Sunday, July 28, 2013

ኮሚቴዎቻችን በነገው ቀነ በቀጠሯቸው መሰረትፍርድ ቤት እንደማይቀርቡ ተገለፀ፡

ኮሚቴዎቻችን በነገው ቀነ ቀጠሯቸው መሰረትፍርድ ቤት እንደማይቀርቡ ተገለፀ፡


በሂጅራ ግቢ ታስረው የሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ 


አባላት እና ውድ ኢስላም ልጆች ከአንድ ወር በላይ ተቋርጦ የነበረው
የፍርድ ቤት ሂደት በቀነ ቀጠሮ መሰረት በነገው ዕለት ሰኞ ሐምሌ 22 ይጀምራል 

ተብሎ የተጠበቀ የነበረ ሲሆን ኮሚቴዎቻችን በመጅሊስ አመራሮች ላይ በመሰረቱት 

ክስ መሰረት የኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት ኡስታዘ አቡበከር አህመድ ጉዳዩን 

ለመከታተል ፍርድ ሄደው በነበረበት ወቅት በነገው ቀነ ቀጠሮ መሰረት ችሎት ፊት 

እንደማይቀርቡ አንደተነገራቸው ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ከአንድ ወር በላይ ተቋርጦ የነበረው የፍርድ ቤት ሂደት በነገው ዕለት ይጀምራል 


ተብሎ ሲጠበቅ ከክፍለ ሃገር ድረስ እዚህ አዲስ አበባ የምስክር
ቃላቸውን ለመስጠት የሚመጡ ስላሉ እነሱን አስተናግደን አስክንጨርስ ፍርድ ቤት 

አትቀርቡም መባላቸው ተሰምቷል፡፤ ኮሚቴዎቻን መቼ ችሎት እንደሚቀርቡ በሰበር 

ሰሚ ችሎት ተወስኖ የፊታችን ማክሰኞ እንደሚገለፅላቸው እንደተነገራቸው ምንጮች 

ያስታወቁ ሲሆን ቀድመን ያሳወቅናችሁም በቀነ ቀጠሮ መሰረት ብናቀርባችሁ 

ትጉላላችሁ በሚል ነው ሲሉ መናገራቸውን ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል፡፤ የፍትህ 

ባለቤት የሆነው አላህ ፍትህን ያስፍንልን!!!

No comments: