political views. (http://www.ekklesia.co.uk/node/21899)
Since his kidnap, Tsege has been refused access to a lawyer or his family, and has not been charged with any crime or subjected to any form of legal process. Lawyers at the human rights organization Reprieve have been barred from visiting him.
It’s now emerged that Andy Tsege  is afraid that he will soon die; he has asked the British government to ensure that he is buried in England, and told his children to “be brave.” In the comments – made recently during a rare, closely monitored visit by Britain’s ambassador to Ethiopia – Andy also revealed that:
- The Ethiopian authorities have not allowed him outside his cell for months;
- He is an effective ‘ghost prisoner’ – the Ethiopian authorities have not told him what charges or sentence he faces, and he has no prisoner number;
- He has demanded a lawyer, but the request has been refused;
- He has been refused access to an independent doctor, despite illness.
The UN has condemned Mr Tsege’s ordeal and ordered Ethiopia to release him, but the British government – a close ally of Ethiopia – has so far limited itself to requesting proper consular access and ‘due process’ to be followed in his case. Last week, Foreign Office Minister Grant Shapps MP hosted a trade event in London with the Ethiopian Foreign Minister and other officials, promising in his remarks that the UK would stand “shoulder to shoulder” with them. Foreign Secretary Philip Hammond later revealed that he had raised Andy Tsege's case with his Ethiopian counterpart during the visit, but that he had not asked for Andy’s release.
Commenting, Maya Foahead of the death penalty team at Reprieve, said "Andy Tsege is a British father of three who has been subjected to 16 months of abuse at the hands of the Ethiopian authorities – from kidnap to torture to an in absentia death sentence. It is tragic that he now feels the only way he will return home to Britain is in a coffin. Yet instead of demanding Andy’s release from unlawful detention, ministers have been cosying up to the Ethiopians at a special trade event just last week. The Foreign Office must urgently push for his release, so he can return to his partner and children in London before it’s too late.”

