Wednesday, July 29, 2015

የዞን 9 ጦማርያን በድጋሚ ለብይን ተቀጥረዋል



በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው ከአንድ አመት በላይ እየተጓተተ ከሚገኙት አራቱ የዞን 9 ጦማርያን ለነሀሴ 13/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥረዋል፡፡
ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ "ፍርድ ቤት" ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት ጦማርያኑ በተከታታይ ቀጠሮ በተሰጠበትና እልባት ባላገኘው ‹ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ወይስ ይከላከሉ› በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ሌላ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
መዝገቡ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው የአቃቤ ህግ የደረጃ ምስክሮች ቃል ከመቅረጸ ድምጽ ተገልብጦ በጽሁፍ ከመዝገቡ ጋር መያያዙን ለመጠባበቅ ነበር፡፡ በዚህም ፍርድ ቤቱ የምስክሮቹ ቃል በጽሁፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር መያያዙን በመግለጽ መዝገቡን መርምሮ ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ወይስ መከላከል ያስፈልጋቸዋል የሚለውን ለመበየን ለነሀሴ 13/2007 ቀጠሮ ይዟል፡፡
የተሰጠው የቀጠሮ ጊዜ ረዘመ በሚል ቀጠሮው አጭር እንዲሆን የተከሳሾች ጠበቃ ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ‹‹ከተያያዘው የመዝገብ ብዛት አንጻር ከነሀሴ 13/2007 በፊት አይደርስልንም›› በማለት የተሰጠው ጊዜ ምክንያታዊ እንደሆነ ለማስረዳት ሞክሯል፡፡ ጠበቃው በበኩላቸው ‹‹መዝገቡ ብዙ ቢመስልም የተጠቀሰውን ያህል ጊዜ ሊወስድ አይችልም ብለን ስለምናምን አጭር ቀጠሮ ይሰጠን፤ በሌላ በኩል ክሱ ከተቋረጠላቸው ሰዎች ጋር በተያያዘ መዝገቡ እንደቀነሰ እናምናለን›› በማለት መዝገቡ ከተባለው ጊዜ በፊት ተመርምሮ ብይን ሊሰጥ ይገባል በሚል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ ከነሀሴ 15/2007 ዓ.ም በኋላ እንደማይሰየም በመግለጽ፣ ከዚያ በፊት ነሀሴ 13/2007 ዓ.ም ብይኑን ለማድረስ፣ ካልተቻለ ደግሞ እስከ 15/2007 ባሉት ሁለት ቀናት ለመጨረስ እንደሚሞክር በመግለጽ ቀጠሮውን በነሀሴ 13/2007 ዓ.ም አጽንቷል፡፡
በዛሬው ውሎ ከቂሊንጦ እስር ቤት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ አቤል ዋበላና ናትናኤል ፈለቀ የቀረቡ ሲሆን አሁን በክስ ላይ ከሚገኙት ውስጥ አንደኛ ተከሳሽ የሆነችው ሶልያና ሽመልስ በሌለችበት ጉዳያቸው ለአጭር ጊዜ ታይቷል፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
የዞን9 ጦማርያንን የፍርድ ቤት ሂደት በማጓተት ያልተሰራ ወንጀልን መፍጠር አይቻልም፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ጉዳየዮን ማንጓተቱን ያቆም ዘንድ የመንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላት በጉዳዬ ላይ ውሳኔያቸውን በአፋጣኝ እንዲሰጡልን ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ የሚገኙት ቀሪ 5 የዞን 9 ጦማርያን ለነሀሴ 13/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥረዋል፡፡

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ የሚገኙት ቀሪ 5 የዞን 9 ጦማርያን ለነሀሴ 13/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥረዋል፡፡
በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት አራቱ በእስር ላይ የሚገኙት ጦማርያን እና በሌለችበት ጉዳዩዋ የሚታየው አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ወይስ ይከላከሉ በሚለው ጉዳይ ላይ ለብይን ሊቀጠሩ ችለዋል፡፡

Tuesday, July 28, 2015

An Official White House Visit to Ethiopia? Africans Tell Obama ‘Don't Do It!’

Ethiopians march for human rights in Washington DC, 2006. Photo by Elvert Barnes via Flickr (CC BY 2.0)
Ethiopians march for human rights in Washington DC, 2006. Photo by Elvert Barnes via Flickr (CC BY 2.0)
US President Barack Obama's last trip to Africa before his term ends will take him to Kenya and Ethiopia, where he'll be the first sitting US president to visit. Obama first toured Africa nearly two years ago, making stops in Senegal, Tanzania, and South Africa.
Obama's decision to stop in Ethiopia has surprised human rights activists and advocates for good governance both in Africa and elsewhere. Ethiopia is one of the worst human rights offenders in Sub-Saharan Africa. In its 2014 report, Human Rights Watch noted that Ethiopia increasingly restricts the freedoms of assembly and expression:
[…] the Ethiopian authorities continue to severely restrict the rights to freedom of expression, association, and peaceful assembly, using repressive laws to constrain civil society and independent media, and target individuals with politically motivated prosecutions.
Muslim protests against perceived government interference in their religious affairs were met by security forces with arbitrary arrests and detentions, beatings, and other mistreatment throughout the year. The trial of 29 protest leaders who were arrested in July 2012 has been closed to the public, media, and family members since January. Others convicted under the country’s deeply flawed antiterrorism law—including opposition leaders and four journalists—remain in prison.
Despite the troubling state of human rights in the country, Ethiopia remains a major recipient of foreign aid money and security support from the United States. A White House statement about the trip said that Obama will visit the country for bilateral meetings with the Ethiopian government as well as the leadership of the African Union as part of US efforts to “work with the countries and citizens of sub-Saharan Africa to accelerate economic growth, strengthen democratic institutions, and improve security.”
Last month, Ethiopians voted in parliamentary elections, where opposition parties said the voting was not free or fair. The African Union said the elections were peaceful, but fell short of using the words “free and fair.” While noting that the elections were peaceful, the US State Department expressed concern about restrictions on civil society, the news media, opposition parties, and independent voices and views.
Hannah McNeish, a freelance journalist East and Central Africa, juxtaposed last month's suspicious elections results with the White House's decision to honor Ethiopia with an official visit:
Source: globalvoicesonline

Obama says Ethiopia should not jail journalists, restrict opponents

U.S. President Barack Obama said on Tues that Ethiopia "cannot unleash the complete potential of its people" if it jails journalists and restricts legitimate opposition groups.

Ethiopia's government has acknowledged it had additional work to try and do to develop its democracy however also says any journalists it's detained committed crimes.

In a speech at the African Union, Obama conjointly said Central African Republic leaders required to conceive to comprehensive elections and a peaceful transition of power. Elections in Oct can mark a return to democratic rule after the Seleka rebels toppled President Francois Bozize in March 2013, sparking a conflict.

Reuters


Monday, July 27, 2015

ፕ/ት ኦባማ ” ኤርትራ ያለ ተቃዋሚ ድርጅትን በአሸባሪነት ለመፈረጅ ” የሚያስችል በቂ መረጃ የለንም አሉ

ሐምሌ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አሜሪካዊው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት " በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ " ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ ዌዲ ሸርማን አርበኞች ግንቦት7ትን በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ያቀረቡትን ጥያቄ፣ ለፕ/ት ኦባማም ማቅረባቸውን የሚያመለክት ነው። ፕ/ት ኦባማ በመልሳቸው " ፖሊሲያችን መንግስትን በሃይል ከስልጣን ማውረድን አይደግፍም፣ ይህ ፖሊሲያችን በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ የተመረጠውን የኢትዮጵያን መንግስትንም ያካትታል" ካሉ በሁዋላ፣ "በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩብኝ ነው በማለት የሚፈርጃቸው ድርጅቶች እንዳሉ እናውቃለን፣ ይሁን እንጅ በመንግስት ላይ ተቃውሞ ቢያሰሙም የሽብር ዝንባሌ እንደሌላቸው የእኛ የመረጃና የደህንነት መረጃዎች ያሳዩናል" በማለት በኢህአዴግ መንግስት በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ተናግረዋል። "ይህንን በመገምገም በኩል ግልጽ የሆነ መስፈረት አለን ያሉት ኦባማ፣ ለወደፊቱ እነዚህ ድርጅቶች የሽብር ጥቃት ይፈጽማሉ አይፈጽሙም የሚለውን ለወደፊቱ የምናየው ይሆናል ብለዋል። " አንድ ድርጅት የፖለቲካ ተቃውሞውን ቢገልጽ ፣ ከአስተሳሰቡ ጋር ባንስማማም እንኳ ከለላ እንሰጠዋለን፣ ይሄ በአሜሪካ በሌላም ቦታ የሚሰራበት እውነታ ነው፤ ይህን ማድረግ ለዲሞክራሲ እድገት አስፈላጊ ነገር ነው " አሉት ኦባማ ፣ ድርጅቶቹ ወደ ሃይል ሲያዘነብሉና በህገመንግስት የተቋቋመን መንግስት ለመገልበጥ ሲሞክሩ፣ ድርጊቱ ያሳስበናል። " በማለት መልሰዋል። የውጭ አገር ጋዜጠኞች ፣ በእስር ላይ ስለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እንዲሁም ስለኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ለፕ/ት ኦባማና ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥበቃ እና በዲሞክራሲ ዙሪያ ከአቶ ሃይለማርያም ጋር ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን፣ አሜሪካ በቅርብ ሁና እገዛ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልጸዋል። የኢህአዴግ መንግስት ከፕ/ቱ ጉብኝት በዋናነት የሚጠብቀው ለስልጣኑ ስጋት የሚፈጥሩ ድርጅቶች በሽብረተኝነት እንዲፈረጁለት ቢሆንም፣ ይህንን ሳያገኝ ቀርቷል። ይሁን እንጅ ባራክ ኦባማ የኢህአዴግን መንግስት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ሳያስቆጣ አይቀርም። ኦባማ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየጠበበ ስለመጣው የፖለቲካ ምህዳር ሲናገሩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ የሚል ካባ ማላበሳቸው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊስን ተቃርኖ የሚያሳይ ነው። በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል ለፕሬዝደንት ኦባማ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታውቀዋል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት መንግስት ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገውን የእራት ግብዣ ያልተቀበሉት፣ ‹‹ አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ፣ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም›› ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸውም ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው›› ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡

ኢ/ር ይልቃል መንግስት ለፕሬዝደንት ኦባማ ያዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ



• ‹‹ኦባማ ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ውሃ የሚቸልስ ነው››
• ‹‹ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ››
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ ለነገረ ኢትየጵያ ገልጸዋል፡፡ የራት ግብዣው ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥሪ የተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ‹‹ አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም›› ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው›› ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል በነገው ዕለት የአሜሪካ ኤምባሲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

