Friday, January 31, 2014

ወያኔን ያሸበረው የግንቦት 7 መንገድ ምንድነው?

ወያኔን ያሸበረው የግንቦት 7 መንገድ 

ምንድነው? 

የትግራይን ሕዝብ ከብሄር ጭቆና ነጻ አወጣለሁ በሚል ጠባብ ዓላማ ተደራጅቶና ታጥቆ ለበትረ ሥልጣን የበቃው ህወሃት ወይም ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥልጣን ከተቆጣጠረ 23 አመት ሊሞላው እነሆ ጥቂት ወራቶች ብቻ ቀርተውታል።
ለጋራ ቤታችን ለሆነቺው አገራችን ኢትዮጵያና በአስተዳደር በደል ለከፋ ድህነት ለተዳረገው መላው ሕዝቦቿ የሚሆን አንዳችም ራዕይ ሳይኖረው ለመንግሥትነት ሥልጣን የበቃው ይህ ቡድን ላለፉት 23 ዓመታት ከግል ኑሮአቸው አሻግረው የአገርንና የወገንን ጥቅም ማየት የማይችሉ ወይም የማይፈልጉትን በዙሪያው አሰባስቦ እያካሄደ ካለው ዘርፈ ብዙ የሃብት ምዝበራ ወንጀል በተጨማሪ እየፈጸመ ያለው የመብት ጥሰትና አፈና ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም።
ሰሞኑን እያፈተለኩ በመውጣት ላይ ከሚገኙ ምስጥራዊ የድምጽ መረጃዎች ለማረጋገጥ እንደተቻለው ደግሞ ለጥቂቶች የሃብትና የብልጽግና ምንጭ የሆነው ሥልጣን ከእጃቸው እንዳይወጣ በአንድ በኩል በምርጫ ስም እንዴት አድርገው ሕዝቡን ቀፍድደው የምርጫው ተሳታፊ ማድረግ እንደሚችሉ ሲዶልቱና በሌላ በኩል ደግሞ በቁጥጥራቸው ሥር የሌሉትንና ለሥልጣናቸው ያሰጉናል ያሉዋቸውን የደሃዉን ልጅ በማጋፈጥ እንዴት በጦርነት እንደሚጨፈልቁዋቸው ሲመክሩ ተሰምተዋል።
ከወያኔው ቁንጮ አንዱ የሆነው በረከት ስሞን በየደረጃው ላሉት የአገዛዙ ሹሞችና ካድሬዎች ባደረገው ገለፃ መሬትን የመንግሥት ባደረገው ኮሚኒስታዊ አዋጅ ምክንያት የመንግሥት ጭሰኛ ለመሆን የተፈረደበትን ሰፊውን አርሶ አደር “ተኛ ስንለው ይተኛል፤ ቁም ስንለው ይቆማል ፤ እንደፈለግን ብንበድለው እንኳ አያማርረንም ” እያለ ሲዘባበትበት ተደምጦአል ። በአንድ ለአምስት ኮሚንስታዊ አደረጃጀት ተጠርንፎ የወያኔ የንግድ ድርጅቶች ብቻ የሚያቀርቡትን ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ያለውዴታው እንዲራገፍበትና ከአቅሙ በላይ ዕዳ እንዲቀፈቅፍ የተፈረደበት የኢትዮጵያ አርሶ አደር በዚህ አይነት ንቀት ደረጃ የሚዘባበትበትን መሪ ከወያኔው በረከት ስሞን በፊት ገጥሞት አያውቅም ። ለወደፊትም ሊያይ አይፈልግም ። ወያኔን ሥልጣን ላይ ለማምጣት የሰሜኑ ክፍለአገራችን አርሶ አደር የተጫወተው ሚና ተዘንግቶ በበረከት ስሞን እንዲህ መዋረዱ እጅግ ያሳዝናል። ለነገሩ ከፍተኛ የህይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ለድል ያበቃው የትግራይ ሕዝብ ቁም ስቅሉን እያየ አይደል?
ሌላው አስገራሚ ክስተት በአገር ደህንነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ባደረጉት ዝግ ስብሰባ ታማኝነታችን ለአገራችን ነው ወይስ የሥርዓቱን አገዛዝ ዕድሜ ለማራዘም? ብለው ላነሱት ጥያቄ የጠቅላይ ሚንስትር ተብዬው የህግ አማካሪ ጌታቸው ረዳ የሰጠው መልስ ነው። ደህንነት ብቻ ሳይሆን የመከላኪያ ሠራዊትና ፖሊስ ጭማር ታማኝነታቸውና ግዴታቸው ሥርዓቱን ሥልጣን ላይ ማቆየት መሆን አለበት ሲል ጌታቸው እንቅቹን ነግሮአቸዋል ። በምላሹ “ላለፉት 23 አመታት እያደረግነው ያለው ይሄው ሆኖ ሳለ አሁን ምን ብታስቡ ነው ጥያቄ ያነሳችሁ?” የሚል ይመስላል ። ይባስ ብሎም ሥርአቱን ለመጠበቅ ያልቻለና በግንቦት 7 መንገድ የሚጓዝ ደህንነት ሠራተኛ የተስፋየ ገብረስላሴን ያህል የደህንነት እውቀት ቢኖረውም ሆነ እስራኤል አገር የዓመታት ስልጠና ያገኘ ቢሆን ዋጋ የለውም ብሏቸዋል።
ለመሆኑ ወያኔዎች እንደመርገም የቆጠሩትና ተከታዮቻቸውን የሚያስፈራሩበት የግንቦት 7 መንገድ ምንድ ነው።?
ግንቦት 7 የፍትህና፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራችን ኢትዮጵያ የእያንዳንዱ ዜጋ ዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት የተከበረባት፤ የኢኮኖሚ ብልፅግናና ማኅበራዊ ፍትህ የሰፈነባት ፤ የዜጎች ሕይወት፣ ደህንነትና ጥቅም የተከበረባት እና የሕዝቧ አንድነትና ትስስር የጠነከረባት ሃገር ሆና ማየትን ብቸኛ ራዕይ አድርጎ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ ድርጅት ነው። ይህንን ራዕይ እውን ለማድረግ ደግሞ እስከ ዛሬ በጠመንጃ ኃይልና በጉልበተኖች ጡንቻ ከአንዱ ወደሌላው የሚፈራረቀው የመንግሥት ና የፖለቲካ ሥልጣን በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት የሚያዝበትን ፤ የሃገሪቱ ዜጎች ምርጫ በተግባር የሚገለፅበት፤ ማኅበራዊና የፖለቲካ ችግሮች በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚፈቱበት እና ዲሞክራሲያዊ ባህል የሚበለፅግበት ብሄራዊ የፖለቲካዊ ሥርዓት መገንባት አማራጭ የሌለው ነው ብሎ ያምናል።
ይህ ደግሞ ያለምክንያት አይደለም። ወያኔ የዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ በሩን ከፈት አድርጎ በነበረበት ምርጫ 97 ወቅት ከተገኘው ልምድና ከተመዘገበው ውጤት ሕዝባችን በአምባገነኖችና በከፋፋዮች ለመገዛት አለመፈለጉን በግልጽ አስመስክሮአል።
ንቅናቄያችን ግንቦት 7 ሕዝባችን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በነቂስ ወጥቶ መሪዎቹን የመረጠበትንና ድሉን የተነጠቀመበትን ታሪካዊ የግንቦት 7 1997ን ቀን ምን ጊዜም አይረሳም። መጠሪያ ስሙንም በዚያ ታሪካዊ ቀን የሰየመው ሕዝብ የተነጠቀውን ድል በማስመለስ ፍትህ የሰፈነባት፤ የበለጸገችና የተከበረች አገር ባለቤት እንሆን ዘንድ ነው። ሁላችንም አትራፊ እንጂ ተጎጂ ለማንሆንበት ለዚህ ቅን አለማና ራዕይ ደንቃራ ሆኖ የተገኘው ወያኔና ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ከወያኔ ጋር የተጣበቁ አንዳንድ ባዕዳን አገሮች ናቸው።
ወያኔ የግንቦት 7 መንገድ የሚለው ለዚህ ክቡር ዓላማ ሲባል እንቅፋት የሆነውን ሥርዓቱን በሁለ- ገብ ትግል አስገድዶ ለሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር አካል ማድረግ ካልተቻለ ደግሞ በተባበረ ትግል አስወግዶ በምትኩ በሕዝብ ለሕዝብ ከሕዝብ የሚመጣ ሰላማዊ የመንግሥት ሥርዓት መመሥረትን ነው። ይህንን የተቀደስ አላማ ለማክሸፍና የተጀመረውን ትግል ለመጨፍለቅ ሲባልም ወደ ሥልጣን ለመምጣት በጦርነት ማግዶ ካስጨረሳቸው የደሃ ልጆች በእጥፍ የሚበልጡትን መልምሎ በጸረ ሽምቅ ውጊያ ከማሰልጠን ጎን ለጎን ለግንባታ ቢውል ስንት ፋይዳ ሊያስገኝ ይችል የነበረ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ተቃዋሚ ድርጅቶችን ድምጽ ለማፈንና ለመሰለል እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ለአገራችን ሉአላዊነት ጠቀሜታው እስከዛሬ ምንም ባልታወቀ ጦርነት ወደ መቶ ሺ የሚጠጉትን ያስጨፈጨፈ፤ የተልዕኮ ጦርነት ለማካሄድ በመንግሥት አልባዋ ጎረቤት ሱማሌ እስከዛሬ ቁጥራቸው ያልተገለጸ ወገን ያስፈጀ ፤ ለሥራ ፍለጋ ውትድርና የገቡትን ወጣቶች ለይቶ በሰላም አስከባሪ ስም በድንበር ዘለል ጦርነቶች እየማገደ ገንዘብ የሚቀበል፤ ስለአገርና ስለወገን ምን ሊገደው ይችላል?
ትናንት ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት የቀደምቶቹ መንግስታት ልጆቻቸውን ለትምህረት ወደ ፈረንጅ አገር እየላኩ የደሃውን ልጅ በጦርነት ይማግዳሉ በማለት በጅምላ ሲከስ የኖረ ዛሬ በተራቸው ልጆቻቸውን ብቻ ሳይሆን ዘርማንዘሮቻቸውን ታይቶ በማይታወቅ ብዛት ወደ ፈረንጅ አገር ለትምህርት እየላኩ ለነጻነታችንና ለክብራችን የምንታገለውን እርስ በርስ ለማጨራረስ ሲዶልቱ ዝም ብሎ መመልከት ከየትኛውም ቅን ዜጋ የሚጠበቅ አይሆንም።
ስለሆነም የበላይ አዛዦቻቸው በሚሰርቁት የሕዝብ ገንዘብ ፎቅ ላይ ፎቅ እየገነቡ ሃብት በሚያካብቱት አገር ሠራዊቱን እረፍት ለመንሳት ሆን ተብለው በሚቀሰቂሱት ግጭቶች ከአንዱ ማዕዘን ወደ ሌላው ማዕዘን ያለ ዕረፍት እየተንከራተተ ያለው የመከላኪያ ሠራዊት ፤ የፖሊስና የደህንነት ኃይል ለአገዛዙ አልታዘዝም በማለት ተገዶ ሥልጣን ለሕዝብ እንዲያስረክብ የማድረግ ወገናዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ግንቦት 7 የፍትህ የነትጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪውን ያቀርባል።
የግንቦት 7 መንገድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት የተጠማውን ፍትህ እኩልነትና ነጻነት በአገራችን ለማስፈን አሁን ሥልጣን ላይ ያለው የጎጠኞችና የዘራፊዎች ስብስብ በማስገደድ ወይም በማስወገድ ሰላማዊ ህጋዊና ዲሞክራሲያዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር ማድረግ ነው። ይህንን ደግሞ የሚፈሩት በሥልጣን ቱርፋትና በሃብት ዘረፋ የሰከሩ ብቻ ናቸው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