ቴድሮስ አድሃኖም የት ናቸው? – አንዳርጋቸው ጽጌ ‹‹በእንግሊዝ ቅበሩኝ ››

ከዳዊት ሰለሞን
የሶስት ልጆች አባት የሆኑት የግንቦት ሰባቱ ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡና ያሉበት ሁኔታ ሳይታወቅ 16 ወራቶች ተቆጥረዋል፤ በወህኒ ቤት እንዳሉም ሊገደሉ እንደሚችሉ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
andargachew new picture
አንዳርጋቸው ይበሩበት የነበረ አውሮፕላን የመን ሰንዓ ማረፉን ተከትሎ ታፍነው ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፈው የተሰጡት በወርሃ ሰኔ 2014 መሆኑ አይዘነጋም፡፡ለአንድ ዓመት ያህል ድብቅ በሆነ እስር ቤት ውስጥ ለወራቶች ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩት አንዲ በቅርቡ ወደ መደበኛ ወህኒ ቤት መዘዋወራቸው ቢነገርም እስካሁን በውል ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም፡፡ይገኙበታል የተባለው የቃሊቲ ወህኒ ቤት ኃላፊዎችም አንዳርጋቸውን ለምስክርነት ጠርቶ ለነበረ ፍርድ ቤት አንዳርጋቸው በወህኒ ቤቱ እንደማይገኙ አስታውቋል፡፡
አንዳርጋቸው በሌሉበት በቀረበባቸው ክስ በሁለት አጋጣሚዎች የእድሜ ልክና የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው መሆኑ አይዘነጋም፡፡እጃቸው ከተያዘበት ወቅት ጀምሮም የአንዳርጋቸው ቤተሰቦች ያቀረቡት የጉብኝት ጥያቄ አልተሳካም፣ጠበቃ ለማቆም የተደረገው ሙከራም እንዲሁ ፣በህግ ፊት እንዲቀርቡ ባለመደረጋቸውም ከዚህ ቀደም የተላለፈባቸውን ፍርድ በምን መንገድ ሊተገብሩት እንዳሰቡ አሳሪዎቻቸው ግልጽ አላደረጉም የእንግሊዙ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሪፕራይቭ ጠበቆቹ አንዳርጋቸውን እንዲጎበኙ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡
አሁን አንዳርጋቸው በቅርቡ ሊገደሉ እንደሚችሉ ስጋት የገባቸው በመሆኑ ለእንግሊዝ መንግስት ‹‹በእንግሊዝ ስርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም እንዲያረጋግጡላቸው ጠይቀዋል፡፡ለንደን ለሚገኙ ልጆቻቸው ባስተላለፉት መልእክትም ‹‹ጎበዞች››እንዲሆኑ መክረዋል፡፡
በቅርቡ በጣም ውስን ለሆኑ ደቂቃዎች በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደርን ያገኙት አንዳርጋቸው ለአምባሳደሩ
–የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለወራት ከወህኒ ቤት ክፍላቸው እንዳይወጡ መከልከላቸውን
–የእስረኛ ቁጥር እንዳልተሰጣቸውን አሳሪዎቻቸው የእስር ምክንያታቸውን ወይም የተወነጀሉበትን ጉዳይ ያልነገሯቸው መሆኑን
–ጠበቃ ለማግኘት ጠይቀው መከልከላቸውን
— በህመም ላይ የሚገኙ ቢሆንም ህክምና እንዳያገኙ መደረጋቸውን
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአንዳርጋቸውን ኢሰብአዊ አያያዝ በመቃወም እንዲለቀቅ ጠይቋል፡፡የእንግሊዝ መንግስት ግን ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት አጋርና አንዳርጋቸው ዜጋው ቢሆኑም በቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኙና መደበኛ የሆነ ክስ እንዲመሰረትባቸው አልጠየቀም፡፡ባሳለፍነው ሳምንት የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ግራንት ሻፕስ የኢትዮጵያ መንግስት አቻቸውንና ሌሎች ባለስልጣናት ወደ ለንደን በመጋበዝ የንግድ ልውውጥ ስለሚደረግበት ሁኔታ መክረዋል፡፡
በሁለትዮሽ ግኑኝነቱ ወቅት ሻፕስ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነቱ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋና ጸሐፊ ፊሊፕ ሃሞንድ ከዝግጅቱ መጠናቀቅ በኋላ ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት የአንዳርጋቸውን ጉዳይ እንዳነሱባቸው ቢናገሩም ከእስር እንዲፈቷቸው ግን አልጠየቁም፡፡
በሪፕራይቭ የሞት ቅጣት ተከራካሪ ቡድን አባል የሆኑት ማያ ፎ ‹‹አንዳርጋቸው የሶስት ልጆች አባትና እንግሊዛዊ ነው፡፡ለ16 ወራት ያህል በኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለእስር ተዳርጎ ቶርቸር ተፈጽሞበታል፡፡በሌለበትም ሞት ተላልፎበታል፡፡ወደ እንግሊዝ የሚመለስበት ብቸኛው መንገድ ስርዓተ ቀብሩ ሲፈጸም እንደሆነ እንደሚሰማው መናገሩ በጣም አስደንጋጭ ነው፡፡አንዳርጋቸው ከህገ ወጥ እስሩ እንዲለቀቅ ከመጠየቅ ይልቅ የእንግሊዝ ሚኒስትሮች ልዩ የንግድ ትርኢት ባሳለፍነው ሳምንት ማዘጋጀታቸው አስገራሚ ነው፡፡ግዜው ሳይዘገይ የእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንዳርጋቸው እንዲለቀቅና በለንደን የሚገኙትን ቤተሰቦቻቸውን እንዲቀላቀሉ በአስቸኳይ መጠየቅና መጫን ይኖርባቸዋል››ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
የኢህአዴጉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም አንዳርጋቸው የአዳማውን አዲስ የፍጥነት መንገድ መጎብኘታቸውንና ላፕ ቶፕ ተሰጥቷቸው መጽሐፍ እየጻፉ እንደሚገኙ ለቪኦኤ በሰጡት አስገራሚ ቃለ ምልልስ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
Source: zehabesha

ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ በሕይወት ይኑሩ አይኑሩ ማረጋገጫ ሊገኝ አልቻለም::