Tuesday, July 21, 2015

በእነ ወይንሸት ላይ የተጠየቀው ይግባኝ ውድቅ ተደረገ


መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ የቆዩት እነ ወይንሸት ሞላ ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት እንዲፈቱ ከተፈረደላቸው በኋላ ሰኔ 22/2007 አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ነበር፡፡ ይሁንና የልደታ ፍርድ ቤት ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቄራ ፍርድ ቤት በእነ ወይንሸት ላይ የወሰነውን ውሳኔ በማፅናት አቃቤ ህግ የጠየቀውን ይግባኝ ውድቅ አድርጎታል፡፡
ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ከውጭ ሆነው ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን ‹‹የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አልተቀበልክም›› በሚል ተጨማሪ አንድ ወር የተፈረደበት ማስተዋል ፈቃዱ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሆኖ ጉዳዩን ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ማስተዋል ፈቃዱ የ3 ወር እስሩን የጨረሰ በመሆኑ በዛሬው ዕለት ከእስር ይለቀቃል ተብሎ ይገመታል፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር 

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ

• ለነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጥረዋል
በእነ ዘላለም ወርቃገኘው የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው ተከሳሾቹ ሀምሌ 1/2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር በኋላ ጥቅምት 7/2006 ዓ.ም ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተገኘ የተባለ መረጃ ከአቃቤ ህግ ማስረጃዎች ማስረጃ ዝርዝርነት እንዲወጣ፣ ተከሳሾቹ ለፖሊስ መረጃ የሰጡበት መንገድና ፖሊስ የሰነድ ማስረጃዎችን የያዘበትን መንገድም አቃቤ ህግ ህጋዊ መሆኑን ስላላረጋገጠ በደንበኞቼ ላይ በማስረጃነት እንዳይያዝ ሲሉ መቀወወሚያ አቅርበው ነበር፡፡
ከተከሳሾቹ መካከል በዛሬው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹መቃወሚያው የቀረበው ከተከሳሾች እጅ ተገኙ የተባሉት ማስረጃዎች በህጋዊ መንገድ የተገኙ ስለመሆናቸው አቃቤ ህግ በማስረጃ ስላላረጋገጠ ነው›› ሲል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን እንዲቀበለው ጠይቋል፡፡ ሆኖም ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መቃወሚያውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በነፃ ይሰናበቱ ወይንም ይከራከሩ የሚለውን ለመወሰን ለብይን ለነሀሴ 14/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም 9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ ከጥብቅና በመታገዳቸው ምክንያት ሰባቱም ተከሳሾች በዛሬው ችሎት ያለ ጠበቃ ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ተከሰው አቶ ተማም መቃወሚያ ካቀረቡላቸው መካከል አቶ የሸዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሽ ይገኙበታል፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Monday, July 20, 2015

‹‹ፍርድ ቤቱ›› የዞን 9 ጦማርያንን ጉዳይ ማጓተቱን ቀጥሏል



አንድ አመት ከሦስት ወር በእስር ላይ ያሉትና በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው እየታየ የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን ለ31ኛ ጊዜ ዛሬ ሐምሌ 13/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ለ32ኛ ጊዜ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
መዝገቡ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው ተከሳሾች የቀረበባቸውን ክስ ይከላከሉ ወይስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ የሚለውን ለመወሰን ነበር፡፡ ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግ የደረጃ ምስክሮች ቃል በጽሑፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር አልተያያዘልኝም በሚል መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት እንዳልቻለ በመግለጽ አራቱ ጦማርያን ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ እንደገለጸው እስካሁን በ30/07/07 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወቅት የተሰሙት የአቃቤ ህግ የደረጃ ምስክሮች ቃል በጽሁፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር አልተያያዘም፡፡ በተጨማሪም ሰኔ 8/2007 ዓ.ም በአንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ በቀረበው የአቃቤ ህግ ማስረጃ (ሲ.ዲ) ላይ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን ላይ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡት አቤቱታም እንዲሁ በጽሁፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር እንዳልተያያዘ ተገልጾዋል፡፡
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ዛሬ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቅ የነበረውን ብይን በማራዘም የጦማርያኑን ጉዳይ ማጓተቱን ቀጥሏል፡፡ በዚህ መሰረትም ሐምሌ 22/2007 ዓ.ም የተጠቀሱት የምስክሮች ቃል እና የጠበቆች አቤቱታ በጽሁፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር መያያዙን ‹‹ለመጠባበቅ›› ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በዚህም በተከሳሾች ላይ የሚሰጠው ብይን ማራዘሙ ተመልክቷል፡፡ ይህን የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተከትሎ 5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ‹‹450 ቀናት በእስር ቆይተናል፤ እኛም ቤተሰቦቻችንም እየተጉላላን ነው፡፡ ይህን ከግምት በማስገባት ብይን ለመስማት አጭር ቀጠሮ ይሰጠን›› ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ለብይን ሳይሆን ‹ከመዝገቡ ጋር መያያዙን ለመጠባበቅ› ‹‹አጭር›› ያለውን ቀጠሮ ለሐምሌ 22/2007 ዓ.ም ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ሐምሌ 1/2007 ዓ.ም ድንገት የፍርድ ቤት ቀጠሯቸው ሳይደርስ ‹‹ክሳችሁ ተቋርጧል›› በሚል ከእስር የተለቀቁት ጦማርያንና ጋዜጠኞች ዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ችሎት ፊት ቀርበዋል፡፡ ተፈችዎቹ ፍርድ ቤቱ በይፋ እንዳላሰናበታቸው በማሰብ ‹‹በእነ ሶልያና ሽመልስ!›› የሚለው የዳኞቹ ጥሪ ሲሰማ በእስር ላይ ከሚገኙት ጓደኞቻቸው ጋር ከመቀመጫቸው በመነሳት ችሎት ፊት የቀረቡ ሲሆን፣ ዳኞቹ በመካከልም ‹‹የሌሎቻችሁ ክስ ተቋርጧል›› በማለት አልፈዋቸዋል፡፡
ሆኖም ግን አምስቱ ተፈችዎች ለእስር በተዳረጉበት ወቅት ቤታቸው ሲፈተሽ በኤግዚቢትነት እና በሰነድ ማስረጃነት በፖሊስ የተያዙባቸው እቃዎቻቸው እንዲመለሱላቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ማቅረባቸው ተገልጾዋል፡፡ ተፈችዎቹ አቤቱታቸውን ቀደም ብለው በጽ/ቤት በኩል አስገብተዋል፣ ፍርድ ቤቱም አቤቱታቸው እንደደረሰው በመግለጽ ትዕዛዝ እንደሚሰጥበት አስረድቷል፡፡
በዛሬው የችሎት ውሎ ከቂሊንጦ እስር ቤት የቀረቡት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አቤል ዋበላ ያለውን ኢ-ፍትሃዊነት ለመቃወም ጥቁር ቲሸርት ለብሰው ፍርድ ቤት ለመቅረብ ሞክረው የነበር ቢሆንም በእስር ቤቱ አስተዳደር መከልከላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የዛሬውን የፍርድ ቤት ውሎ በርካታ የጦማርያን ወዳጆች፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ጋዜጠኞችና ዲፕሎማቶች ተከታትለውታል፡፡ በቅርቡ የእስር ጊዜዋን አጠናቅቃ ከእስር የተፈታችው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙም ችሎቱን ታድማለች፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
አራቱ በእስር ላይ የሚገኙት ጦማርያንን እና ቤተሰባቸውን በማጉላላት እና ፍትህ በመንፈግ የሚሰበር ሞራል የላቸውም ፡፡ ሆነ ተብሎ በሚደረገው በዚህ የፓለቲካ ውሳኔን የመጠበቅ ሂደት የሚባክነው የወጣቶች እድሜ አሁንም ባይሆን አንድ ቀን የህሊና ዋጋ እንደሚያስከፍል ለዳኞች ለማስታወስ እንወዳለን፡፡ ቀላሉ እርምጃ ቀሪውን የሌለውን ማስረጃ በመመርመር ሰበብ ከማጉላላት ይልቅ አራቱን ጦማርያን መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ማሰናበት ነው ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ባለፈው አንድ አመት ከሶስት ወር አጋርነታችሁን ላሳያችሁ በዛሬው ብይን ወቅትም ከፍተኛ ድጋፍ ስትሰጡን ለነበራችሁ የዞን9 ነዋርያን ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
Source: Zone9

Saturday, July 18, 2015

የማስመሰል ክህሎቱን ያጣው ስርዓት:- መቶ በመቶ አሸንፌያለሁ የማለት ጉዳይ

በኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣ ላይ “ኢህአዴግ ለምን መቶ በመቶ ውጤት ደፍኖ ለማሸነፍ ፈለገ” ለሚል ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ፤ (የተወሰነ ማስተካከያ እና ጭማሪ ጋር)
እኔ እንደምረዳው በዋናነት አንድ ሥርዓት ወደ ማብቂያው አፋፍ ላይ ሲቃረብ፣ የማስመሰል ክህሎቱን ያጣል፡፡ ለዚህ አመለካከት ብዙ የታሪክ ምሳሌዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
በቅድሚያ፣ ኢህአዴግ ከደርግ የሚለይበት አንድ ወሳኝ ነገር ነበር፡፡ ደርግ ማስመሰል ላይ ደካማ ሲሆን ኢህአዴግ ማስመሰል ላይ በጣም የተካነ ነበር፡፡ አሁን ጊዜው እያለፈ ሲሄድ፣ ኢህአዴጎች ማስመሰል እየተሳናቸው መጥቷል፡፡ ማስመሰል ለማንኛውም የፖለቲካ ስርዓት አብሮ የሚጓዝ አካል ነው፡፡ ወደ ተነሳንበት ጥያቄው ስንመለስ፣ አገኘን የተባለውን የውጤት ጠንጠረዥ በምንመለከትበት ጊዜ በህዝብ ተቀባይነት ይኖረዋል ብለው ማመናቸው፣ ለማስመሰል መሰጠት ያለበትን አተኩሮ እና ችሎታ በእጅጉ እንዳጡት ማሳያ ነው፡፡