    Wednesday, January 29, 2014

    Ethiopia – Land for Sale – aljazeera

    Ethiopia – Land for Sale – aljazeera


    As the economy thrives, we examine the plight of Ethiopians forced from their land to make way for foreign investors.

    NGO’s and policy advocates say the true consequences of the land grabs are almost all negative [Reuters]
    Just a few decades ago, Ethiopia was a country defined by its famines, particularly between 1983-1985 when in excess of half a million people starved to death as a consequence of drought, crop failure and a brutal civil war.
    Against this backdrop, it is impressive that in recent years, Ethiopia has been experiencing stellar economic growth. The headline statistics are certainly remarkable: the country is creating millionaires faster than any other in Africa; output from farming, Ethiopia’s dominant industry, has tripled in a decade; the capital Addis Ababa is experiencing a massive construction boom; and the last six years have seen the nation’s GDP grow by a staggering 108 percent.
    But it is not all positive news, because for all the good figures there are still plenty of bad ones.
    Around 90 percent of the population of 87 million still suffers from numerous deprivations, ranging from insufficient access to education to inadequate health care; average incomes are still well below $1500 a year; and more than 30 million people still face chronic food shortages.
    And while there are a number of positive and genuine reasons for the growth spurt – business and legislative reforms, more professional governance, the achievements of a thriving service sector – many critics say that the growth seen in agriculture, which accounts for almost half of Ethiopia’s economic activity and a great deal of its recent success, is actually being driven by an out of control ‘land grab’, as  multinational companies and private speculators vie to lease millions of acres of the country’s most fertile territory from the government at bargain basement prices.
    At the ministry of agriculture in Addis Ababa, this land-lease programme is often described as a “win-win” because it brings in new technologies and employment and, supposedly, makes it easier to improve health care, education and other services in rural areas.
    “Ethiopia needs to develop to fight poverty, increase food supplies and improve livelihoods and is doing so in a sustainable way,” said one official.
    But according to a host of NGO’s and policy advocates, including Oxfam, Human Rights Watch and the Oakland Institute, the true consequences of the land grabs are almost all negative. They say that in order to make such huge areas available for foreign investors to grow foodstuffs and bio-fuels for export – and in direct contravention of Ethiopia’s obligations under international law – the authorities are displacing hundreds of thousands of indigenous peoples, abusing their human rights, destroying their traditions, trashing the environment, and making them more dependent on food aid  than ever before.
    “The benefits for the local populations are very little,” said renowned Ethiopian sociologist Dessalegn Rahmato. “They’ve taken away their land. They’ve taken away their natural resource, because these investors are clearing the land, destroying the forest, cutting down the trees. The government claims that one of the aims of this investment was to enable local areas to benefit by investing in infrastructure, social services … but these benefits are not included in the contract. It’s only left up to the magnanimity of the investor.”
    And those investors, he continued, are simply not interested in anything other than serving their own needs: “They can grow any crop they want, when they want it, they can sell in any market they want, whether it’s a global market or a local market. In fact most of them are not interested in the local markets.”
    He cited as an example a massive Saudi-owned plantation in the fertile Gambella region of south west Ethiopia, a prime target area for investors: “They have 10,000 hectares and they are producing rice. This rice is going to be exported to the Middle East, to Saudi Arabia and other places. The local people in that area don’t eat rice.”
    But the most controversial element of the government’s programme is known as ‘villagisation’ – the displacement of people from land they have occupied for generations and their subsequent resettlement in artificial communities.
    In Gambella, where two ethnic groups, the Anuaks and the Nuers, predominate, it has meant tens of thousands of people have been forced to abandon a traditional way of life. One such is Moot, an Anuak farmer who now lives in a government village far from his home.
    “When investors showed up, we were told to pack up our things and to go to the village. If we had decided not to go, they would have destroyed our crops, our houses and our belongings. We couldn’t even claim compensation because the government decided that those lands belonged to the investors. We were scared … if you get upset and say that someone stole your land, you are put in prison. If you complain about being arrested, they will kill you. It’s not our land anymore; we have been deprived of our rights.”
    Despite growing internal opposition and international criticism, the Ethiopian government shows no sign of scaling the programme back. According to the Oakland Institute, since 2008, an area the size of France has already been handed over to foreign corporations. Over the next few years an area twice that size is thought to be earmarked for leasing to investors.
    So what does all this mean for the people on the ground? In Ethiopia – Land for Sale, filmmakers Veronique Mauduy and Romain Pelleray try and find out.
    People & Power can be seen each week at the following times GMT: Wednesday: 2230; Thursday: 0930; Friday: 0330; Saturday: 1630; Sunday: 2230; Monday: 0930.
    Click here for more  People & Power
    Source:
    Al Jazeera

    ESAT Breaking News - Privacy International reveals Ethiopian government spying on Ginbot 7 leaders' PCs | Jan. 29, 2014

    ESAT Breaking News - Privacy International reveals Ethiopian government spying on Ginbot 7 leaders' PCs | Jan. 29, 2014




    "የኢትዮጵያ መንግስት በግንቦት 7 አመራሮች ኮምፒውተሮች ላይ ስለላ ሲያካሂድ፣Privacy International የተባለ 

    አለማቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት እንደደረሰበት አስታወቀ።" ሲል ኢሳት ቴሌቪዥን ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው 

    ሰበር ዜና አስታወቀ። | Privacy International reveals Ethiopian government spying on Ginbot 7 

    leaders' PCs - ESAT Breaking News

    ጥር ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህዝቦችን ደህንነት ከመንግስታት ጥቃት ለመከላከል 

    የተቋቋመው ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም ለእንግሊዝ መንግስት የገቢዎቸና ጉምሩክ መስሪያ ቤት 

    በጻፈው ደብዳቤ “ጋማ ኢንተርናሽናል የተባለው የእንግሊዝ ኩባንያ በአለም ላይ የሰብአዊ መብቶችን በመጣስ 

    ለሚታወቁ አገሮች ኮምፒይተሮችን፣ የሞባይልና የስካይፕ የስልክ ግንኙነቶችን እንዲሁም የኢሜል ልውውጦችን 

    በርቀት ሆኖ ለመከታተል የሚያስችለውን ፊን ፊሸር ወይም ፊን ስፓይ በሚል ስም የሚጠራውን የመሰለያ መሳሪያ 

    ከአውሮፓ ህብረት ውጭ ላሉ አገሮች በመሸጥ ዜጎች እንዲሰለሉና ደህንነታቸው አደጋ ላይ እንዲወድቅ በማድረጉ 

    ምርመራ እንዲጀመር” ሲል ጠይቋል።

    የግንቦት7 ከፍተኛ አመራር በሆኑት በ ዶ/ር ታደሰ ብሩ የግል ኮምፒዩተር ላይ የመሰለያ ቫይረሱ መገኘቱን በቶሮንቶ 


    ዩኒቨርስቲ የሙንክ ስኩል ግሎባል አፌርስ የምርምር ተቋም የሆነው ሲትዝን ላብ ማረጋገጡን ፕራይቬሲ 

    ኢንተርናሽናል በደብዳቤው ገልጿል።

    የመሰለያ መሳሪያው የሰብአዊ መብቶችን በሚጥሱ 36 አገራት ላይ መሸጡን የገለጸው ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል፣ 


    በተለይም በቬትናም፣ ማሌዚያና ኢትዮጵያ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን ለመሰለያነት እየዋለ ነው ብሎአል።


    በኢትዮጵያ የግንቦት7 ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር ታደሰ ብሩ ኮምፒተራቸው ሲሰለል መቆየቱን የገለጸው 


    ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል፣ በአንድ የብሃሬን የሰብአዊ መብት ተማጓች ኮምፒዩተር ላይም ተመሳሳይ የስለላ ሶፍት 