ካለፈው ሳምንት ጀምሮ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ከካሳንቺሱ የደህንነት ምድር ቤት ከሚገኘው እስር ቤት ወደ ደብረዘይት አየር ሃይል እስር ቤት በሌላ ጊዜ በአሮጌው አይሮፕላን ማረፊያ የማሰቃያ ምድር ቤት ወደ ተለያዩ ቦታዎች ሲያንገላቱት ቆይተው በስተመጨረሻ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት አምጥተውት ከነብሰ ገዳዮች ጋር ያሰሩት እና በእንግሊዝ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና በአባቱ የተጎበኘው የነጻነት ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ በሕይወት ይኑር አይኑር ማረጋገጫ የለም ሲሉ ለደህንነት ቢሮ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለዲፕሎማቶች ተናግረዋል::
በወያኔ የማወዛገብ ፖለቲካ ልምዱ ያላቸው የለውጥ ሃይሎች ምናልባት ወያኔ የሃሰት ዜናዎችን በመንዛት የታወቀ ስለሆነ ዲፕሎማቶቹን እና የለውጥ ታጋዮችን ለማሳሳት የፈጠረው ዜና ነው ቢሉም ታጋይ አንዳርጋቸው ከቃሊቲ እስር ቤት በለሊት መወሰዱ እና መመለሱን ከሁለት ሳምንት በፊት ጉዳዩን አይተናል ያሉ ምንጮች ተናግረው ነበር::ሆኖም ከነብሰ ገዳዮች ጋር ያሰሩት ለነብሰ ገዳዮች የሰጡት የግድያ ተልእኮ አስፈጽመውበት እንዳይሆን ያሰጋል የሚሉ ቢኖሩን እስካሁን ግን በሕይወት ይኑር አይኑር አልታወቀም የሚሉ መረጃዎች በርክተዋል::ላለፉት አራት ሳምንታት አንዳርጋቸውን ለመጠየቅ የፈለጉ ዲፕሎማቶችም እንዳልተፈቀደላቸው ምንጮቹ ይናገራሉ::ወያኔ የተቃዋሚዎችን ፕሮፓጋንዳ ለማሳጣት እና በሕዝብ ትዝብት ውስጥ ከቶ አዲስ ዶክመንተሪ ለመስራት ያቀደው እንዳይሆን የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች ሁኔታውን በትእግስት መጠበቅ ይሻላል ሲሉ ይናገራሉ::በአንዳርጋቸው ሞቷል የሚል ዜና የማህበራዊ ድህረገጾች በውስጥ መስመር ተወጥረው በገሃድ ሊፈነዱ ደርሰዋል::ለሁሉም በትእግስት መጠበቅ ነው::
Source: mereja

Monday, October 26, 2015

‘Our Detention Tells a Broader Story About Our Country': Reflections From Ethiopia's Zone9 Bloggers

Zone9 bloggers, together after their release. Photo via Zone9 Facebook page.
Zone9 bloggers, together after their release. Photo via Zone9 Facebook page.
In the wake of their acquittal and release from prison, Ethiopia's Zone9 bloggers reflect on their experience and thank their supporters. The bloggers were arrested in April of 2014 and prosecuted under Ethiopia's Anti-Terrorism Act. Five members of the group were released in July of 2015 and the remaining four were acquitted and released during the week of October 19, 2015. Learn more about their case.
This post was collectively written by Zone9 and translated from Amharic to English byEndalk Chala.
Our release was as surprising as our detention. Five of us were released after our charges were “withdrawn” in July. The remaining four of us were released in October because we were acquitted (save for the appeal against our acquittal). Still one member of our group, Befeqadu, was released on bail and must defend himself later this year in December. Even though we were released in different circumstances, one thing makes all of us similar – our strong belief that we didn’t deserve even a single day of arrest.
Yes, it is good to be released, but we were arrested undeservedly. All we did was write and strive for the rule of law because we want to see the improvement of our country and the lives of its citizens. However, writing and dreaming for the better of our nation got us detained, harassed, tortured and exiled. Undeservedly.
…writing and dreaming for the better of our nation got us detained, harassed, tortured and exiled. Undeservedly.
It makes us happy when we hear people say they are inspired by our story. But it also makes us sad when we learn people are scared to write because they have seen what we have gone through for our writings. Our incarceration makes us experience happiness and grief at the same time. The bottom line is that it is good to know we have inspired people while it is saddening that people have left the public discourse as a result of our detention. It is sad to know that our detention has had a chilling effect on public discourse.
We are victims of institutionalized misconduct. But this does not lie not beyond our ability to forgive. To our incarcerators who gave us those ordeals, even if you are not asking us for forgiveness, here we are.
Our incarceration made us feel our lives pass by us. It is true we have missed and lost things. But we also have increased our learning curve. We have learned a lot. Our detention tells a broader story of our country. We were able to witness the price of freedom of expression is dearly expensive. We are firsthand witnesses of injustice. More than anything, we have learned that a nation which is rampant with injustice is the foremost enemy of its law abiding citizens.
We are victims of institutionalized misconduct. But this does not lie not beyond our ability to forgive. To our incarcerators who gave us those ordeals, even if you are not asking us for our forgiveness, here we are. And please forgive us, for we are law abiding citizens who refuse to live on your terms.
For all people who were with us both in good times and in bad times, those of you who stood by us not only in our successes but also in our failures, YOU are awesome! You are our friends, you are our family, you were our lawyers, you campaigned for us, and you defended our cause. Thank you! Media organizations, rights groups and the entire community who showed solidarity and concerns for our cause. Thank you! You all deserve our heartfelt gratitude for your actions reduced the length of our prison time and eased our boredom while we were in prison.
Source: globalvoices