በዚህ ብቻ ሳይሆን፣ በሰሜን አፍሪቃ እና በአረብ አገር ኢትዮጵያውያን ስደተኖች በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ እና ዜናው እንደተሰማ፣ የመንግሥት ሹመኞች ስለተፈጸው ዘገናኝ ሁኔታ በነበራቸው አቀራረብ ብዙ ሰዎች በእጅጉ አዝነዋል፡፡ እነሱ ከነገሩ ክብደት ይልቅ ፖለቲካቸውን በማስቀደም የሀዘን ስሜት እንኳን እንዳደረባቸው ለማስመሰል አልቻሉም፡፡በማግስቱ፣ህዝቡ በራሱ ተነሳስቶ፣ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ‹‹አይ የነገን እለፉንና እኛ እራሳችን ሰልፍ እንጠራለን ብለው፣ የሆነው ነገር ሆኗል፡፡ ለማጠቃለልም መቶ በመቶ አሸንፈናል ብለው ሲወጡ፣ ለፖለቲካ ግብዓት ሊያግለግል የሚችለው የማስመስል ዘይቤ እንኳን እንዳጡት መረዳት አያዳግትም፡፡
በሁለተኛ ደረጃ፣ ከዚሁ ጋር በማያያዝ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በህይወት በነበሩ ጊዜ፣ ያለምንም ጥርጥር የተለያዩ የመንግሥት ዘርፎች ሁሉ፣ በሳቸው መዳፍ ሥር የወደቁ ነበሩ፡፡ በእርግጥ፣ እሳቸውን የተካ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኖረንም ቅሉ፣ የሥርዓቱን ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች እንደሚረዱት፣ በሥርዓቱ ውስጥ የኃይል ትንቅንቅ እና በተቋማት መካከል ልዩነትን እና ጥቅምን ያዘለ ግብግብ አለ፡፡ የክፍፍሉን አሰላለፍ በምንመለከትበት ጊዜ የሚከተለውን ረድፍ እናያለን፤ ሠራዊቱ ለብቻው ሄዷል፤ ደህንነቱና ጸጥታው በሌላ በኩል እየሄደ ነው፡፡የተዳከመው ፓርላማም ቢሆን አልፎ አልፎ ለብቻው አቋም ይዞ ይንቀሳቀሳል፡፡ ከዛ ደግሞ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች አሉ፡፡ በመጨረሻም ደግሞ የክልል አስተዳዳሪዎች አሉ፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ጊዜ ስራዓቱ በሠራዊቱ፣ በጸጥታው ፣ በፓርላማው እና በከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮቹ መካከል ክፍፍል እና ክፍተት አለው፡፡
አገሪቱ ያለችበትን የፖለቲካ ድባብ ለማየት ስንሞክር ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ህልፈት በኋላ ፣ ሁሉንም በበላይነት አጠቃልሎ የሚይዝ ፈረንጆቹ ‘Strong Man’ የሚሉት ‘ጠንካራ ክንድ’ ስራዓቱ ገና አላወጣም፡፡ ስለዚህ፣ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ጊዜ እንደሚያደርጉት፣ መክረው-ዘክረው እንደዚህ ያለ ቁጥር ያስፈልገናል፤ በእንደዚህ ያለ ቦታ እንዲህ እናሸነፋለን፣ በዚህ ቦታ ደግሞ እንዲህ እንይዛለን የሚል ኢህአዴግአዊ የጋራ ሥምምነት ፈጥረውና ስትራቴጂ ነድፈው መቅረብ አቅቷቸዋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ፣መንግስት ደጋግሞ ሊያሳምነን የሚፈልገው አገሪቱ በአለም ደረጃ ከሚገኙት ግዙፍ የፋይናንስ ተቋማት ብር የመበደር አቅሟ ጨምሯል፡፡ ከዚህም ጋር በማያያዝ የዓለም አቀፋዊ ተቋማት አስተያየትና ነቀፊታ እምብዛም አያሳስበንም ብለው ያምናሉ፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የምዕራቡ ዓለም ብቻ ሳይሆን “ቻይናም አለችን” የሚለው አመለካከታቸው እየተጠናከረ መጥቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለማደጋችን እንደማሳያ የሚያቀርቡት፣ “የዓባይ ግድብ ግንባታ በራሳችን አቅም እየገነባን” እንገኛለን የሚል ነው፡፡ ከአሁን ወዲህ ዴሞክራሲ እና ሰብዓዊ መብት አያያዝ ብሎ ሊያስተምረን የሚሞክረውን ማንኛውንም ተቋም አንቀበልም ወደ ማለት ተደርሷል፡፡

በአንጻሩ መዳኘት ያለብን ዴሞክራሲ በማምጣት፣ ሰብዓዊ መብት በማስጠበቅ፣ በአጠቃላይ ነፃነትን ለኢትዮጵያ ህዝብ በማጎናጸፍ ሳይሆን ፈረንጆቹ ‹‹ግብራዊ ቅቡልነት›› (Performance Legitimacy) በሚሉት፣ ‹‹በምንሰራው ልማት፣ በምንሰራው የሸንኮራ አገዳ ፋብሪካ፣በምንገነባው ግድብና መንገድ… ወዘተ ነው፡፡››
ለነገሩ የህዝብ ቁቡልነትን ለማገኘት ሙከራ ብናደርግም ይሁንኑ ማሳካት ቢሳነን ሠራዊቱ፣ ደህንነቱ እና ኢኮኖሚው በእጃችን ስለሆነ እምብዛም አሳሳቢ ሆኖ አናገኘውም ብለው ያምናሉ፡፡የውጭውን ዓለም በሚመለከት ከቻይናም ባሻገር የምዕራብ ዓለሙን ጥቅም የምንገዳደር ስላልሆንን ዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብት አላከበራችሁም ብለው ጠንከር ያለ ጫና አያሳድሩብንም፡፡
ስለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ በምንነጋገርበት ጊዜ፣መንግሰት አቃሎ እንደሚያቀርበው ሳይሆን ቢያንስ ቢያንስ የአምስት ዓመቱን የፖለቲካ ድባብ፣ ነጻ የፍትህ ተቋም፣ የመናገርና የመሰብሰብ መብት እና ገለልተኛ የምርጫ ቦርድን ያካትታል፡፡
በምርጫው ሂደት ተገኘ የተባለውን ቁጥር ስንመለከት ግን አውሮፓውያን እንደሚሉት ‹‹የመሽን ፖለቲክስ›› ውጤት ነው፡፡ ‹‹የመሽን ፖለቲክስ›› ሲባል ከዚህ በታች የሚከተለው ባህሪያት ያካትታል፤ ሀገሪቱን በአንድ ለአምስት በማደራጀት እና በመጠርፍ “መሽኑ” ቁጥር ፈብርኮ እንዲያወጣ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ በፊት ደጋግመው በየክልሉ በዓመት ለስልሳ ቀናት ያህል ገበሬውን ለአካባቢ ጥበቃ በሚል ሰበብ ያለምንም ክፍያ በቁጥር እያሰለፉ ሲያስወጡት ከርመዋል፡፡ ይህኑኑም ተሞክሮ፣ “መሽኑ” ካርድ ለማስወሰድም ተጠቅሞበታል፡፡ ይህንን ካደረጉ በኋላ በአንድ ሳምንት ውስጥ 36 ሚሊዮን ህዝብ መመዝገቡ “የሃገሪቷን የዲሞክራሲ እድገት አመላካች ነው” በማለት አቅርበዋል፡፡
እነሱ እንደሚያቀርቡት በሳምንት የተጠቀሰው ቁጥር በፍላጎትና በራስ ተነሳሽነት ካርድ የወሰደ ቢሆን ኖሮ በእርግጥም ሃገራችን በዴሞክራሲ የተናወጠች ናት ማለት ነው፡፡ የተባለው ዲሞክራሲ ካለም ህብረተሰቡ በትራንስፖርት፣ በካፌቴሪያ፣ በመዝናኛ ቦታዎች…ወዘተ ላይ የተሟሟቀ የፖለቲካ ውይይት እና ክርክር ሲያደርግ ይስተዋል ነበር፡፡
ለነገሩ ጋዜጣው ላነሳው ምልከታ የመሰለኝን አተያይ ለማቅረብ ሞከርኩ እንጂ ምርጫን በሚመለከት በእኔ በኩል ተገቢ እና ወሳኙ ጥያቄ የሚከተለው ነው፡፡ በእርግጥ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ ስርዓት ተዘርግቷል ወይ? በተጨማሪም ዲሞክራሲያዊ ሃገራት እንደሚያደርጉት እና እንደሚረዱት በኢትዮጵያ ምድር ላይ “ምርጫ” ይቻላል ወይ? ለዚህ ጥያቂ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ከተቻለ በእርግጥ ስለቀረበው ውጤት የፖለቲካ ትንተና ማቅረብ ይቻላል፡፡ በእኔ በኩል ግን ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ ተገቢ እና በቂ የሆነ ሁኔታ (Condition and possibility) አለ ብዬ አላምንም፡፡

ኦባማ የሚመጣው ለማን ነው?