    ዌር መገኘቱን ገልጿል።

    ዶ/ር ታደሰ ብሩ ለፕራይቪሴ ኢንተርናሽናል ጠበቃ የምስክርነት ቃላቸውን መስጠታቸውን ተናግረዋል። ፕራይቪሲ 


    ኢንተርናሽናል የስለላ ቫይረሱን የሸጠውን ጋማ ኢንተርናሽናልን የተባለውን ድርጅት ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ 

    ማቀዱን ዶ/ር ታደሰ ገልጸዋል፡

    ከዶ/ር ታደሰ ጋር የተደረገው ቃለምልልስ ከዜናው በሁዋላ ይቀርባል።

    የታመቀው የኢትዮጵያውያን ምሬት፡ የሕይወት ማሽቆልቆልና በፍርሃት መሽማቀቅ አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል

    የታመቀው የኢትዮጵያውያን ምሬት፡ የሕይወት ማሽቆልቆልና በፍርሃት መሽማቀቅ አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል


    ኢትዮጵያ በሕወሃት ዘመነ አመራር የታወቀችባቸው ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። ብዙ “እንዴ!”የሚይሰኙ ጥሩ አሳቦችም ፈልቀዋል – አፈጻጸማቸው እትይለሌ ቢሆንም። ከነዚህም መካከል መሠረተ ልማት፡ በጤናና በትምህርት መስኮች መሻሻሎች መታየታቸው ወዘተ መልካም ይነገርላቸዋል – የቢል ጌትስን የራስ ተጠቃሚነትና ኢምፓየር ግንባታ ወደጎን ትተን! በዕጦት ደረጃም በሀገራችን የስብዓዊ መብቶች አለመክበር፣ የፍትህ አለመኖርና ለአብዛኛው ሕዝባችን የምግብ ዕጦት ዋና ዋና ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው።
    Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
    Prime Ministers Katainen and Hailemariam (Credit: ERTA)
    ለምሳሌም ያህል፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 30 ስላማዊ ስልፍ የማድረግንና መንግስትን መቃወምን ግልጽ ቢያደርግም፡ እሁድ ዕለት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመሰጠት ለመቃወም: ለሚመለተው አሳውቀው ስላማዊ ስልፍ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ሲሉ የአዘጋጁ የስማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት ጎንደር ውስጥ ተይዘው ታስረዋል። በተመሳሳይ መንገድ ትግራይ ውስጥም የአረና አመራሮች ሕዝቡን ቀሰቀሳችሁ በሚል ውንጀላ አዲግራት ውስጥ አመራሩና አባሎቹ ክፉኛ ተደብድበዋል – ጉዳት የደረሰባቸውም ሕክምና ለመሻት ተገደዋል። ይህንኑ አስመልክቶ፡ አንዱ ተደብዳቢ መምህር አብርሃ ደስታ የሚከተለውን ጽፏል፡
      “ህወሓቶች በተግባራቸው ሊያዝኑ ይገባል። ህዝብን ፖለቲካ እንዲያውቅና ራሱ ከጭቆና እንዲከላከል ለማገዝ በምንሞክርበት ግዜ መንግስት ወደ ተራ የሽፍትነት ተግባር መሰማራቱ የሚያስደምም ነው … እኛ ለህዝብ ነፃነት ነው የምንታገለው። ትግላችን ሰለማዊ ነው። ወታደርና ፖሊስም የለንም። እኛ ያለን ህይወት ነው። ያለችንን ህይወት ለህዝብ ደህንነት ስንል መስዋእት አድርገናል። በህዝብ ፊት ተደብድበናል። በፖሊስና አስተዳዳሪዎች ፊት ተደብድበናል። እኛ መክፈል ያለብን ህይወትን ነው።”
    ይህ በግልጽ የሚታየው የዛሬይቱ ኢትዮጵያ የስብዓዊ መብቶች አንጸባራቂ ሥዕል ነው። ይህ ሁኔታ በየቀኑ በተለያየ መልኩ ሀግሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለ የመንግሥት ሕገ ወጥነት ነው!
    በኤኮኖሚው መስክ ያለው ችግር ግዙፍ ነው። ድህነት ከመቀረፍ ይልቅ፡ ሥር እየስደደ መሆኑን ብዙዎች ያማርራሉ። ለጥቂቶች ግን ሀገሪቱ ምድራዊ ገነት ሆናለች። ሕዝቡ እየተደበደበም፡ በየቀኑ አልዋጥ ባይ ፕሮፓጋንዳ በግድ እየተጋተ ነው!
    በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው ለብዙዎቹ የአዲስ አበባ መሽቀርቀር እንደአጠቃላይ የሃገሪቱ የልማትና ዕድገት መለኪያ ተደርጎ እንዲወሰድ የተቀነባበረ ጥረት የሚድረገው። የምርጫ ዘመን በመቃረቡ፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በቅርቡ ስንዴ ለውጭ ገብያ ሻጭ ልትሆን ነው በማለት ጥር 18፣ 2014 አርሲ ሆነው ማስማታቸው ልብ ሊባል ይገባል። ነገር ግን ኢትዮጵያ በልማት ገና ሀ ሁ … ላይ ናት – በምግብ 40 በመቶ የሚሆነውን ሕዝቧን በቀን ሶስቴ ሳይሆን፡ አንዴም መመገብ ያልቻለች አገር ናት! ይህ በመሆኑ አይደል እንዴ የምዕራቡ ዓለም፡ በቋሚነት ከ10 በመቶ በላይ የሆነውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ክዓመት ዓመት በዓለም አቀፍ እህል ዕርዳታ ሕይወት በመስጠት ላይ ያለው?
    ከሁሉም ጎልቶ የሚነገርለትና የሕወሃት ስዎችም ቶሎ የሚስፈነጠሩበት የአገሪቱ ከትላልቅ ጦርነቶች መላቀቋ ነው። ስለዚህም የሕወሃት ስዎችና ደጋፊዎቻቸው በመመጻደቅ ሲናገሩ መስማቱ የተለመደ ሆኖአል። በዚህም መነሻነት፡ እንዲህ ይላሉ: ባለፉት 20 ዓመታት፡ ሕወሃት ለረዥም ዘመናት አገሪቱን ያደሙትን ጦርነቶች አቁሞ ልማት ላይ እንድታተኩር አደረገ የሚባለው በብዛት ይሰማል። የሕወሃት ስዎችም ይህ በተደጋጋሚ እንዲነገርላቸው ብዙ ጥረቶች አድርገዋል፡ እያደረጉም ነው። እራሳቸውም በተደጋጋሚ እራሳቸውን በዚህ ሲያሞካሹ ይሰማል፤ ለውጭ የፕሮፓጋንዳ ድርጅቶችም ይህንን እንዲያስተጋቡላቸው፡ ከፍተኛ ክፍያዎችን በየጊዜው ፈጽመዋል።
    እስከዛሬ አጥግቢ ግንዛቤ ያላገኘው ግን፡ ድሮም ሆነ ዛሬ የጦርነቶች አጋጋይ ሕወሃት መሆኑ ነው። የኤርትራንና የትግራይን መገንጠል ጉዞ በተግባር ሲተረጉም ኖረ። ቀኑ ደርሶ ጅብሃ ሲገነጠል፡ ሕወሃት ባዶ የሥልጣን ወንበር ስለታየው፡ ኢትዮጵያዊነትን መረጠ። በትግል አጋሩ ጅብሃ ዘንድ ይህ እንደክህደት እንዳይታበት – በስላም ሂዱ፡ ኢትዮጵያ ከእናነተ ስላም እንጂ ሌላው ቀርቶ የባህር በር እንኳ አያስፈልጋትም አለ። ይህንን አስመልከቶ፡ በየካቲት ወር 1994 ስብሃት ነጋ ለዓለምስገድ አባይ በስጡት ቃለ መጠይቅ የሕወሃት ቀደምት ፓሊሲ መገንጠል ሆኖ እስክ 1985 መቆየቱን ያረጋግጣሉ። ከቃለ መጠይቁ ውስጥ በጣም አሰገራሚው ነገር ግን፡ ብዙ የሕወሃት ተዋጊዎች ኢትዮጵያዊነትን ገና ድሮ አሽቀንጥርረው የጣሉ በምሆናቸው፡ ዛሬም ቢሆን በተለይ ከአማራ ጋር ኢትዮጵያዊ ሆኖ መገኝትን በሙል ልብ አለመቀበላቸውን ነው ያመላከቱት [See Identity Jilted: Re-imagined Identity (1998)]።
    ያለፈው አልበቃ ብሎ፡ ዛሬም ሕወሃት ሀገሪቱ ውስጥ ሽብርና ፍርሃት በማንገስ የውስጥ ግጭቶችን በመተንኮስ: የተለያዩ ብሄረስቦችን አባሎች በማፈናቀልና ችግሮችን በማባባስ ተጠቃሚ ለመሆን ሲምክር ይታያል – ድ/ር ቴድሮስ ፍጹም “እኔ ያለሁበት ፓርቲ ውስጥ ይህ አይደረግም!” ብለው ዝናቸውን አጋልጠው ቢገዘቱም። ነገሩ ግን፡ ዛሬም በምሥራቅ በተለያያዩ የኦሮም ክፍሎችና ኢትዮጵያውያን ሶማሌዎች መካከል፡ በደቡብም እንዲሁ በተለያዩ ጎሣዎች መካከል፡ አማራንና ኦርሞችን በማጋጭት፡ ጥላቻና መቃቃርን በዜጎች መካከል ለመፍጠር ብዙ ሲሞክር ቆይቷል። አንዳንድ ቦታዎችም፡ ለምሳሌ ቦረና፡ ተሳክቶለት ስሞኑን የብዙ ዜጎች ደም ፈሷል፤ ሕይወትም ተቀጥፏል። ቤት ንብረቶችም ተደምስሰዋል። ሌላው ቀርቶ፡ የሕክምና ባለሙያ የነበሩት የአገር አስተዳደር ሚኒስትሩ – የዛሬው የሃይማኖትች ጉዳይና የጸረሽብር ኤክስፐርቱ ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም – ኬንያ በሥጋቷ ምክንያት (2012ን በማስታወስ) ልተቀስቅሳቸው ብትሞክርም፡ ነገሩ አውቆ የተኛ ቢነቀንቁት አይሰማ ሆኖ እሳችውም እንደክረምት ድብ ክፉኛ አሸልበዋል።
    ለማንኛውም፡ በዓለም ላይ እንደሕወሃት የተሳካለት የለም – ዕድሉን ሃገራችንን ለማሻሻል በሚገባ አልተጠቀመበትም እንጂ! ስለሆነም ክሥራ ይልቅ ፕሮፓጋንዳ፡ ዕውነትን ተናግሮ ችግሮችን በጋራ ከመፍታት ይልቅ፡ ሁሉንም ስው ማሞኘት እንችላለን በሚል ትዕቢት ብዙ የሚያሳፍሩ ተግባሮች ሲያከናወን ይታያል።
    ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ በበጎነታችው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደጉን የሚመኙ የውጭዎቹ የፖለቲካ፡ የዲፕሎማሲና ኅብረተስባዊ መሻሻሎችን አራማጆች ይህንን የሕውሃትን የሰላም ማስፈን የዋህ መስል ቅጽል በአመኔታ የሚጋሩት በሁለት ተክፈለው ይታያሉ፡ –
    (ሀ) በእውነትም ጦርነትና የንጹሃን ዕልቂት መቆሙን፡ ኢትዮጵያ ክድህነት ተላቅቃ ማየት የሚሹ ወገኖች፤
    (ለ) ጊዘው የበለጸጉት ሃገሮች ወደታዳጊ ሀገሮች ውስጥ ዘልቀው በመስፋፋትና በኢኮኖሚ ትብብር ስም የራሳቸውን ኤኮኖሚያዊ፡ የበላይነት ማቆየት የሚሹበት፡ ፖለቲካዊና ስትራተጂካዊ ጥቅሞቻቸውን የሚያበራክቱበት በመሆኑ፡ ከላይ ከተጠቀሱት ጋር ተዳብረው፡ የሕወሃትን ገድል መተረኩ፡ ለሚሹት ዓላማ አንድ ጥቅም ትስስሮሽ መፍጠር የሚያስችል መሣሪያ አድርገው የሚጠቀሙበት ወገኖችም እዚሀ ውስጥ ተስልፈዋል።
    ከላይ የተመለከቱት ከተለያየ አግጣጫ ተነስተው ሁለቱም አንድ የሚገናኙበት መጋጠሚያ፡ ስለኢትዮጵያ በጎ ነገር እንዲስተጋባ ማድረጋቸው ነው። በተለይም በሁለተኝው ክፍል የሚገኙት፡ በተቻለ መጠን ስለኢትዮጵያ በጎውን በማጋነን፡ የሕወሃትን የስብዓዊ መብቶች ጽልመት፡ ጎስኝነት፡ ሙሰኝነት የሚሸፋፍን አመለካከት በምዕራባውያንም ሆነ ምሥራቃዊ ሚዲያዎች ላይ በጊዜው ያስደስኮሩላቸዋል።
    በተጨማሪም፡ እነዚህ ሀገሮች ለኢትዮጵያ ግዙፍ ዕርዳታ መፍሰሱን ይደግፋሉ። ነገር ግን ይህ ዕርዳታ በብዙ መስኮች – በተለይም በግብርናው – መስክ የሀገሪቱን ችግሮች፡ በምግብ ምርት እራስን ከማስቻል ይዘት ስሌለው፡ ትኩረታችውም ሆነ ጥረታቸው – በዘለቄታ ሀገሪቱን ከምግብ ዕርዳታ ተመጽዋች ነጻ ለማድረግ አላስቻለም። በመሆኑም፡ እየተደረገ ያለው፡ ትላንት እንደነበረ ሁሉ ዛሬም ኢትዮጵያ አንድ ሶስተኛ መንግሥታዊ በጀቷን በዓለም አቀፍ ዕርዳታ ተመጽዋችነት ላይ የተመሰረተ ሆኖ የውስጥና የውጭ ፖሊሲዋን በማክራየት እንድትቀጥል አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሮባታል።
    በአሁኑ ወቅት፡ በተለያዩ ምክንያቶች (የስብዓዊ መብቶች አለመከበር ችግር፡ የየራሳቸው የሀገሮቹ የኢኮኖሚ ችግሮች) መንስኤነት፡ ከለጋሽ ሀገሮች በቀጥታ የሚገኝው ዕርዳታ በክፍተኛ ድረጃ ቀንሷል (ክአሜሪካና እንግሊዝ በስተቀር)። በዚህም ምክንያት የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚስጠውን ብዙውን የዕርዳታና ብድር ጫና ድርሻ ተሸካሚ ሆኖአል።
    ለምሳሌ፡ ሌላው ቀርቶ ስብዓዊ ዕርዳታን እንኳ በተመለከተ፡ 12 የአውሮፓ ኅብረት ሀገሮች (እንግሊዝን አይጭምርም) በ2012 ለኢትዮጵያ በባይላተራል መንገድ ለዕርዳታ ያዋጡት €24 ሚልዮን ሲሆን፡ በ2013 ይህ መዋጮ ወደ €12.4 ሚልዮን ወርዷል። ከነዚህም መካከል ትልቁን ቅናሽ ያደረገችው ጀርመን ናት – ከ€8.2 ሚልዮን ወ €4.2 ሚልዮን ዝቅ በማድረግ። በመሆኑም፡ከዚህም ከዚያም አስባስቦ የበጀት ምንጮች በማስባስብና ተጨማሪ ምክንያቶች በመፍጠር (ነፍስ ወክፈ መልሶ ማቋቋም) በ2013 እንዳደረገው፡ የአወሮፓ ኮሚሽን በ 2011-2013 12 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ለመርዳት እንዲቻል €130 ሚልዮን ለግሷል።
    አሁን ለሁሉም ለጋሾች ከባድ የሆነው “የልማት” ዕርዳታውም እንዲሁ በበዙ ጥያቄዎች ላይ መውደቁ መሆኑ ይሰማል።
    በዓለም ዙሪይ ያለፉው ሩብ ምዕተ ዓመት የልማት ጊዜ በመሆኑ፡ ብዙ ታዳጊ አገሮች ከፍተኛ ተጠቃሚ ሆነዋል። ኢትዮጵያ ይህ ዕድል ቢገጥማትም፡ መሣሪያ ያነገቡት የሕወሃት ሰዎችና አጫፍሪዎቻቸው ግንባር ቀድም ተጠቃሚዎች የሆኑበት ሥርዓት በመዘርጋቱ፡ የትላንቱ ጦረኞችና የዛሬዎቹ የስላም ደጋፊ-መስል የአንድ ብኄረስብ ሰዎች፡ ሆን ብለው ዕኩልነትን የሚጻረር የፖለቲካ፡ የኤኮኖሚ፡ የደህንነትና ማኅበራዊ ፓሊስዎችን በኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
    ይህ ግን ዘላቂ መሠረት ስሌለው፡ ዛሬ የኤኮኖሚው የጥንድ ዕድገት ውደሳው ጋብ ብሎ፡ ሀገራችን የመንግሥት ብልግናና የሃስት ፕሮፓጋንዳ ከሚመገቡት መካክል ወድቃለች። በዚሁም ምክንያት (ሽፋኑ የውሃ ዕጥርረት፡ ድርቀት፡ የሃይማኖትና የብኄረቦች አለመቻቻልና ግጭቶች ላይ ቢመካኝም)፡ ተደጋጋሚ ዓለም አቅፍ ጥናቶች ኢትዮጵያ ከሚወድቁት የአፍሪቃአገሮች (Failed States) መካከል ተደምራ፡ የወደፊት ጽዋዋ አስፈሪ እንደሚሆን ቀንደኛ ደጋፊዎቿ ድምዳሜ ላይ መሆናቸውን በግልጽ የምንሰማበት ዘመን ላይ ደርስናል።
    ድሮስ ቢሆን፡ የሕዝብ ዓመኔታ ያጣ መንግሥት፡ መሣሪያውን ደግኖ በኅይል ለመግዛት ከመሞከር ውጭ ምን አማራጭ አለው? ጊዜው የጥላቻ፡ የክፋትና የቂም በቀል በመሆኑ፡ በአንድ በኩል፡ የሕወሃት ስዎች ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ሲሆን፡ በሌላ በኩል ደግሞ፡ የኢትዮጵያውያንን ስብዓዊ መብቶች በመግፈፍና መርገጣቸውን በማባባስ፡ ሃገሪቱን ወደ ቀውስ ጎዳን እየገፉ ናቸው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዴት ዕድገት ይኖራል?
    እንዲያውም፡ የራሱን የአገዛዝ ዘመን ለማራዘም ሲል፡ የኢትዪጵያ ሕዝብ ፍላጎትና አመለካከት ሳይጠየቅ ኤርትራን በፊርማው እንድትገነጥል ያደረገ፡ አገሪቱን የባሀር በር ለማሳጣት የደፈረ የመንግሥታዊ ባህልና ኃላፊነትና ግንዛቤ የሌለው ሕወሃት፡ ለሱዳን የኢትዮጵያን መሬት ቆርጦ ለመስጠት ዝግጅት ላይ መሆኑ ሕዝቡን በቃ! የሚል ድምዳሜ ላይ ማድረሱ አያጠራጥርም!
    በዓለም ታሪክ ውስጥም ሕወሃት “ታዋቂ” የሚሆነው፡ ራሱን ሥልጣን ላይ ለማቆየት፡ የሀገርን ልኡላዊነትና መሬት ቆርሶ ለጎረቤት ሀገርና ለከፍተኛ ብድር ስጭና ገንዘብ ለዋጭ አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ ነው።
    ዛሬም ሆነ ነገ፡ ለሀገራችን ዘላቂው መፍትሄ ግን መንግሥት የሕዝብን ፍላጎት ለማክበር መቻሉና ለዚህም ተጠያቂነት ያለበት ሥርዓት መዘርጋቱ ነው። ይህንን ለማድረግ፡ አሁንም ትንሽ የተስፋ መስኮት አለ – የሕውውሃት ስዎች ኃላፊነት የሚስማቸው ቢሁን። ይህ ለሕወሃትና ግብረአበሮቹ ተቀባይ ሳይሆን ቢቀር፡ ቀሪው ምርጫ ሕዝቡ እየተረገጠ መቀጠል፡ ወይንም እነርሱ ከመድረኩ መወገድ ነው።
    እስካሁን በዚህ ድህረ ገጽ ይህንን አሳብ አላራመድንም ነበር። የሁኔታው አስከፊነት ግን አሁን የወቅቱ አስፈላጊ እርምጃ አድርጎታል!
    http://ecadforum.com/