he Tyranny of the TPLF is sanctioned by the People itself – GK

“The Only real prison is fear, and the only real freedom is freedom from fear.” - Aung San Sun Kyi.
“Repression is not the way to virtue. When people restrain themselves out of fear, their lives are by necessity diminished.” - Mihaly Csiszentmihalyi
Though the regime released few Zone 9 bloggers, still many are unjustly languishing in various notorious prisons all over the country. Eskinder Nega, Temesgen Desalegn, Andwalem Arage, Habtamu Ayalew, Abraha Desta, Negist Wondafraw, Sintayehu Checkol, Olban lelessa , Zemene Mihret….the list goes on and on.
Why does the EPRDF continue incarcerating and denying justice to our fellow Ethiopians? The answer is simple; it is because the people allowed it.
Ethiopia is equal for all Ethiopians. There is no reason why one would pay more sacrifice than others. It is wrong to expect freedom by the efforts of the very few only. It is very crucial that the rest of us would come out from our closets and start to be counted on. It is time to speak out and assert our freedom in our country. We are all created in the image and likeness of God. God has given us a country called Ethiopia. He has given us the right to live in peace and dignity in it. The EPRDF must not be allowed to continue taking away from us, our rights and our dignities, that God gave us and are only ours.
Let our silence end. We may not have supported the EPRDF. We may not have directly contributed to the incarceration of prisoners of conscience However, our silence is the reason many peaceful political activists, journalists and human right activists are still in jail. Our silence is providing bullets to EPRDF forces.
In every struggle there are ups and downs. Some may say, "It is impossible to force change in the EPRDF". Our effort may be seen as meaningless. On the surface the peaceful struggle may seem to be "vanished". HOWEVER, WE SHOULD NEVER GIVE UP.
It is in this context that I call for a renewal of spirit. Instead of being filled with fear and despair we should learn to believe in ourselves. What is man without freedom? A life lived in fear and despair is no better than death. A life lived without a purpose is a tragedy. A man who only thinks of himself and forgets where he came from, is a man who is spiritually weak.
As is the case with Zone 9ers, It is my hope that all other prisoners of conscience would be unconditionally released soon. However, should the EPRDF refuses to listen to the people and says no to peace and reconciliation, Ethiopians must be ready to show what PEOPLE’S POWER is all about.
Tyrants are holding us by our neck by making us fear them. The day we break our fear , would be the day the regime would listen the will of the people. The Oppression of the regime is sanctioned by the People itself, for without the approval of the People , the regime would not have done what it has been doing; and the People has given sanctioned tyranny by its silence and fear.
A fellow Ethiopian so discouraged by events in Ethiopia recently said to me that Ethiopia is cursed. Yes on the surface it may look like we are cursed. However, Ethiopia is not cursed. Ethiopia has “US”. If we stop being selfish and prepare ourselves to pay a little sacrifice we can turn around the fate of our country. With the help of the Almighty God we shall overcome.
The following are few of prisoners of conscience languishing in jails. (W/r Emmawayesh, Ato Alene Matsentu, Ato Eyassu Hussen and Aster Seyoum)

Sunday, October 25, 2015

የሕወሃት ስታይል

"TPLF style " ይሉታል፣ በትግራይ አስተዳደር ያለውን በጣም አስቂኝ እና አሳፋሪ ሁኔታ፣ የለዉጥ ኃይሉ አንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ የነበሩት፣ አቶ አስራት አብርሃ ።
አባይ ወልዱ የትግራይ ክልል ፕሬዘዳንት ናቸው። በትግራት አስተዳደር የሚሰራዉን ግፍና ወንጀል፣ ሙስና፣ የገንዘብ ዘረፋ ..ለመቆጣጠር የትግራይ ክልል የጸረ-ሙስና ጽ/ቤት አለው። የዚህ ጽ/ቤት ሃላፊ ሆነው እንዲሰሩ የተደረጉት፣ ወ/ሮ ትርፊ ኪዳነ ማሪያም ይባላሉ። ወ/ሮ ትርፉ የሕግ ባለሞያ፣ ገለልተኛ አስተሳሰብ ያላቸው፣ ለቦታው ብቁ የሆኑ ሰው አልነበረሙ። ወይዘሮዋ፣ የአቶ አባይ ወልዱ ሚስት ናቸው።
"ጥሩ ነው አልጋ ላይ ጭምር ትቆጣጠሯለች!! " ሲል አስራት አብራሃ ምን ያህል በአገራችን ያለው የፖለቲክ ስርዓት አሳፋሪ መሆኑን ይገልጻል።
ወይዘሮ ኪዳነማሪያም በትግራይ የጸረ-ሙስና ሃላፊ ብቻ አይደለኡም። ከባለቤታቸው ከአቶ አባይ ወልዱ ጋር የሕወሃት ፖሊት ቢሮ አባል ናቸው።