ጌታቸው ሺፈራው
አሜሪካ ከኃይለስላሴ መንግስት ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ቢሆንም ከአሁኑ አንጻር ሲታይ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች አዲስ አበባ ድረስ መጥተው እንዲጠበቅላቸው የሚፈልጉት እንቅልፍ የሚነሳ ስጋት ነበራቸው ለማለት ግን ይከብዳል፡፡ ያም ሆኖ ግን በወቅቱ ለጥቁር ምቹ ባልነበረችው አሜሪካ ለጥቁር ህዝብ ነፃ መውጣት ስትባዝን የነበረችው ኢትዮጵያ መሪን ከዛሬዎቹ ገዥዎች በተሻለ በክብር አሜሪካን እንዲጎበኙ ጋብዛቸዋለች፡፡ ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ኢትዮጵያን የሚጎበኙበት ምክንያት አልነበረም፡፡ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ኢትዮጵያን መጎብኘት የነበረባቸው ባለፉት 24 አመታት ነው፡፡ ራሳቸው በተቋሞቻቸው አግዘው ወደ ስልጣን ያመጡትን ህወሓት/ኢህአዴግ ስራ ያለችውን ኢትዮጵያ ቢጎበኙ ብዙም አይገርምም ነበር፡፡ ሆኖም እነ መለስን ‹‹አዲሶቹ›› እያሉ ሲያንቆለጻጽሱ የነበሩት እነ ክሊንተን እንኳ በህወሓት/ኢህአዴግ ስር ያለችውን ኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ሆነው መጎብኘት ያልፈለጉት የራሳቸውን ክብር ዝቅ ስለሚያደርግባቸው ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግም እነሱ ባመኑት መልኩ እንኳ አላገኙትም፡፡ የሰብአዊ መብት፣ ዴሞክራሲና መሰል ቅድመ ሁኔታዎች ጭራሹን ሲሸረሸሩ ከኦባማ አንጻር ሲታይ በጡንቻ የሚያምነው ቡሽ እንኳ በርካታ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰባሰቡበት አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ ከመምከር የሚፈልጓቸውን መሪዎች ሀገራቸው ድረስ እየሄዱ ማውራትን መርጠዋል፡፡ ሶማሊያ ውስጥ እንዲዘፈቅ የወከሉትን የህወሓት/ኢህአዴግን መሪዎች አሜሪካ ድረስ ጠርተው ከማነጋገር ባለፈ አዲስ አበባ ውስጥ እጃቸውን ሊጨብጧቸው አልፈለጉም፡፡ ይህም የሆነው የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅም ቢሆን አስጠርተው እንጅ የአምባገነኖቹ ቤተ መንግስት ድረስ መምጣት የሚጠይቋቸውን ተቋማት ለገነቡት፣ ሚዲያና ህዝባቸውን ለሚያዳምጡት አሜሪካኖች ክብር የሚቀንስ በመሆኑ ነው፡፡ ግን ደግሞ የግድ ለሀገራቸው ጥቅም አስፈላጊ ሲሆን አሜሪካኖች ሀፍረታቸውን ዋጥ አድርገው ከአምባገነን ጋር ይቆማሉ፡፡
ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ መሆኑ ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ በዋነኛነት ሶስት አይነት አስተያየቶች እየተሰጡ ነው፡፡ አንደኛው የማህረሰብ ክፍል ኦባማ መጣ አልመጣ የሚመጣ ለውጥ የለም የሚል ነው፡፡ በቅርቡ ተደርጎ የነበረው የ‹‹3ኛው ፋይናንስ ለልማት ኮንፈረንስ›› ትራፊክ ያጨናነቀበት ሳይቀር ‹‹እሱ መጣ አልመጣ ምን ለውጥ ይመጣል!›› እያለ ትርፉ የትራፊክ መጨናነቅ ብቻ መሆኑን ታክሲ ውስጥም የሚሰጠውን አስተያየት ሳይቀር ታዝበናል፡፡ ሌላኛው ደግሞ ኦባማ መምጣቱ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠት መሆኑን በመግለጽ መምጣቱን የሚቃወም ነው፡፡ ሶስተኛው ደግሞ የኦባማ መምጣት ሀገሪቱ በእድገት ጎዳና መሆኗን የሚያሳይ ብስራት ነው የሚል ነው፡፡ የእኔ ከሶስቱም ይለያል፡፡ ኦባማ ለኢህአዴግ ሲል አልመጣም፣ ኦባማ ኢትዮጵያ በማደጓ ምክንያት አልመጣም፡፡ ኦባማ የሚመጣው በስርዓቱ አፈና ምክንያት ኢትዮጵያ ወደ አደጋ እያመራች በመሆኑ፣ በዚህም የአሜሪካ ጥቅም አደጋ ውስጥ ስለሚገባ ነው፡፡ ኦባማ በመምጣቱ ከተጠቀምንባቸው አወንታዊ፣ ካልተጠቀምንባቸው አሉታዊ ወይንም በዛው የሚረግጡ ጉዳዮች/ጥቅሞች ይኖራሉ፡፡
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ነች፡፡ ቻይና ከምዕራባውያን እየነጠቀቻት ያለች ሀገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ በህዝብ ቁጥር ሁለተኛ ሀገር ነች፡፡ ኢትዮጵያ የሶማሊያ፣ የሱዳን፣ የደቡብ ሱዳን፣ የኤርትራ፣ በደህንነት በኩል የደካማዋ ኬንያ ጎረቤት ናት፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ባራክ ኦባማ አይነት ጥቁር መሪ ሊኮራባት የምትገባ ታሪካዊም ሀገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ ለአሜሪካ በርካታ ምሁራንና የዳያስፖራ ቁጥር ያላት ሀገር ናት፡፡ ምናልባት በመካከለኛው ምስራቅ እስራኤልና ሳውዲ እንዳሉት ሁሉ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከዛም አለፍ ሲል በአፍሪካ ለአሜሪካ ታሪካዊ የረዥም ጊዜ ወዳጅ ልትሆን የምትችል ሀገርም ናት፡፡ ታዲያ ባለፉት 24 አመታት የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ለምን ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም? ያልፈለጉት ስርዓቱን ነው ሀገሪቷን? ለእኔ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹን የሚከስባቸው ኒዮሌብራል፣ አሸባሪ፣ የቀለም አብዮተኛ አይነት እነ አሜሪካን ከበስተጀርባ ያስቀመጡ ፍረጃዎች፣ እንዲሁም የአሜሪካ መንግስትና ተቋማት በስርዓቱ ላይ የሚያነሱት የሰብአዊ መብት ክስ በኢህአዴግና በአሜሪካ መካከል ያለውን ቅራኔ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ከኢትዮጵያ ርቀው የቆዩት በኢህአዴግ ምክንያት ለመሆኑ ዋነኛው ማሳያ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ስርዓቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ ይለወጣል ብለው ጠብቀውታል፡፡ ሀገሪቱ አደጋ ውስጥ ከመግባቷ በፊትም አስተማማኝና አማራጭ ኃይል ይመጣል ብለው ተስፋ አድርገው ነበር፡፡
አሁን ግን ስርዓቱም መሻሻል አልቻለም፡፡ ከኢትዮጵያ ህዝብ በላይ የራሳቸውን ጥቅም የሚጎዳ አዝማሚያ እየታየ ነው፡፡ ኢህአዴግ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ሲል፣ ከ24 አመት በኋላ የትጥቅ ትግል እንደገና በአዲስ መልክ እንዲያውም ዋና መስሪያ ቤቱን አሜሪካ ባደረገ ድርጅት ሲጀመር ለአሜሪካኖች ትልቅ የማንቂያ ደወል ነው፡፡ በዚህ ሰዓት በኢህአዴግ አምባገነንነት ምክንያት ኢትዮጵያን ማጣት አይፈልጉም፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ እንደ ሶማሊያም እንደ ሱዳንም፣ እንደ ኬንያም ብቻ የምትታይ ሀገር አይደለችም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር ከተፈጠረ አፍሪካ የብጥብጥ ቀጠና እንደሚሆን፣ መካከለኛውን ምስራቅ ከአፍሪካዎቹ ነውጠኞች ጋር የሚያገናኝ የሽብር ቦይ እንደሚከፈት ያውቁታል፡፡
በአሁኑ ወቅት የመን እየተበጣበጠች ነው፡፡ ከየመን ጋር በሰፊ ባህር የምትገናኘውና የበርካታ ሀገራት ሰራዊት ቢላክም ያልተረጋጋችው ሶማሊያ ጋር ትገናኛለች፡፡ ከመካከለኛው ምስራቅም ጭምር የሚመነጨውን የሶማሊያን ችግር በዋነኝነት ትቋቋማለች የምትባለው ኢትዮጵያ ነች፡፡ የመንና ሶማሊያ በፈራረሱበት ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር ቢደርስ ይህ ችግር ሙሉ አፍሪካን ያዳርሳል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሶማሊያን ያለውን ችግር የሚመክት ሀገር ስለሌለ ብቻ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የሶማሊያን ስደተኞች የምትቀበል ሀገር ነች፡፡ በሌላ ጎኗ ደግሞ ደቡብ ሱዳን አለች፡፡ ደቡብ ሱዳን በአንድ በኩል ‹ሎርድ ሪዚስታንስ አርሚ› የሚፈነጭበት ሰሜን ዩጋንዳ፣ በሌላ በኩል ከምትበጣበጠው ኮንጎ በአንድ በኩል ደግሞ ከዳርፉር ጋር ደቡብ ሱዳን ሌላኛዋ የሁከት አገር ማዕከላዊ አፍሪካም ጎረቤት ነች፡፡ ደካማዋ ቻድ የማዕከላዊ አፍሪካም የሱዳንም አጎራባች ስትሆን ይህን መስመር ቦኮሃራም የሚንጣት ናይጀሪያና የሰሜን አፍሪካው የአልቃይዳ ክንፍ መነሃሪያ ለሆኑት ሊቢያና ኒጀር ጋር ትገናኛለች፡ የመንና ሶማሊያ እንዲሁም ደቡብ ሱዳን መካከል ኢትዮጵያ የምትባል ታኮ ከሌለች አልሸባብ እስከ ሊቢያ፣ ቦኮሃራምና የሰሜን አፍሪካ አልቃይዳ እስከ ኪስማዩ ከዛም አልፎ እስከ የመን የሚፈነጩበት መስመር ወለል ብሎ ይከፈታል፡፡ ኢትዮጵያ በአፈናው ምክንያት ችግር ውስጥ ከወደቀች፣ አሸባሪዎች ከየመን ሊቢያ የሚንሸራሸሩበት፣ አፍሪካን ዋና መረማመጃቸው የሚያደርጉበት ክፉ ምልክት እየታየ ነው፡፡ ወቅቱ ደግሞ ኦባማ በየአካባቢው በአሸባሪዎች ጥቅሟ የሚነካባት፣ የዓለም ፖሊስ የሆነችው አሜሪካ ፕሬዝደንት የሆነበት ነው፡፡