    Tuesday, January 28, 2014

    በሽብርተኝነት ህጉ ውይይት ስም የአዲስ አበባ ህዝብ እየተሸበረ ነው ሲሉ አንዳንድ ተወያዮች ገለጹ

    በሽብርተኝነት ህጉ ውይይት ስም የአዲስ አበባ ህዝብ እየተሸበረ ነው ሲሉ አንዳንድ ተወያዮች ገለጹ

    ጥር ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  :-በቅርቡ በአዲስ አበባ ውስጥ ለሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞችና በተዋረድም ከህዝቡ ጋር እተደረገ ባለው የሽብርተኝነት ህግ ውይይት፣  ነዋሪዎች ጥላቸውን እንኳን ማመን እንደሌለባቸው በአሰልጣኞች እየተነገራቸው ሲሆን፣ በስልጠናው ላይ የተካፈሉ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች፣ ስለሽብረተኝነት ልንማር ሂደን ተሸብረን መጣን ሲሉ ተናግረዋል።
    በመንግስት  ከፍተኛ አመራሮች የተዘጋጀው የማሰልጠኛ ሰነድ ኢሳት እጅ የገባ ሲሆን፣ ሰነዱ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን ቆሞ ልማቱን እንዲጠብቅና እንዲያፋጥን ይጠይቃል። በመስተዳድሩ የሚገኙ  የቢሮ ሃላፊዎች፣ በአዲስ አበባ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር በሆኑት በአቶ ተወልደ ወ/ጻዲቅ መሪነት በሰነዱ ላይ ውይይት አድርገውበታል ። በሰነዱ ላይ የመስተዳድሩ የየደረጃው  አመራሮችና ሲቪል ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው  ህዝብ እየተወያዩበት ነው።
    እስካሁን ባተካሄደው ውይይት እንደታየው የመንግስት ሰራተኞች በስልጠናው ላይ የሚገኙት የስም ምዝገባ ስላለ  እንጅ በዝግጀቱ አምነውበት አይደለም ይላሉ ተሳታፊዎች።
    በውይይቶች ወቅት የመንግስት ባለስልጣኖች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጡት ከህዝቡ ስለሚጠበቀው ግዴታ መሆኑን የሚናገሩት ተሳታፊዎች ፣ የአገሪቷን ደህንነት ፖሊስና የደህንነት ሃይሉ ጠብቆ ስለማይችል፣ ህዝቡ ከኮሚኒቲ ፖሊስ ጋር በመተባበር ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበት ባለስልጣኖች ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተሰታፊዎች ይገልጻሉ።
    የፌደራል ፖሊስ ሽብርተኝነትን ለመከላከልና ወንጀለኛን ለመለየት የአፍና የጸጉር ምርመራ ሊያደርግ እንደሚችል፣ ምርምራው እንዲደረግበት የተጠረጠረ ሰው ፈቃደኛ ካልሆነ ተመጣጣኝ ሃይል በፖሊስ ሊወሰድበት እንደሚችል፣  በማንኛውም ጊዜ በድነገት በከተማ ባስና በታክሲ ላይ ፍተሻ ሊደረግ ስለሚችል ህዝቡ መተባበር እንዳለበት የመንግስት ባለስልጣናት ተናግረዋል።
    የመንግስት ሰራተኞች  ቦርሳ፣ፌስታልና መሰል ቁሳቁሶችን ቢሮ ውስጥ ጥለው እንዳይሄዱ የተነገራቸው ሲሆን ፣ ቢሮ ውሰጥ የተገኙ ፌስታሎችና ቦርሳዎች ለአደጋ ከማጋለጣቸው በፊት በጥንቃቄ እንዲታዩ ምክር ተሰጥቷል።
    ለማወያያነት በቀረበው ሰነድ ላይ በግልጽ እንደሚታየው “ከፍርድ ቤት ፈቃድ በመውሰድ በሽብርተኝነት የተጠረጠረን ሰው የስልክ፣ የሬዲዮ፣ የኢንተርኔት የኤሌክትሮኒክስ፣ የፋክስ፣ የፖስታ ግንኙነት እና የመሳሰሉ ግንኙነቶችን ለመጥለፍ ወይም ለመከታተል፣ ጠለፋውን ለማስፈፀም ወደ ማንኛውም ቤት በሚስጢር የመግባት ወይም ይህንኑ ለመፈጸም የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ለማስቀመጥ ወይም ለማንሳት የፌደራል ፖሊስ ስልጣን ተሰጥቶታል።
    እንዲሁም “ ማስረጃ ከሚሰበሰብባቸው የተለያዩ ዘዴዎች መካከል አንዱ በሽብርተኝነት ወንጀል ከተጠረጠረው ሠው ላይ ናሙናዎችን መውሰድ እና የህክምና ምርመራ እንዲያደርግ ማድረግ በመሆኑ ፣ ተጠርጣሪውም በምርመራ ሂደት ናሙናውን ለመስጠት ወይም የህክምና ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ ካልሆነ ፖሊስ ተመጣጣኝ ኃይል ተጠቅሞ ናሙናውን የመውሰድ ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡
    ሰነዱ “ የሀይማኖት አክራሪነትና አሸባሪነት ዋናው ምንጭ ድህነትና ተስፋ መቁረጥ ” መሆኑን ከገለጸ በሁዋላ ፣  ”ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ በመንግስት የወጡ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና እቅዶች ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ሰፊ ርብርብ ማድረግ” ከህብረተሰቡ እንደሚጠበቅ ይገልጻል።
    ኢሳት አስተያታቸውን የጠየቃቸው ሰልጣኞች እንዳሉት ውይይቱ ህዝቡን የበለጠ የሚያሽብር ቢሆንም መንግስትም ሽብር ውስጥ መግባቱን ያመለክታል።
    በሰነዱ ላይ  ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት7፣ አልሸባብና አልቃይዳ አሸባሪ ድርጅቶች ተብለዋል

    Monday, January 27, 2014

    ዳር ሆነው የሚመለከቱት የጎሳ ፖለቲካ ምሱ “ደም”!!

    ዳር ሆነው የሚመለከቱት የጎሳ ፖለቲካ ምሱ “ደም”!!