ወቅቱ የጣለበት ኃላፊነትና አጣብቂኝ እንዳለ ሆኖ ኦባማ ከሌሎች ፕሬዝደንቶች የሚለየው የቆዩቱ የሚኮፈሱበትን ጉዳይ ሰብሮ ግንኙነት በመጀመር ነው፡፡ ለዚህም ‹‹እኔ ከመወለዴ በፊት የነበረ ጦርነትን ውስጥ ገብቼ መነታረክ አልፈልግም›› ብሎ ግንኙነት የጀመረባት፣ ከ55 አመት በኋላ ኤምባሲ የከፈተባት ኩባ ትልቅ ምሳሌ ነች፡፡ በዚህ ወቅት ግን የኩባን መሪዎች መክሮና ዘክሮ ኩባን ከማራቅ ይልቅ ወደ አሜሪካ እንድትቀርብ የራሱን ጥረት አድርጓል፡፡ ‹‹ብዙ ጊዜ ራሳችንን ከማሳመን ባለፈ ጉዳይ ውስጥ ስናስገባ የሚብሰን መዘዙ ነው›› ነበር ያለው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ሌላ መዘዝ በሚያመጣ ጉዳይ ለስርዓቱ መፍትሄ ከመስጠት ከሰሙ እኔ እግረ መንገዴን ሄጀ ላነጋግራቸው የሚል አቋም እንዲይዝ ተገድዷል፡፡ ግብፅ ውስጥ እንዲያውም ሌሎቹ ‹‹አክራሪ›› የሚሏቸው ባዘጋጁት መድረክ መጥቶ ታሪካዊ ንግግር ሲያደርግ ማስጠንቀቂያም የግንኙነት አረንጓዴ መስመርም እያሳየ ነበር፡፡ ውየስት ባንክን ሲጎበኝ ለአሜሪካ በጎሪጥ ለማትታየው እስራኤልም ለሙስሊሙ ዓለምም መልዕክትም፣ ማስጠንቀቂያም አስተላልፏል፡፡ ከኢራን ጋር ቁጭ ብሎ ተደራድሯል፡፡ እነዚህ አብዛኛዎቹ ሌሎች ያልደፈሯቸው ከገባቸው ግንኙነታቸውን የሚያድሱበት፣ ካልገባቸው ማስጠንቀቂያ የሰጠባቸው ናቸው፡፡ ኢህአዴግም የሚሰጠው የመጨረሻ እድል ወይንም ማስጠንቀቂያ ነው፡፡
ኦባማ ካለፉት የአሜሪካ ፕሬዝደንቶችም፣ በዓለም በወቅቱ ካሉት ፕሬዝደንቶችም በላይ በርካታ ሀገራትን የጎበኘ ፕሬዝደንት እንደሆነ ይነገራል፡፡ የአሜሪካ መከላከያ ሰራዊት ያለባቸው ኢራቅና አፍጋኒስታን ከሁለት ጊዜ በላይ ተመላልሷል፡፡ ወደ እነዚህ አገራት ሲሄድ በሌላ ስብሰባ ምክንያት ሳይሆን በቀጥታ ነው፡፡ በእርግጠኝነት ኢትዮጵያ ሶማሊያ ውስጥ አሜሪካን ወክላ ባትገኝና የአሜሪካ ሰራዊት ሶማሊያ ውስጥ ቢሆን ኖሮ ኦባማ ከአንዴም ሁለቴ ወደ ሞቃዲሾ ማቅናቱ የማይቀር ነበር፡፡ አሁን ባለው አዎንታዊ ሁኔታ ግን ሶማሊያ ብቻ ሳትሆን ኢትዮጵያም በህወሓት/ኢህአዴግ አፋኝነት ምክንያት የባሰ ችግር ውስጥ እየገባች በመሆኑ የኦባማ አስተዳደር ገንዘብ ደጉሟቸው ሪፖርት የሚያወጡት ተቋማት በየጊዜው እያወጡት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለመውደቅ ስጋት ላይ ያለች ሀገር ነች፡፡
በመሆኑም ይች አፍሪካ የቀጠና ዞን እንዳይሆን ታኮ የሆነችው ሀገርን ሳትፈርስ ደርሰው፣ አሜሪካ ውስጥ ጠርተው፣ መልዕክተኛ ልከው ያስመከሯቸውን የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች ኢትዮጵያ ድረስ መጥተው ቢገባቸው መምከር ነበረባቸው፡፡ ይህን ሲያደርጉም በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ መምጣትን አልፈለጉም፡፡ የሚያዙት አምባገነን ስርዓት ጋር ለመጨባበጥ ምክንያት አስፈልጓቸዋል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ! ያውም ኬንያ ውስጥ ለሌላ ስብሰባ ከመጡ በኋላ እግረ መንገዳቸውን፡፡ ኦባማ በቀጥታ ኢትዮጵያን ቢጎበኝ እንኳ የሚገርም አይደለም፡፡ ኦባማ ጆርዳን፣ ትሪንዳድና ቴቬጎ፣ ጃማይካ፣ ኮስታሪካ፣ ታንዛኒያን እና ሴኔጋልን የመሳሰሉ ትንንሽና ለሀገሪቱ ጥቅም ከኢትዮጵያ አንጻር ይህን ያህል ጥቅም አላቸው የማይባሉ ሀገራትን ጎብኝቷል፡፡ ከእነዚህ መካከል ከአሜሪካ ጎን የምትገኘውን ጃማይካን ጨምሮ አብዛኛዎቹን ሀገራት ሲጎበኝ ስልጣን ላይ ያለ የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ነው፡፡ ባለፉት አመታት ኢህአዴግ ጋር እጅ መጨባበጥ አሳፋሪ ሆኖ ሌሎች ባለመምጣታቸው፣ አሁን ግን የማይታለፍ ሁኔታ ላይ በመደረሱ ኦባማ ኢትዮጵያን የጎበኘ የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ሆነ፡፡ ‹‹በእድገቱ ምክንያት ነው›› የሚባለው ግን ውሃ የማይቋጥር ምክንያት ነው፡፡ አብዛኛዎቹን ትንንሽና የኢትዮጵያን ያህል በርካታ መሪዎችን በአንድ ጊዜ የማይገኙባቸው፣ የኢትዮጵያን ያህል ጥቅማቸውን የማያስጠብቁ ሀገራትን የጎበኘው በመጀመሪያው የስልጣን ዘመኑ ሆኖ ኢትዮጵያን ከሁለተኛ ዙር ስልጣኑ በኋላ (ያውም ሊያልቅ ሲል በጥድፊያ) ለመጨረሻ ጊዜ መጎብኘቱ አሜሪካኖች ይችን ማጣት የማይፈልጓትን ሀገር ለመጎብኘት የከለከሏቸው በርካታ ምክንያቶች እንደነበሩ በጉልህ የሚያሳይ ነው፡፡
ኦባማ ለኢኮኖሚ፣ ለፖለቲካዊና ለደህንነት ጉዳይ ሲባል ኢህአዴግ የሚገዛትን ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ኢህአዴግን የምታግዘውን፣ ከምዕራባውያን እንዲያፈነግጥ አይዞህ የምትለውን ቻይናንም ጎብኝቷል፡፡ በአምባገነንነት ከሆነ ሳውዲ የሚባል ጋዜጠኛና ሌሎች ጥያቄ የሚያነሱትን በጅራፍ የሚገርፍ፣ አሰቃቂ ግድያ የሚፈፅም ሀገርንም በተደጋጋሚና በቀጥታ ጎብኝቷል፡፡
በርማ ወይንማ ማይናማር በዓለም የሰብአዊ መብት በመጣስ ከሚታወቁት አስር አገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ በወታደራዊ አገዛዝ ስር የሆነችው በርማ ኢህአዴግ ውስጥ ካለችው ኢትዮጵያ ቢበዛ እንጅ የማያንስ በደል የሚፈፀምባት ሀገር ናት፡፡ በርማ ድረስ ሄዶ ከገዥዎቹ ጋር መጨባበጥም ኢትዮጵያ ውስጥ መጥቶ ከኢህአዴግ መሪዎች ጋር የመጨበጥን ያህል ለአሜሪካውያን የሚያሳፍር፣ የሚያስተች ነው፡፡ የበርማ መንግስት ከዜጎች መሬት በመንጠቅ ለውጭ ባለሀብቶች ይሰጣል፡፡ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የመከላከያ ሹሞችና ሌሎችም ባለጊዜዎች ነዋሪዎችን ከቤትና ቀያቸው በማፈናቀል የራሳቸውን ንብረት የሚያካብቱባት ሀገር መሆኗንም ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሪፖርቶች ያመላክታሉ፡፡ ስርዓቱን የሚተቹ በገፍ የሚታሰሩበት አገርም ነው፡፡ ዘመናዊ ባርነትም በስፋት የሚታይበት ሀገር ነው፡፡ ህፃናትን ለቁፋሮ ብቻ ሳይሆን ለመከላከያም ይለምላል፡፡ ከ70 ሺህ በላይ የሰራዊቱ አባላት ከ15 አመት ጀምሮ እስከ 18 አመት እድሜ ያላቸው ናቸው፡፡ በየእስር ቤቱ እስረኞች በአሰቃቂ ሁኔታ የሚገረፉበት ሀገርም ነው በርማ፡፡ የዘር ማፅዳት በተለይም ሙስሊሞች በአደባባይ የሚታረዱበት ሀገር ነው በርማ፡፡ መከላከያው እንደ ፈቀደ ሰው የሚገድልበት ሀገር ነው በርማ፡፡ ይህን ሀገር ግን ኦባማ ለሁለት ጊዜ ያህል ጎብኝቷል፡፡
ምንም እንኳ የበርማ ወታደራዊ አገዛዝ በሙስናም በምንም ብሎ የውጭ ባለሀብቶችን እየጠራ ሰፋፊ መሬትን በመስጠት፣ ግድቦችን በመስራት ልማት እያፋጠንኩ ነው ቢልም ኦባማ ግን ሁለት ጊዜም መሪዎቹን ያገኘው ለመምከርና ለመውቀስ ነው፡፡ ሳን ሱ ኪ የተባለችውን የተቃዋሚ መሪ ጨምሮ በርካቶችን በማሰቃየት ሀገሪቱን ወደ ብጥብጥ ሊያመራት ነው ብለው ስለፈሩ እዛው ቦታው ድረስ ሄደው ምክር ለግሰዋል፡፡ ይህ የሆነው ከእጃችን ትወጣለች ወዳሏት ኢትዮጵያ ከመውጣቱ ከሶስት አመት በፊት ነው፡፡
የአሜሪካ መንግስት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣበት ዋነኛ ምክንያት የደህንነት እንደሆነ ገልጾአል፡፡ ከዚህም ባሻገር ኢህአዴግ ያለ መረጃ ያሰራቸውን ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያንና ተማሪዎች በአጋጣሚ መፍታቱ ኦባማ የኢኮኖሚ እድገቱ አማልሎት ሳይሆን ኢህአዴግ እየሄደበት ያለው መንገድ የተሳሳተ በመሆኑ የፖለቲካ ማሻሻያዎች እንዲያደርግ ለመገሰፅ እንደሚመጣ ምስክር ሆኗል፡፡ ኦባማ የሚያዘውንና ይፈርሳል ብሎ የሚፈራውን ሀገር ብቻ ሳይሆን አሜሪካም ለውጦችን እንድታደርግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ አውሮፓ ውስጥና በሌሎች አካባቢዎች ያሉ ሚስጥራዊ እስር ቤቶችን እንዲዘጉ አድርጓል፡፡ የቀደሙት መሪዎች የማይደፍሩት የጓንታናሞ ጉዳይ የተደፈረው በኦባማ ነው፡፡ ዴሞክራሲያዊ በምትባለው አሜሪካ ለብሄራዊ ጥቅሟ ስትል በሌሎች ላይ የምታደርገውን እንድትቀንስ እየሰሩ ያለው ኦባማ ታዛዥ መንግስታት ለስልጣን ሲሉ በህዝባቸው ላይ የሚፈፅሙትን እንዲቀንሱ እየወተወተ ነው፡፡ የሀገራቱ የፖለቲካ ቡድኖችና ሌሎችም የለውጥ አካላት የበኩላቸውን ሲያደርጉ ለአሜሪካ ምቹ ይሆናል፡፡ በእርግጠኝነት ለኢትዮጵያውያን ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ የኦባማ መምጣት ሲሰማ ጥቂቶችን የፈታው ኢህአዴግ ሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ አሁን ካለው የተሻለ እንቅስቃሴ ቢኖር ይበልጡን ተገዶ ሌሎች ማሻሻያዎችን የማያደርግበት ምክንያት የለም፡፡
ያም ሆነ ይህ ኦባማ ላክ ሲባል ጦር የሚልከውን ኢህአዴግን ብሎ ቢመጣ ኖሮ ከ9 አመት በፊትም በመጣ ነበር፡፡ ጋና፣ ሴኔጋል፣ ኤልሳቫዶር፣ ጃማይካ ከመሄዱ በፊት ደግሞ ደጋግሞ ኢትዮጵያ በጎበኘ ነበር፡፡ የቀድሞዎቹ ፕሬዝደንቶችም በመጡ ነበር፡፡ እንዲያውም በዚህ በፈራረሰ ቀጠና መሪዎችን ሰብሰብ ብለው ወደ ሚያገኙባት ኢትዮጵያ ሌሎች ፕሬዝደንቶችም ያልመጡት ኢህአዴግ መልዕክት ተልኮበት፣ አሊያምና ቶሎ ተብሎ ከመምከር የበለጠ ክብር የማይሰጠው ሆኖ ስላገኙት ነው፡፡ በዚህም ከኢህአዴግ ጋር መቆም ስላፈሩ ብቻ ከሚፈልጓት ኢትዮጵያ ርቀዋል፡፡ አሁን ደግሞ የሚያልፈው ኢህአዴግ የማያልፍ ዕዳ እንደሚያመጣ፣ መራቁም መፍትሄ እንደማይሆን ተገንዝበዋል፡፡ ለመምከርና ለማስጠንቀቅም ወስነዋል፡፡
የአካባቢው ሁኔታ፣ የኢህአዴግ የቀልድ ምርጫ በመልዕክተኛም የሚያልቅ አልሆነም፡፡ ጭራሹን ኢትዮጵያ አደጋ ላይ መሆኗን የሚያመላክት እንጂ! በመሆኑም ሚዲያዎቻቸው፣ ተቋሞቻቸው እየተቿቸውም ቢሆን ኢትዮጵያ አደጋ ውስጥ ወድቃ ጥቅማቸው እንዳይነካ ስርዓቱን መክረው መሄድ አለባቸው፡፡ ለአሜሪካ ሲባል ኢትዮጵያን ከውድቀት መታደግ አለባቸው፡፡ ስርዓቱ ከሰማ! ተቃዋሚዎችም ይህን አጋጣሚ ከተጠቀሙበት! ተቃዋሚዎች ካልተጠቀሙበት ደግሞ ስርዓቱ ተመክሮ ሰማም አልሰማም የኦባማ መምጣት እውቅና ይሆንለታል፡፡ ጥቅሙም ጉዳቱም ማን በምን መልኩ ይጠቀምበታል በሚለው ይወስነዋል፡፡

የእለት ተእለት ጥያቄዎቻችን

በናትናኤል ፈለቀ
“ለምን እጅግ አላስፈላጊ ዋጋ ታስከፍናለህ? አንተ ከሌሎች ኢትዬጲያውያን በምን ትለያለህ? በግል የደረሰብህ በደል የለ! አንተ በመረጥከው መንገድ ልጆችህ አለአባት ሲያድጉ ሌላው በሞቀ ጎጆ ልጆቹን ምንም እንልተፈጠረ እያሳደረ እኮ ነው! እነደው ለእኔ እካን ብለህ ባይሆን ለልጆችህ ስትል የሚሉህን ሁሉ እሺ ብለህ ከዚህ ብትወጣ ምን አለ? ልጆችንን አርፈን ብናሳድግስ “ የምትል ሚስት ስለሌለን ነው ?
“በእኔ እስር ምክንያት ባለቤቴ ልጆቼን ለማሳደግ ስራዋን አቁማ በሽታ ላይ ወደቀች፡፡ ልጆቼንም እነዳልንከባበብ ሆንኩ ፣ አግኝቻቸው ለማላውቃቸው ሰዎች ነጻነት ስል ከምንም አብልጨ የምወዳቸው ልጆቼ ጉሮሮ ላይ መቆም ምን ያህል ትክክለኛ ምርጫ ነው ?” የሚል ጭንቅላት የሚጠብጥ አጣብቂኝ ስለሌለብን ነው ?
“በዚህ እድሜዋ እናቴን መጦር ሲገባኝ ልጄ ታሰረ ብላ ጭንቀት ውስጥ እንድትገባ እና የአእምሮ እረፍት አንድታጣ ምክንያት ሆንካት ፣ አንድ ልጅ ወልደህ አይኔን በአይኔ አሳየኝ ልመናዋን እንካን ሳላሳካላት “ የሚል ቁጭት ስለሌለን ነው ?
“ልጅ ሆኜ እናቴ በማስፈልጋት ሰአት እናቴ ተገቢው ህክምና እንካን ማግኘት አንድትችል ሳላግዝ አጣሃት፡፡ አሁን ደሞ ሽማግሌ አባቴ እንክብካቤ በሚፈልግበት ጊዜ ጭራሽ እስር ቤት ገብቼ እሱን አመላልሳለሁ ፣ እድሜዬን ሙሉ ሊያስተምረኝ ጥሪቱን ማፍሰሱ ሳያንስ አሁንም እዳው ሆኛለሁ ፣ የልጅነት ሃላፌነቴን የምወጣበት ጊዜ አገኝ ይሆን?” የሚል አስጨናቂ ፍርሃት ውስጣችንን ስለማይበላው ነው ?
“የወጣትነትን እድሜሽን አታስበዬ፣ አይምሰልሽ ፣ እድሜሽ እየገፋ ሲሄድ ይቆጭሻል፡፡ ልክ አንደእኩዬችሽ ትዳር ይዘሽ ልጅ ወልደሽ የተረጋጋ ኑሮ አትኖሪም? ጊዜሽን አትቀልጂበት! የሚል መካሪ አጥተን ነው ?
“ትዳር ይዘን የተረጋጋ ቤተሰብ የምንመሰርትበት እቅድ ላይ ለምን እንቅፋት የሚሆን ስራ ተሰራለህ ? አላሳዝንህም? ምናልባት እኮ ከእስር ስትፈታ መውለድ የማልችልበት እድሜ ላይ ልሆን እችላለሁ? ደሞ ህይወቴ አንተ ታስረህ እየሄች እኮ ነው” የሚል እጮኛ ስለሌለችን ነው ?
“መንግስትን ማስገደድ የሚችል ጉልበት ያለን ስለመሰለን ነው ? ከእስር ወጥተን ራሳችንን የምናሳድርበት ሞያ ስለሌለን ነው ? ጀግና መባል ስለምንፈልግ ነው? እውቅና ዝና ፍለጋ ወይስ ልበ ደንዳናነት ነው? ምንድነው እስር ቤት ያስቀመጠን ?
ለሁሉም ጥያቄዎች መልሱ አይደለም ነው ፣ እነደማንኛውም ሰው ሁሉ ልንጦረው የምንፈልገው እናት ወይም አባት ፣ በእንክብካቤ ልናሳድጋቸው የምንፈልጋቸው ልጆች ፣ መስዋአትነት የከፈበት የፍቅር ግንኙነት ወይስ ትዳር አለን፡፡ ህይወታችንን ሁሉ እነሱን ለማስደሰት ስንደክም የማይሰለችን እና የማይበዛባቸው ሰዎች በእያንንዳችን ህይወት ውስጥ አሉ ፡፡ዝና ጀግና መባል ሁሉ ያለእነሱ ትርጉም ያጣበትና እስር ቤት ሆነን የምንወዳቸው እና የመኖራችን ትርጉም የሆኑትን ሰዎች ደስታቸውና ምኞታቸውን ነጥቀናቸዋል፡፡ የሚመኙትን እና የምንመኝላቸውን ህይወት እንዳይኖሩ እንቅፋት ሆነናል፡፡ የሚወዱትን ሰው ደስታ እንዳያገኝ እንቅፋት ከመሆን ህመም ጋር የታሰርነው በመታሰራችን የምናጣው ነገር ሳይኖር ቀርቶ አይደለም፡፡
ከላይ የተጠቀሱት በሙሉ የኢትዮጵያ የፓለቲካ እስረኞች የምር ድምጾች ናቸው ፡፡ ( ለዚህ ጽሁፍ ሲባልም የተፈበረከ ወይም የተጨመረ ነገር የለም) እነዚህ ጩኀቶች መልስ የሚያገኙት መቼ ይሆን; ይሄ ጥያቄ አንድ የወዳጄ የጦማሪ በፍቃዱ ጽሁፍን ያስታውሰኛል ፣ 80 ሚሊዬን እስክንደርስ እንታገላለን፡፡ “

Source: Zone9

“እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር 5 “

“ቃላቸው” 
ተከሳሾች ሠጡት የተባለውን ቃል ስንመለከተው ደሞ ከመጻፍም አልፎ ከላይ የተባሉትን ይዘት ያላቸውን ጽሁፎች ማንበባቸውም ጭምር ተከሳሾችን ያሳሰራቸው ይመስላል፡፡ በብዙ ድብደባ እና አንግልት የተገኙት እነዚህ የተከሳሽ ቃላት ከላይ የሚገኙትን ከሰነዶች ላይ በመገልበጥ የእኔ ነው ብለው አንዲፈርሙ የተገደዱበት ነው ወንጀል ያልሆኑ ጉዳዬችን ዘርዝሮ ተከሳሹን ራሱን ጥፋተኛ ነኝ ማስባል ተከሳሾችን ራሳቸውን አንዲወነጅሉ ማድረግ ሲሆን ያም ሆኖ ተከሳሾች ጥፋተኛ ነን አንዲሉ የተገደዱባቸው እና ለፍርድ ቤት የቀረቡትን የማስረጃነት ሰነዶች ለአብነት አንይ ፡፡
- “የዞን ዘጠኝ የስም ስያሜ ስህተት ነው ፡፡ ምክንያቱም ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውጪ የሚገኝ ማለውን የኢትዬጲያ ህዘብ እስረኛ ነው በማለት ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ታራሚዎች ጋር ማነጻጸሬ ጥፋቴ ነው”
- “የተቃዋሚ ፓርቲዎችን አላማ በማስተዋወቅ ህዝቡ በምርጫ 2007 ኢህአዴግን አንዳይመርጥ መቀስቀሳችን ጥፋት ነው
- ህገ መንግስቱ ይከበር የሚል ከህዳር 27-29 2005 ድረስ በተደረገው ዘመቻ ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ህገ መንግስቱ ይከበር በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ”
- “የትራንስፓርት ችግር በአዲስ አበባ የሚለው ጽሁፍ ዞን9 ጦማር ላይ እንዲጻፍ በማድረጌ ጥፋተኛ ነኝ”
- “የጸረ ሽብር አዋጅ የኢትዬጲያ መንግስት ሆነ ብሎ ሰዎችን ለማጥቃት ፈልጎ ያወጣው ህግ መሆኑን ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመጡት የፓርላማ አባላት መረጃ በመስጠቴ ጥፋተኛ ነኝ፡፡”
- “የኬንያ ነጻነት እስከ ምርጫ ድረስ የሚል ጽሁፍ በዞን9 ጦማር ላይ በመጻፌ ጥፋተኛ ነኝ፡፡”
- ““Freedom of expression” የሚል ፌልም አዘጋጅቼ ለስራዬ የተከፈለኝን ክፍያ በባንክ በኩል ባለመላኩ ምክንያት መንግሰት ሊያገኝ የሚገባውን የአገልግሎት ክፍያ ባለመከፈሉ ጥፋተኛ ነኝ”
- “እስክንድር ነጋ ፣ ርእዮት አለሙ መ ውብሸት ታዬ አንዷለም አራጌ እና በቀለ ገርባ የተባሉ እስረኞችን ለማስፈታት ሰላማዊ ሰልፎች ላይ እና ድረ ገፅ ተሳትፎ በማድረጌ ጥፋተኛ ነኝ”
እነዚህን ጥፋቶች ነው ተከሳሾች በሶስት ወር የማእከላዊ ምርመራ ከብዙ ማሰቃየት በኋላ አንዲፈርሙ የተደረጉት፡፡ ይህንን መርምሮ ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ይዟል፡፡
“ስልካቸው”
ሌላው ተከሳሾች ላይ በማስረጃነት የቀረበው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት በሽብር ህጉ አንቀጽ 652/2001 አም አንቀጽ 14 መሰረት ‘በተለያዬ ድረገፆች የኢትዬጲያን ገጽታ ለሚያበላሹ ሃሳቦችን በመሰንዘር እና በኢትዬጲያ ውስጥ የሽብር ተግባር የመፈጸም አንቅስቃሴ ላይ ናቸው ያላቸው ተከሳሾች ላይ የላከው ማስረጃ ነው፡፡ በአጭሩ ተጠናቀረ የተባለው ማስረጃ የተከሳሾቹን ሽብርተኛነት ድርጊት ያሳያል ተብሎ የቀረበ ሲሆን ሰነዱ ከግል ቤተሰባዊ ስልክ ልውውጦች እስከ የጓደኝነት ቀልዶች ድረስ ይዟል፡፡ በትንሹ ብንጠቅስ
“በ10/09/2005 አም የቃሊቲ ትዊተር ቻት ( Kality twitter chat ) አምስት ሰአት አንደሚጀመር እና አራት ኪሎ ካፌ ውስጥ እንዳለ የቡድኑ ጸሃፊ በፍቃዱ ሃይሉ ለዘላለም ክብረት ገልጾለት ዘላለምም ወደአራት ኪሎ ለመሄድ ተስማምቷል”
“በ01/05.2006 ሰሞኑን የማህበራዊ ድህረ ገጾች ላይረ ሲወጡ የነበሩ ጽሁፎች በጣም አከራካሪ ስለሆኑ በዚህ ዙሪያ ፎርቹን ጋዜጣ ላይ የሚወጣ ጽሁፍ እያዘጋጀ ስለሆነቃለ መጠይቅ ሊያደርገው ስለፈለገ ይመቸው አንደሆነ ተስፋለም ወልደየስ የቡድኑ አባል ለነፍቃዱ ሃይሉ የቡድኑ ጸሃፊ ገልጾለት በፍቃዱ ሃይሉም ቀደም ብለው በ6 ሰአት መገናኘት አንደሚችሉ ገልጾለታል”
እነዚህና መሰል የተከሳሾቹን የስልክ ንግግሮች ያለ ፍርድ ቤት ፍቃድ ከተጠለፈው ስልካቸው ጋር እነደማስረጃ በመሆን ተከሳሾቹ ላይ ቀርቧል ይህንንም ፍርድ ቤቱ መርምሮ ብይን ይሰጣል ማለት ነው ፡፡
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ በሌሎች ሰዎች የተጻፉ እና ኮምፒውተር ላይ የተቀመጡ ጽሁፎች ተከሳሾች በልጅነታቸው የጻፉት የትምህርት ቤት ግጥሞች አለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ የጻፏቸው ፕሮፓዛሎች ሰነዶችም ማስረጃ ተብለው ለፍርድ ቤቱ ቀርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ይህንን መርምሮ ለሰኞ ብይን ይሰጣል፡፡
Source: Zone9