    (ርዕሰ አንቀጽ)
    image1



    “ህወሃት” የሚባለው የትግራይ ነጻ አውጪ ትግራይን መቼና ከማን ነጻ እንደሚያወጣ በውል የተቆረጠ ቀን ባይኖርም ህገ መንግስታዊ ዋስትና ግን አለው በሚል እየተተቸ 23 ዓመታትን አስቆጥሯል። አገር እየመራም ነጻ አውጪ፣ በረሃም እያለ ነጻ አውጪ፣ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲወከልም ነጻ አውጪ!!
    ይህንን የተለመደና ግራ የሚያጋባ እውነት ያነሳነው ወደን አይደለም። ይህ የህወሃት ግልጽ መለያና ከመለያው የሚነሳው ትንታኔ ለማንም የተወሳሰበ ይሆናል ብለንም አንገምትም። ኢህአዴግ የሚባለው የ”ሎሌዎች” ስብስብ ያበጀውና የሚመራው ህወሃት ከሌሎቹ በተለየ በነጻ አውጪ ስም 23 ዓመት አገር ሲገዛ ሌሎቹ “የነጻ አውጪ” ስም አለመያዛቸው ግን ሁሌም ሊመረመር የሚገባው ጉዳይ ይመስለናል።
    አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ “ነጻ” መውጣት ያለባቸው ህወሃቶች ሳይሆኑ ሌሎች የአገራችን ህዝቦች፣ የትግራይን ንጹሃንን ጨምሮ ነው። ህወሃት ሲጠነሰስ ጀምሮ የነበሩትን ቀደምት አመራሮች በሂደት እየበላ አራት ኪሎ የደረሰው፤ ህወሃት መጥበብ የጀመረው ገና ከጥንስሱ ጊዜ ጀምሮ ነው። ስለ ህዋሃት የሚወጡ የምስክሮች ሪፖርቶችና መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ህወሃት በደም የታጠበ፣ በደም የተለወሰ፣ የበርካታ ንጹሃን ደም ያጨማለቀው፣ ታሪኩ ሁሉ በደም ዙሪያ የተሰራ፣ አሁንም ከዚሁ የደም ቁማር ነጻ መሆን ያልቻለ መሆኑን ነው።
    ህወሃት ግዛቱን እያሰፋ ሲሄድና አጋጣሚው ሲያመቸው ከተቋቋመለት መሰረታዊ ሃሳቡ ዘሎ “መንግስት” መሆን ሲያምረው “ኢህአዴግ” የሆነው ዓላማውን በወጉ ከ”መጥበብ ወደ መስፋት” በመቀየር ሳይሆን “በሰፍቶ መጥበብ ውስጥ” እየተጫወተ አገርና ህዝብን ረግጦ ለመግዛት ነው። ለዚህም ይመስላል ኢህአዴግን አሁን ድረስ “አገዛዝ” ከማለት በዘለለ በመንግሥትነት ሊጠሩት የማይፈልጉ የበረከቱት።
    በግብር እንደታየው በህወሃት “የሰፍቶ መጥበብ” ጨዋታ ውስጥ ቅድሚያ ትግራይ መወለድ፣ ሲቀጥል የትውልድ ቦታንና ስምን በመቀየር ማጭበርበር፣ ከዛም ታማኝ መሆን፣ ከሁሉም በላይ አነስተኛ ክልል በሚል ስልታዊ አካሄድ ብርና ኮብራ እየሸለሙ ማታለል፣ የአገዛዙ መለያ ሆነ። አሁን ድረስም ይዘቱ ባይቀየርም አፈጻጸሙ ግን ከክልል ወደ አውራጃ፣ ከአውራጃም ወደ ወረዳና ቀበሌ፣ ከወረዳና ቀበሌ ወርዶ ስጋና ደም የሚቆጠርበት የስልጣን ቅርምት ደረጃ “እድገት” አሳይቶ ይገኛል።
    በዚህ መልክ በተዋቀረው የህወሃት አገዛዝ ቁጥጥርና ክትትል አስቸጋሪ በመሆኑ አገሪቱ በሙስና በሰበሰች። ሙስናው ፈር ለቅቆ በድሃው ህዝብ ላይ ነገሰ። አወቃቀሩ ስርዓቱን በመታደግ ላይ የተመሰረተና የህወሃትን ባለጊዜዎች ስልጣን ማስጠበቅ በመሆኑ ሁሉም ነገር ሸተተ፤ ገለማ። ያቋራጭ ሃብታሞች ናኙ። ግንባታው ጨሰ። “ህዳሴው” ለተወሰኑ ወገኖች ፈንጠዝያ የተሰጠ ስያሜ ሆነ። ግድያ፣ እስር፣ እንግልትና አፈና እደግ ተመንደግ ተባለ። ነገሩ እንዲስተካከል ትግል የሞከሩ ተባረሩ፣ ታሰሩ፣ የተገደሉም አሉ። የተሰደዱ ጥቂት አይደሉም። አገር ውስጥ የቁም እስረኛ ሆነው ጊዜ የሚጠብቁ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።
    ሲጀመር በብሔር ብሔረሰቦች ስም ሲምሉና ሲገዘቱ የነበሩት የህወሃት መሪዎች፣ የራሳቸውን ሰዎች ሳይቀር ወረዳ እየለዩ የፈጸመባቸው ተግባር፣ በሌሎች የአገሪቱ ህዝቦች ላይ ከስርዓቱ መርህ በመነሳትና “በጥጋብ” የተፈጸመው በደል፤ “የገዢው መደብ ነኝ” በሚል ንጹሃንን ከስራና ከሃብታቸው ከማፈናቀል ጀምሮ የተሰራባቸው ግፍ ከጎሳ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ጋር ተዳምሮ የተካረረ ደረጃ ደርሷል።
    የከፋቸው በዝተው ቂማቸው እየተናነቃቸው ይገኛሉ። የህወሃት አመራሮች ከፊታቸው ክፉ ዘመን ስለመኖሩ ብዙም የተጨነቁ አይመስሉም። የቂም በትር ቀጠሮ የለውም። ቂም ቦታ አይመርጥም። የጎሳ ፖለቲካ በባህሪው ምሱ ደም ነው። የጎሳ ጣጣ ባለባቸው አገሮች የታየው ይኸው እውነት ነው። በተለይ ህወሃቶች አሁን ባጨመላለቁት ደረጃ እንለካው ከተባለ አደጋ አለ፤ ያውም ግልጽ የሆነ አደጋ። ችግሩ ሲነሳ፣ ቂም በትር ሲሰነዝር፣ ጥላቻ ልጓሙ ሲበጠስ፣ በብርና በመሳሪያ ብዛት መታደግ የሚቻል አይሆንም። ይህንን ስንል ላገራችን ችግርና የደም አታሞ ለመምታት አይደለም። የቆምንለት ዓላማና የሙያ ቃልኪዳናችን ከጎሠኝነት ይልቅ ሰብዓዊነትን ማስቀደም መሆኑን የሚጠሉንም ጭምር ያውቁታል፡፡ በዚህ የሰፋ ራዕይ ውስጥ ስላለን የመጥበብ አደጋ ምን እንደሆነ በግልጽ ይታየናል፡፡ ስለዚህ የአደጋ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን፡፡
    ዛሬ ዳር ቆመን የምንመለከተው የጎረቤታችን ደቡብ ሱዳን የጎሳና የዘር ጭፍጭፍ “እኛም ቤት እሳት አለ” ስለሚያሰኝ ነው። የሚታሰሩ፣ የሚገረፉ፣ የበይ ተመልካች የሆኑ፣ የተገደሉ፣ አሁን ድረስ በስቃይ ላይ ያሉ … ቤቱ ይቁጠራቸውና ዘመድ፣ ወገን፣ ተቆርቋሪ፣ አለኝታ፣ ታዳጊ አላቸው። ብሶት ህወሃትን ብቻ አይወልድምና ሁሉም ረጋ ብሎ ያስብ። ህወሃት ብቻ የብሶት የበኩር ልጅ አይደለም፤ ሊሆንም አይችልም። ሲያሻ ህግ እየተጠቀሰ፣ ሲያሻ በተቀነባበረ ድራማ፣ ሲፈለግ በተፈለገው መንገድ የሚፈነጭበት ጊዜ ሳያረጅ ለሰላም ሁሉም እጁን ያንሳ!! የጎሳ ፖለቲካ ምሱ ደም ነውና ሃዘን ሳይመታን በእውነተኛ እርቅ ጊዜው ሳያልፍብን የጎሳ ፖለቲካን ምስ እናምክን!! ተቃዋሚዎችም ጭምር!!

    The Ethiopians and their past

    The Ethiopians and their past

    (Yilma Bekele)
    fikre book



    We love to visit the past. There is no one like us that digs deeper, travel further to harvest the bounty of our rich past. To say we dwell on the past is definitely an understatement. I would not be surprised if scientists after mapping our brain find a special pocket where we store ugly little tidbits of the past to fuel our anger. To claim we live in the past is not far from the truth.
    Compared to others what makes our situation a little different is how we use the past to explain or understand the situation in the present.  We are beyond unique on how we use a wrecking ball to smash our past to pieces and are surprised when we are unable to build the future because there is nothing to stand on. How in the world can you build without a foundation?
    From what I can see compared to us others use their past in a completely different manner. Let alone a country even a family weaves a rich history to put the ancestors in a good light and favorable condition. Countries are notorious for spinning such tales they put little Rumpelstiltskin, the weaver of straw into gold to shame. All are the ‘exceptional, the Middle kingdom, where the sun never sets, the Motherland etc. etc.  If they are rich and strong they like to assure us that it has always been like that and if they are poor and weak they will invite us to sit down so they can tell us of the times when they were a great empire with ships in all the seven seas.
    As I said earlier we are a little different. Sometimes it is a little bizarre when others say all those good things about us and we are too busy to notice since we are trashing the past. The joke is on us I guess. I brought all this up because lately we have been going thru one of our periodic self flagellation exercise. Every Tom Dick and Harry has been picking on my motherland. You notice the names, of course I could have given them Abesha names but I just don’t want diversions. Tom Dick and harry should do. Every little narrow nationalist village idiot with a keyboard has been dumping on my glorious past.
    We celebrated Christmas and welcomed a new European New Year. December and January are times of renewal and in our area we celebrated like never before. Among other things the visit by Chairman Yelekal of Semayawi party was a memorable moment. It is refreshing to see our country is still capable of producing such a young and courageous person that dares to demand justice for his people.  We also held a fund raising for ESAT and were entertained by our children playing traditional music using modern instruments. Chairman Yelekal comes across the ocean to bring us ‘determination’ from home and the young ones born here showed us the bond is still strong.
    This month happens to be the 100 year anniversary of King Minilik’s death. King Minilik is the father of modern Ethiopia. He is also a figure of such historical importance and is included in all historical books as a leader of an early kingdom called Ethiopia. He took nation building to be his primary task and accomplished that in a spectacular manner. Force was used sparingly. Marriage, title, recognition were his favorite tool.
    His fascination with technology is legendary. His diplomatic skills not only united Ethiopia but forced others to recognize him as an equal. When you consider this was the period referred to as ‘the scramble for Africa’ by the European powers we were lucky to have such a skilled leader. You know what happened to the rest of Africa. We stayed independent and never kowtowed to any foreign devil.
    King Minilik of Ethiopia is also an International hero to all black people. The battle of Adwa fought one hundred eighteen years ago between Italy and Ethiopia is the first instance where a European power was defeated by an African Army. In the scheme of human history historians claim it is a big deal. I have no reason to disagree.
    To celebrate the centennial of his death EHSNA (Ethiopian Heritage Society in North America) is holding a commemoration in Silver Springs, Maryland. All Ethiopians are invited to attend and get in touch with their past.
    It was also a delight to see the lecture at Harvard University by Raymond Jonas a historian from the University of Washington discussing his book ‘The Battle of Adwa- African Victory in the Age of Empire.’  He has no axe to grind. His perspective is purely as a professional and his conclusion is music to our ears. After careful study the good professor gave credit to our King for his leadership skills in amassing such a force in a short notice to bring the invader to their knees. It showed that when we feel threatened we come together. That is because like it or not Ethiopia is part of our DNA. It cannot be deleted, erased, written over or corrupted without consequences. Split personality is one of the symptoms that foolishly question their identity.
    As I said before, we Ethiopians are a little different. Some of our supposedly learned friends with papers from the most prestigious universities decided to reinterpret history in a layman’s manner. It was without shame they went out in public to insult, condemn and treat our history as nothing but a Hollywood fiction. They were following on the footsteps of the dead warlord from Adwa that rose to prominence using force and treachery and declared our flag to be nothing but a piece of cloth as he entered Minilik’s palace. Today his underlings are continuing that path of revising our glorious past.
    As if the assault by the ethnically challenged is not enough we have another lost soul from the past trying to get our attention. It is no other than Captain Prime Minster Fekre Selassie Wegderes out with a book trying to put his own spin on what happened yesterday. To be honest I do not think I want to read his book. Reading a book by a convicted mass murderer is not one of my priorities. In all sincerity I was debating whether to buy the book or not when I came across his interview.
    Based on that interview I am sure to stay away from this work of fiction. What exactly did we do to deserve such individuals instead of remorse and begging for forgiveness show up to tell us the survivors how great they were and how they could teach us today where we are going wrong.
    This convicted criminal instead of coming clean with the truth now is trying to feign ignorance for the crimes that were committed when he was part of the group. I have no idea why he came on the interview if he was not going to shed light on the ugly things he did and answer questions in a direct way since there is nothing to hide. But that was not his style. He said he was here to set the Derg era straight which he referred to a major part (telek akal) of our history. How delusional can one get? Our country is three thousand years old and he considers his twenty years romp as major event? It is sad all those years in prison did not help him accept his crimes and come to terms with his weak and cruel personality. You think he still feels bullied and is afraid of the Colonel? Too bad he is trying to profit from his crimes at the same time white wash history and we are letting him do that. I told you we are unique.
    It is another instance where our past becomes an impediment to progress. It is not accidental. They are deliberate insertions by the regime to create diversion. We so much dwell on the past that we have no time to create the future. They know that just like a bee is attracted to a flower we will flock over to this kind of sensational news and activity. The regime with its unlimited resources is creating news for us and we react.
    There are eighty million of us. I am sure there are plenty with rich and wonderful stories that can elevate our spirit and mend our broken hearts. Both inside Ethiopia and in the Diaspora there are thousands that are working in all kinds of different ways to improve the spiritual, financial, health and family concerns of their people in a positive manner. Instead of bringing out the best in us we seem to prefer to sink to the bottom and feed on sludge and toxic garbage.
    They call it freedom of expression. I call it groping in the dark. The ethnic based regime is doing all it can to instill fear, destroy our self worth, divide us into ethnic and religion based Bantustans and we the supposedly free souls are cooperating by trashing our past and elevating criminals as historians and someone worthy of a conversation. It is not a winning strategy. It will not help us secure our freedom, help our people lead a better and fruitful life and lay the foundation to build a country our children would be proud of. It is never too late to learn from the past and use it to construct the Ethiopia that is destined to shine like the North Star. We can start today by saying no to peddlers of hate convicted criminals.