Friday, July 17, 2015

“እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር 4"

ምሁራን በሰነድ ማስረጃው
እስቲ ከዚህ ቀጥሎ ያሉትን ግለሰቦች ስሞች ይመልከቱ
“Amartya Sen ,Richard Nixon , Edward Hermon , Noam Chomsky, Navi Pillay , Franz Kafka, Carl Bernstein, Bob Woodward , Eleanor Roosevelt, Kenneth Roth, Hina Jilani, Michael D. Watkins, John wade , Jay Heinrichs, Bernard Mayer , Terie S Skjerdal” ከላይ የተጠቀሱት ምሁራን የሃገር መሪዎች የህግ ባለሞያዎች ጋዜጠኞች የስነጽሁፍ ሰዎች አንድ የሚያደርጋቸው ብቸኛ ነገር ቢኖር በክሱ ማስረጃዎች ላይ የሽብርተኛነት ድርጊትን ለማስረዳት አንድ ላይ መቅረባቸው ነው፡፡
“Where after all do universal human rights begin? In small place close to home” ብለው ወይዘሮ ኢላኖር ሩዝቬልት መናገራቸው በክሱ ማስረጃነት የቀረበ ጉዳይ ነው ፡፡ “Thank you for arguing what Aristotle, Eminem and Homer Simpson can teach us about the art of persuasion” በማለት ጄ ሄንሪች የጻፉት መጽሃፍ በማስረጃው ዝርዝር ውስጥ ያገኛል፡፡ ይህ ቀልድ አይደለም “There had never been a famine in any country that has been a democracy with a relatively free press” በማለት ፕሮፌሰር አማርተያ ሲን የጻፉትን የጻፉት ሃሳብ ተተርጉሞ ለክሱ የማስረጃነት ተያይዟል፡።
“Believing means liberating the indestructible element in one self or more accurately being indestructible or more accurately being “ በማለት ቼካዊው የስነጽሁፍ ሰው ፍራንስ ካፍካ የጻፈው ጽሁፍ እንደሃሳብ ማበልጸጊያ የተጻፈ ጽሁፍም በማስረጃነት ይገኛል፡፡
“All human beings are born free and equal in dignity and rights. They are endowed with reason and conscience and should act towards one another in a spirit of brotherhood." ብሎ አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ድንጋጌ Universal Declaration of Human Rights (UDHR) በአንቀጽ አንድ ላይ የደነገገው ድንጋጌ ወንጀል ለመፈጸም በመዘጋጀት እና ማቀድን ለማስረዳት ከሰነድ ማስረጃዎቹ ተቀላቅሎ ይገኛል፡፡ እነዚህ ከላይ ለአብነት የጠቀስናቸው የማስረጃ ክፍሎች እንዲሁ በአጋጣሚ የተቀላቀሉ አይደሉም ፡፡ ይልቅም ፓሊስ የተከሳሾች ቤት እና ቢሮ እና መገልገያዎች መርምሮ ለክሱ አስፈላጊ ናቸው የሽብር ድርጊትን ያስረዱልኛል ብሎ በአማርኛ ቋንቋ ቃል በቃል አስተርጉሞ ለፍርድ ቤት ያቀረባቸው ናቸው፡፡ መቼም ከ Homer Simpson እስከ UDHR በስህተት የተካተቱ ሊመስለን ይችላል፡፡ ነገር ግን በፍርድ ቤቱ የስራ ቋንቋ ተተርጉመው መቅረባቸውን ስናይ ከሳሾች ላይ የቀረቡት ማስረጃዎች ከታላላቅ ምሁራን እስከ ካርቱን ፊልም ባህሪያት ድረስ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ፍርድ ቤቱ ይህንን መርምሮ ለመወሰን ቀጠሮ ይዟል፡፡

Source: Zone9

Thursday, July 16, 2015

“እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር 3 “

"በግንቦት ሰባት አማካኝነት የተሰጠው የሽብር ስልጠና ማስረጃዎች "
የሽብርተኛነት ስልጠናውን ለተከሳሾች ሰጥተዋል ተብለው በማስረጃነት የተጠቀሱትን ድርጅቶች ማየትም የማስረጃዎቹ አስደንጋጭ ይዘት ነው፡፡ በፍርድ ሂደቱ ወቅት ከሳሽ ስልጠና የሰጡ ተቋማትን እና ስልጠናው አይነት በዝርዝር እንዲያቀርብ ሲጠየቅ አድበስብሶ ያለፋቸው የስልጣና ይዘቶችና አሰልጣኞችም በሰነድ ማስረጃው ተካተዋል፡፡ የሽብር ሰልጠና ሰጡ የተባሉት ድርጅቶች ዝርዝር
Civil rights defenders ( CRD) , The floke bernadotte academy , the Swedish institute , Swedish international development cooperation agency ( SIDA), the open society foundation , tactical thec , Kenya Media council ( KMC) , Article 19 , freedom house , National endowment for democracy , IREX , united nations higher commission for human rights, amnesty international , committee to protect journalist (CPJ) , eastern and southern Africa Journalists association ( ESAJA) , Rhoedeb Journalism university and African institute for governance with integrity ይገኙበታል ፡፡
የክሱ የሰነድ ማስረጃ ውስጥ ከትምህርት ተቋማት እስከ ማህበራት እና አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ( የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ) ቀርበው ሲታይ የሰነድ ማስረጃውን አስገራሚ ያደርጉታል፡፡ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅትን የመሰሉ ተቋማት ጋር ግንኙነት በመፍጠር ሽብር የተከሰሱት ተከሳሾችን የሽብር ስራ ለማጣራት እና ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ እነዚህንም ሰነዶች ይመረምራል፡፡
Source: Zone9

Diplomats and policy advisers are warning the rouge Ethiopian regime


Here in Washington DC, today just before an hour, there was an interesting panel discussion regarding President Obama's visit to Ethiopia and Kenya and its implication ( also its aftermath).
Various questions were raised, and the diplomats / policy advisers have addressed every question. Lily ( screen name for Soliyana i hope), Mena from the congressional black caucus, and the known Ethiopian activist Obang Metho have raised stunning and thoughtful issues.
Impressively, the Americans know each atrocities and injustice being committed by the authoritarian regime of Ethiopia.
Please watch an excerpt from the discussion


“EPRDF Friendly Authoritarian Regime” US Officials: Terrence Lyons Discussed


"እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር 2''

“በጻፉት ጽሁፍ አልከሰስናቸውም “
ተከሳሾች በታሰሩበት ወቅት የኢትዮጲያ መንግሰትየመናገር ነጻነትን ለመገደብ የወሰደው እርምጃ አንደሆነ በተለያዬ አካላት ትችት ሲቀርብበት የተለመደ መልሱን “ በጻፉት ጽሁፍ አልከሰስናቸው”በማለት በተደጋጋሚ መልስ ሲሰጥ አንደነበር ይታወሳል፡፡ ይህ መንግስት ገለጻ ግን ቆየው ተከሳሾች ላይ መደበኛ ክስ እስኪመሰረትድረስ ብቻ ነበር ፡፡ ከግማሽ በላይ የሆኑት አንደማስረጃ የቀረቡት የተከሳሾች የግል ጦማርና በዞን9 ጦማር ላይ እና ፌስቡክ ላይየተጻፉ ጽሁፎች ናቸው ፡፡
በተከሳሾች የሽብር ክስ ላይ በማስረጃነት ከቀረቡትጽሁፎች መካከል ጥቂቹን ለአብነት ያህል ብንጠቅስ
ልማታዊ ጋዜጠኝነት ወይስ ይሁንታን ማምረት እንዴት እደመጥ  የመለስ ውርስና ራዕይ ፣ ነጻነትና ዳቦ ሰብዓዊ መብቶች በሕገ-መንግስትና መንግስት  ግልፅ ደብዳቤ ለጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ  ሕግ ምርኩዝ ወይስ ዱላ   መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ መፅሄቶች  አራማጅነት በኢትዮጵያ ፣  የእነርሱ እና የእኛ ሕዳሴ ፣  ልማት ሲሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ልማ አለ ማለታቸው ነውን የ1966 ዓ.ም አብዮት እና የሲቪል ማኅበራት ሚና  የሥርዓትና ሐይማኖት ለውጥ  ኬንያ ከነፃነት እስከ ምርጫ እና በሀገሩ ጉዳይ የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ ……”
ከላይ ለአብነት የጠቀስናቸው ሃያ ጽሁፎች በዞን9ጦማር ላይ ወጥተው መንግስት "በጻፉት ጽሁፍ አልከሰስናቸውም" በማለት ላቀረበው ክስ በዋነኛ ማስረጃነት ያቀረባቸው ጽሁፎች ናቸው፡፡እንግዲህ እነዚህና መሰል ጽሁፎች ናቸው የህብረተሰቡን ደህንነትና ጤና አደጋ ላይ ጥለዋል ተብለው የሽብርተኝነት ድርጊትን ለማስረዳትየቀረቡት፡፡ ጽሁፎቹን ያነበበ ማንኛውም ሰው አንኳን ማህበረሰቡን ደህንነት አደጋ ላይ ሊጥሉ ቀርቶ የአንድን ግለሰብ መብት አንኳንየሚጥሱ እንዳልሆነ ማንም ያነበበ ሰው ሊረዳቸው ይችላል፡፡
“የሚያስደነግጡ ማስረጃዎች”
ከላይ ያሉ ጽሁፎችን አንብቦ ለተገረመ ሰው በቀሪዎቹማስረጃዎች የበለጠ ሊደነግጥ ይችላል፡፡
1.     “Ethiopiathousands protest political repression – June 02/2013 Associated Press (AP) byKirubel Tadesse
2.    የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ፓርቲውንጸረ ህገ መንግሰታዊ እንቅስቃሴ ያጋለጠ ነው- ኢህአዴግ ግንቦት 26.2005 ( ፋና ብሮድ ካስቲን ኮርፓሬሽን ኤፍ ቢሲ) ጥላሁንጎሳ
3.    Thousands marchfor rights in rare Ethiopia protest June 02/2013 – Reutors Aron Masho
4.    Ethiopiathousands stepped anti government protest June 02/ 2013 Posted by Daniel Brhane ( by Marthe vanaderwolf)
5.    ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰልፍግንቦት 25 /2005 አም በአዲስ አበባ ተካሄደ ( ERTA reporter Kebede Kassa)
6.    Thousands ofEthiopian Opposition activily demonstrate in Addis Ababa June 02/2013 VOA byPeter Hailen
7.    Beware of wishfulthinking one swallow does not make a swimmer – June 03/ 2013 Tigray onlineDilwenberu Nega
8.    ሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሰልፍአካሄደ ጁን 02/2013 ሶደሬ ዜና
እነዚህከላይ የጠቀስናቸው የዜና ርእሶች ጽሁፎች በሙሉ ተከሳሾች ላይ የተገኙ ማስረጃዎች ናቸው በመባል እንግሊዘኛዎቹ በ56 ገጽ ተተርጉመውተከሳሾች ላይ ማስረጃ ሆነው ቀርበዋል፡፡  የመንግሰት የመገናኛ ብዙሃን ( ኢቢሲ፣ ፋና …)ሳይቀር ያወጧቸውን ዜናዎች ሳይቀር የሽብር ህግ ያስረዳሉተብሎ የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱ እነዚህን ሰነዶች ይመረምራል፡፡