    Sunday, January 26, 2014

    የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ

    የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ


    “ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።
    1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
    ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።
    2. አመላካች ሁለት: ለምግብ የመክፈል አቅም (Affordability)
    ይህ አመላካች “የአገሩ ሕዝብ በአገሩ ዋጋ ምግብ ገዝቶ ለመብላት ምን ያህል አቅሙ ይፈቅድለታል?” የሚለውን የሚመልስ ነው። አሁንም ከመጨረሻ እንጀምር። አንጎላ፣ ዚምባቡዌ፣ ቻድ፣ ጉያና፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ጋምቢያ እና ኢራን የየአገሩ ሕዝብ ምግብ መሸመት የሚቸገሩባቸው አገሮች ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ ከመጨረሻ አምስተኛ ናት።
    3. አመላካች ሶስት: የምግብ ጥራት
    ይህ የምግብ ይዘትንና የአያያዝ ንጽህናን የሚመለከት ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ሞዛምቢክ፣ ቻድ፣ ቶጎ፣ ዛምቢያ፣ ማሊ፣ ናይጄሪያ፣ ባንግላዴሽ፣ ሌሶቶ ከመጨረሻው እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ጥራት የመጨረሻዋ አገር ናት።
    4. አመላካች አራት፡ የሰውነት ውፍረት እና የስኳር በሽታ
    ይህ አመላካች ከልክ ያለፈ ውፍረት ዓለም ዓቀፍ የጤና ችግር እየሆነ በመምጣቱ የገባ አመልካች ነው። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥሩ ውጤት ያመጣችሁ በዚህ አመላካች ብቻ ነው። ኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝቧ ቀጫጫ ነው፤ የስኳር በሽታም እንደሌላው አገር የተስፋፋባት አገር አይደለችም።
    5. አማካይ ውጤት
    የእነዚህ አራት አመላካቾች ድምር ውጤት አጠቃላይ ውጤትን ይሰጣል። በአጠቃላይ ውጤት: ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ማዳካስካር፣ የመን፣ ቡሩንዲ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዚምባቡዌ፣ ሴራሊዮን ከመጨረሻ እስከ አስረኛ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛ ነች።
    ይህ ምንን ያመለክታል?
    ወያኔ ባለፉት አስር ዓመታት በተከታታይ ከ11% በላይ ኢኮኖሚውን አሳድጌዋለሁ ሲለን ነበር። እድገቱ ያተኮረው ገጠር፤ ምንጩም ግብርና ነው ብሎን ነበር። ሐቁ ግን ከላይ የተመለከተው ነው።
    እርግጥ ነው የወያኔ ሹማምንት በከተሞች ሕንፃዎችን ይገነባሉ፤ በገጠሮች በመቶዎች ሄክታር የሚለካ ለም መሬት ይዘው ፈጣን ገንዘብ በሚያስገኙ የአበባ፣ የጫትና የቃጫ ምርት ላይ ተሰማርተዋል። ከራሳቸውም አልፈው ሀብታም የውጭ አገራት ሸሪኮቻቸውን በአገራችን ለም መሬት ይበልጥ ያበለፅጓቸዋል። የእነሱ የግላቸው፣ የቤተሰቦቻቸው፣ የዘመዶቻቸው እና የሸሪኮቻቸው ኢኮኖሚ እየተመነደገ መሆኑን እናውቃለን። ይህን በገዛ ዓይኖቻችን የምናየው ሀቅ ነው።
    ሆኖም ግን የእነሱ ኢኮኖሚ ማደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ አለመሆኑ እናውቃለን። አገራችን ከጓረቤት አገሮች ጋር ስትነፃፀር ወደ ኋላ እየቀረች መሆኑ ያንገበግበናል። በቅርቡ አክስፋም በጥናት ያረጋገጠዉ የኢትዮጵያ ገበሬዎች በየቤታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር በምስጢር የሚያወሩትን እውነት ነው።
    ከሳምንት በፊት ደግሞ “ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት” የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም አንድ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጎ ነበር። በዚህ የጥናት ውጤት መሠረት በዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ያሉ አስር አገሮች በቅደም ተከተል ሞንጎሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ቱርክሜንስታን፣ ቡታን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ላኦስ፣ ቲሞር-ሊስቲ፣ ኤርትራ እና ዛምቢያ ናቸው። በዝርዝሩ ውስጥ ኢትዮጵያ አገራችን የለችበትም።
    በዓለም አቀፍ መድረኮችም የወያኔ መረጃዎች ውሸትነት እየተጋለጡ መሆናቸው በጎ ምልክት ነው። የሚያሳዝነው ግን ይህንን ሀቅ የሚያዉቁ ምዕራባዉያን ለጋሽ አገሮች አሁንም ወያኔን እየረዱና እየደገፉ ሥቃያችን የሚያራዝሙብን መሆኑ ነው።
    ለዚህም ነው ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው በአገራችን መሠረዊ የሆነ የአስተዳደር ለውጥ ሲኖር ነው ብሎ የሚያምነው። የወያኔ አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እስካልተተካ ድረስ የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ መደህየቱ፤ ጥቂት ሀብታሞች ደግሞ በብዙሀኑ ድህነት መበልፀጋቸው አይቀርም። የወያኔ ውሸቶች ለኢትዮጵያ ድሀ ምግብና መጠለያ አይሆኑለትም። ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ማምጣት የምንችለው ወያኔን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ሁለተናዊ እድገት የሚጨነቅ መንግሥት መምረጥ ስንችል ብቻ ነው።
    ስለሆነም ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በውሸት እድገት እያደናቆረን፤ በተግባር ግን እያደኸየን ያለውን ዘራፊውን ወያኔን አስወግደን በሕዝብ ነፃ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖረን ትግላችን እናጠንክር ይላል።
    ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

    Friday, January 24, 2014

    Norway to Co-Chair Human Rights and Democracy Sub Group in Ethiopia With the European Union

    Norway to Co-Chair Human Rights and Democracy Sub Group in Ethiopia With the European Union


    Through this role, Norway is actively engaged in human rights and democracy issues in Ethiopia
    As of November 2013, the European Union has assumed the role as Co-Chair for the Human Rights and Democracy Sub Group in Ethiopia, after the United Nations Office of the High Commissioner for Human Rights. Norway and EU will Co-Chair the group and regularly bring together partners working on human rights and democracy issues in Ethiopia.
    The Human Rights and Democracy Sub Group is a sub-group of the Ethiopian Partners' Group, which reports to the Development Assistance Group (DAG). Norway has co-chaired the group since 2011. Through this role, Norway is actively engaged in human rights and democracy issues in Ethiopia.
    The objectives of the Group are to share information on recent human rights and democracy related events, actions and plans, harmonize efforts to monitor human rights situation and follow-up human rights allegations in the country. Each meeting has a thematic focus and a relevant speaker is invited to introduce a topic. Topics which have been addressed over the last year are:
    - Civil Society in Ethiopia
    - Resettlement and Villagization
    - Federalism, Decentralization and Local Authorities
    - Media, Press Freedom and Journalist Culture in Ethiopia
    - Ethiopia's National Human Rights Action Plan
    - Ethiopia's Structural and Political Framework focusing on the Constitution and Ethnicity
    - Ethiopia's Universal Periodic Review - 2009 and upcoming 2014 - Civil society's report
    - Religious development in Ethiopia focusing on Islam and relations to the State and the Orthodox Church
    (Embassy of Norway)

    Ethiopia Has a Terrible Human Rights Record - Why Is the West Still Turning a Blind Eye?

    Ethiopia Has a Terrible Human Rights Record - Why Is the West Still Turning a Blind Eye?

    2014-01-23-IMG_0008.JPG
    Some disappeared, others were given lengthy prison sentences. One thing all thirty men arrested in 2012 in Ethiopia had in common was that they had criticised the state and the policies of the former Premier, Meles Zenawi.
    And yet last week Japan's Prime Minister Shinzo Abe and a group of Japanese business leaders met with the current Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn to discuss further support for Ethiopia at "government and private sector level."
    The former Meles Zenawi was a staunch supporter of American counter-terrorism policy while at the same time overseeing a country with a violent human rights record. In the eyes of the USA, Ethiopia is strategically situated. Located in the Horn of Africa, next to Somalia, northern Kenya and Sudan, it acts as a buffer zone between the growing Islamic extremism of Somalia and the West. As a result, the human rights violations of Zenawi were ignored.
    As one of the first signatories of the UN in 1948, Ethiopia is a Western ally: 11 per cent of its entire GDP comes from Foreign Aid. The US is one of Ethiopia's largest donors: it is estimated that it gave $3.3bn in 2008 alone. The two countries benefited from their close relation: there have been rumours that America hosted "black sites" in Ethiopia; bases where the CIA interrogated undeclared prisoners during the "War on Terror."
    But Meles Zenawi died in 2012. The opportunity for a more liberal government was not seized: Zenawi was replaced by Hailemariam Desalegn, described by critics as an "identikit Zenawi" running the country on "auto-pilot". Desalegn is following the same political manifesto as Meles - he hasn't changed one member of parliament.
    The arena for debate and discussion is narrowing. Critics argue that Ethiopia is fast becoming a "one party democracy" where there are many parties but the same one wins again and again. Meles spoke to foreign press in 2005 and defended his 97 per cent electoral victory: "In democracies the party with the best track record remains in power." The years since 2005 have seen growing unrest among the Ethiopian population and serious repression against critics of the regime. Human Rights Watch reported that Ethiopia "continues to severely restrict freedom of movement and expression". It adds that "30 journalists and opposition members have been convicted under...vague anti-terrorism laws".
    The day before World Press Freedom Day on May 2 2013, the Ethiopian government ruled to uphold the imprisonment of one of its most well-known prisoners of conscience, Eskinder Nega. He was jailed for being a journalist who criticised the government, and yet, by standing up for his beliefs and expressing his basic human right for Freedom of Speech, he earned an 18 year jail sentence.
    Prime Minister Hailemariam Desalegn has denied his release. America and Britain have done little to challenge their ally, so worried are they about creating another enemy in the Horn of Africa. Britain and America have consistently failed to challenge their ally about its abhorrent Human Rights record. Ethiopia flaunts its apathy towards the UN convention of Human Rights, denying opposition members a right to fair trial and repressing people for trying to voice their opinions peacefully.
    Ethiopian political repression is worsening. There have been repeated crackdowns against the country's Muslim minority. This has included arbitrary arrests as Muslims make peaceful demands for freedom of worship. Again, critics have voiced concern with the regime. Mehari Taddele Maru, head of the African Conflict Prevention Program at the Institute for Security Studies expressed concern that "if legitimate grievances are not met then there is a risk that extremist violent elements will exploit those grievances to further their own."
    The world is waking up to Ethiopia's increasingly poor human rights track record and yet the United States hasn't stopped aid flowing to Ethiopia or threatened the country with sanctions. Japan still tries to conduct business with Ethiopia when instead they should be holding Ethiopia to account.
    As a founding member of the UN and an "ally" of the West, Ethiopia must be held accountable for her crimes. If the West does not challenge Ethiopia and demand that it releases its prisoners who have been locked up without fair trial, then notions of democracy and human rights accountability as embedded in the Human Rights Charter look ever more vulnerable-Human Rights globally will be laughed out of the door.

    Thursday, January 23, 2014

    Man accused of spying for ESAT sentenced to four years in prison

    Man accused of spying for ESAT sentenced to four years in prison
    Man accused of spying for ESAT sentenced to four years in prison 


    Mikiyas Nigatu of the Ethiopian Airports Enterprise’s Gambella Airport Security personnel, who was charged by the federal prosecutor for delivering sensitive information to the ESAT journalist named Fasil Yenealem for 4,460 Br is sentenced to four years in prison by the Federal High Court’s Fourth Criminal Bench on January 20, 2014.

    Mikiyas who has failed to defend himself against a 10 page written document from his e-mail and three pictures from his cell phone has been giving various information to the ESAT television station which was deemed by the Ethiopian government as “a media outlet for the terrorist group Ginbot 7” The charge indicates that Mikiyas has provided information about foreign investors who were killed in the Gambella region and other very sensitive security related materials.



    Girum Tebeje 

    New report calls on Ethiopia to reform repressive anti-terror law

    New report calls on Ethiopia to reform repressive anti-terror law

    IPI and partners also call for immediate release of five imprisoned journalists

    VIENNA, Jan 14, 2014 – Ethiopia’s use of sweeping anti-terrorism law to imprison journalists and other legislative restrictions are hindering the development of free and independent media in Africa’s second largest country, according to a report published today by the International Press Institute (IPI).
    Dozens of journalists and political activists have been arrested or sentenced under the Anti-Terrorism Proclamation of 2009, including five journalists who are serving prison sentences and who at times have been denied access to visitors and legal counsel. The report, “Press Freedom in Ethiopia”, is based on a mission to the country carried out in November by IPI and the World Association of Newspapers and News Publishers (WAN-IFRA).
    “Despite a strong constitutional basis for press freedom and freedom of information, the Ethiopian government has systematically used the anti-terrorism law to prosecute and frighten journalists, which has put a straight-jacket on the media,” IPI Executive Director Alison Bethel McKenzie said. “Our joint mission also found a disturbing pattern of using other measures to control the press and restrict independent journalism, including restrictions on foreign media ownership and the absence of an independent public broadcaster.”
    The report urges the Ethiopian government to free journalists convicted under the sedition provisions of the 2009 measure. These journalists include Solomon Kebede, Wubset Taye, Reyot Alemu, Eskinder Nega and Yusuf Getachew. Mission delegates were barred access to the journalists, who are being held at Kaliti Prison near the capital Addis Ababa.
    The report urges the 547-member lower house of parliament to revamp the anti-terror law to ensure that it does not trample on the rights of freedom of speech and assembly provided under Article 29 of the Ethiopian Constitution and further guaranteed under the African Charter on Human and People’s Rights and the U.N. Human Rights Covenant, which Ethiopia has ratified.
    In addition, the report:
    - Recommends that Ethiopian lawmakers review laws that bar foreign investment in media, measures that inhibit the development of an economically viable and diversified market.
    - Urges the courts to ensure that rulings restrict press freedom only in cases of intentional incitement or clear participation in acts of terrorism, and that judges act independently to protect the public’s right to be informed about political dissent and acts of terrorism.
    - Urges Ethiopia’s journalists and media owners to step up cooperation to improve professionalism and independence, and to form a unified front to defend press freedom.
    The joint IPI/WAN-IFRA mission was carried from Nov. 3 to 6, just ahead of the African Media Leaders Forum (AMLF) in Addis Ababa. The organisations’ representatives met with more than 30 editors, journalists, lawyers, politicians and bloggers, as well as associates of the imprisoned journalists. The delegation also held meetings with the ambassadors of Austria and the United States, a senior African Union official, an Ethiopian lawmaker and government spokesman Redwan Hussien.
    The organisations urged Prime Minister Hailemariam Desalegn to free the imprisoned journalists, some of whom are suffering from deteriorating health. In a joint statement issued immediately following the mission, IPI and WAN-IFRA also expressed their commitment to helping improve the professionalism, quality and independence of journalism in Ethiopia.
    While the report highlights a long history of press freedom violations in Ethiopia, including a crackdown on journalists and opposition politicians following the country’s 2005 national elections, it notes that the 2009 anti-terrorism law has given the government expansive powers.
    “The 2009 anti-terrorism law gave new powers to the government to arrest those deemed seditious, including journalists who step beyond the bounds of politically acceptable reporting or commentary,” the report says. “Armed with statutory authority, the government has not shied from using the laws to bludgeon opposition figures and journalists. Dozens of journalists have been imprisoned or accused of sedition or fomenting unrest, forcing many to flee the country.”
    The report notes other forms of pressure by the government. Independent journalists recalled being the target of smear campaigns by state-run media, while editors recounted that managers of the government-run printing press refused to print editions of newspapers containing controversial articles.
    The report does note positive developments, such as the growth in advertising and readership for some of the country’s leading independent newspapers. Journalists and newspaper publishers also expressed a desire to improve professionalism, quality and solidarity; although they added that government pressure and laws continue to create hurdles to self-regulation and cooperation.
    “We came away from Ethiopia recognising the tremendous potential for a highly competitive, professional and successful media market in Ethiopia,” Bethel McKenzie said. “But to make this happen, the Ethiopian government must remove the roadblocks, starting with the release of imprisoned journalists and then conduct a thorough review of the laws to ensure that reporting on legitimate criticism or dissent is not grounds for prosecution.”