Source: Zone9

1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት እና የነጻ ማኅበራት ፋይዳ


በ2004 የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ‹‹መጅሊስ ይቀየር›› ጥያቄ መቀስቀሱን ተከትሎ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ዩንቨርስቲዎች በአንዱ ውስጥ በጉዳዩ ዙሪያ ለመወያየት ስብሰባ ተጠራ፡፡ ስብሰባው ላይ የዩንቨርስቲው የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዚደንት የነበረው የእስልምና እምነት ተከታይ እጁን አውጥቶ ‹‹ትላንትና ምንም ነገር እንዳልናገር ከዩንቨርስቲው አስተዳደር ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኝ ነበር፥ ሆኖም…›› ብሎ ሐሳቡን ተናገረ፤ ያ የዩንቨርስቲ የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዚደንት በማግስቱ ከኃላፊነቱ ተነሳ፡፡

ይህ በኢሕአዴግ ዘመን ያለውን ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ መብት ደረጃ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ምሳሌ ሲሆን በዚሁ ተንደርድረን፣ በ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት ጉልህ ሚና የተጫወቱትን ተመሳሳይ አካላት እንመለከታለን፤ ለመሆኑ እነዚህ ሕዝባዊ አካላት እነማን ነበሩ?

የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት የኋላ ኋላ ገጠሬው ቢቀላቀለውም፣ በአብዛኛው የተመራው በከተማ ነዋሪዎች ነው ማለት ይቻላል፡፡ አንዳርጋቸው ጥሩነህ Ethiopian Revolution 1974-1987፡ A transformation from an aristocratic to a totalitarian autocracy (1993) በተሰኘው ጥናታቸው ላይ በአብዮቱ ዋና ተዋናይ የነበሩትን አካላት ከነ[ተቀራራቢ] ቁጥራቸው ዘርዝረዋቸዋል፡፡

“የኢትዮጵያ ንግድ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን 80,000 አባላት፤ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር (አባላቱ የመንግሥት ሠራተኞች ነበሩ፤) ብዛታቸውም 18,000 ነበር፡፡ ከመንግሥት ሠራተኞቹ በተጨማሪ 10,000 የምድር ጦር እና 30,000 የፖሊስ አባላትን ጨምሮ 55,000 የሠራዊት አባላትን የሠራተኛ ማኅበሩ ያካትታል፡፡

በወቅቱ የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር 70,000 ነበር፤ ከነርሱ ውስጥ 6,000ዎቹ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ናቸው፤ (በተጨማሪም በውጭ ሃገራት የዩንቨርስቲ ጥናት ላይ የነበሩ ሌሎች 2,000 ተማሪዎች ነበሩ)፡፡

“ስለዚህ ከጠቅላላው 3 ሚሊዮን የከተማና ከተማ ቀመስ ቦታዎች ነዋሪ ሕዝብ ውስጥ ፖለቲካዊ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የነበሩት የመንግሥት ሠራተኞች፣ ወታደሮች እና ተማሪዎች ከ300,000 የማይበልጡ የከተማ ነዋሪዎች ነበሩ፡፡”

በየማኅበራቱ የታቀፉት እና ፖለቲካዊ ንቁ የነበሩት ሕዝቦች ቁጥር ከጠቅላላው የከተማ ሕዝብ አንጻር እንኳን ሲታይ ከ10 በመቶ የማይበልጡ እና በወቅቱ ከነበረው ጠቅላላ የሕዝብ ብዛት አንጻር ከ1 በመቶ የማይበልጡ ቢሆንም አብዮቱን ማስነሳት ችለዋል፡፡ አብዮቱ ከተማ እና ኮርፖሬታዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ ሳይወሰን አገር አቀፍ እንዲሆን በማድረግና ስር ሰድዶ የነበረውን ንጉሣዊውን ስርዓት በማንገጫገጭ ለማስወገድም ችሏል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው በተለያዩ ማኅበራት ጥንካሬ ነው እንጂ በተሳታፊዎቹ ቁጥር ብዛት አይደለም ብዬ አምናለሁ፡፡ በዝርዝር እንመልከተው፡-

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ)

ኢሠማኮ የተለያዩ መሥሪያ ቤት ሠራተኞች ለጥቅማቸው ለመቆም ያቋቋሟቸው ማኅበራት አቃፊ ኮንፌዴሬሽን ነበር፡፡

ኢሠማኮ በ1965፣ 167 የሠራተኞች ማኅበራትን ያቀፈ ሲሆን ከ80,000 በላይ አባላት ነበሩት፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ በ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት ወቅት ውስጥ የነበረው ሚና ከየትኛውም አካል የጎላ ነበር፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ በመጀመሪያ የሠራተኞቹን ጥቅም ያስጠብቃሉ ያላቸውን (የደሞዝ ጭማሪ፣ የሠራተኞች የመደራጀት መብቶች) እና ሌሎችም (5 ያክል) ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ይዘት ያላቸውን - ብዙ ምንጮች እንደሚሉት 16 (አንዳርጋቸው ጥሩነህ 17 ነው ይላሉ) ጥያቄዎች አነሳ፡፡ መንግሥት ይህንን ጥያቄያቸውን ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ ጠቅላላ አድማ ለጥር 30/1965 እንደሚጠራም አስጠነቀቀ፡፡ የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው መኮንን ከአድማው ቀነ ቀጠሮ አንድ ቀን ቀድመው ጥያቄዎቹ ከሦስት እስከ ስድስት ወር በሚደርስ ጊዜ መልስ እንደሚያገኙ ብቻ ተናገሩ፡፡ በማግስቱ (የካቲት 1/1965 /ማርች 8/) ግን እስከ መቶ ሺሕ የሚጠጉ ሰዎች የሥራ ገበታቸው ላይ ባለመገኘት የሥራ ማቆም አድማ አደረጉ፡፡ የታሪክ ጸሐፊዎች በዕለቱ ፀጥ-ረጭ የማለቱን ገጠመኝ የሚያስታውሱት በተለይ አዲስ አበባ ‹‹ሽባ ሆነች /በእንብርክኳ ሄደች/›› በማለት ነው፡፡
በወቅቱ ኮንፌዴሬሽኑ የገጠመው ችግር አብዛኛዎቹ ሠራተኞች በአድማው ከሦስት ቀን በላይ መሳተፍ አለመቻላቸው ነው፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት አብዛኛዎቹ ሠራተኞች ኑሯቸው ከእጅ ወደአፍ ስለሆነና ሥራችንን አጥተነው እንቀራለን የሚል ፍራቻ ስለነበረባቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ለጥያቄዎቻቸው በሙሉ መልስ የሚሰጥ ስምምነት የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው እንዲፈርሙ ማስገደድ አላቃታቸውም፡፡ እንዲያም ሆኖ የአድማው ትልቅ ግብ ተደርጎ እስከዛሬም የሚቆጠረው እንቅስቃሴው ሌሎች በርካታ አድማዎችን እና መንግሥትን ለለውጥ የሚያስገድዱ እበያዎችን ማበረታቱ ነው፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር (ኢመማ)

ኢመማ ከ60 ዓመት በላይ ያስቆጠረ አንጋፋ ማኅበር ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደንጉሡ ዘመን ማብቂያ ሰሞን አቅመ-ትልቅ ማኅበር ሆኖ  አያውቅም፡፡ በ1965፣ 18,000 ያህል አባላት ነበሩት፡፡ ማኅበሩ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ቢያንስ ለስድስት ዓመታት ያክል በደሞዝ ጭማሪ እና የደሞዝ ስኬል ጉዳይ ሲነታረክ ከርሟል፡፡ አንዳርጋቸው ጥሩነህ እንደጻፉት የመምህራን ማኅበሩ የካቲት 11/1966 ታክሲዎች የነዳጅ ጭማሪን ተከትሎ በጠሩት አድማ ላይ ተደምሮ የትምህርቱን ሥርዓት በዝምታ ሊያውለው ወሰነ፡፡ ማኅበሩ ጥያቄዎቹን ከመምህራን (የደሞዝ እና የሴክተሩ ክለሳም) በላይ እንዲሆን፤ የሰላማዊ ሰልፍ መብት እንዲከበር፣ የደሞዝ ወለል እንዲበጅ፣ ለፋብሪካ ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ እንዲደረግ፣ ለኢንዱስትሪ ሠራተኞች የጡረታ መብት እንዲከበር፣ ሠራተኞን የማባረሪያው ሕግ እንዲስተካከል እና ሌሎችንም ጥያቄዎችን አነገበ፡፡

የመምህራን ማኅበሩ የደሞዝ ስኬት ይሻሻል ጥያቄውን ከአብዮቱ 6 ዓመት ቀድሞ ያነሳ ቢሆንም መልስ ማግኘት ባለመቻሉ ትግሉን አጠናክሮ፣ የመምህራንን ብቻ ሳይሆን የሌሎችም ሠራተኞች መብቶችን የሚያስከብሩ እና ሌሎችም ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን አንግቦ ተጠናክሮ በመንቀሳቀስ የሌሎቹን ማኅበራት ዓይን ለመግለጥ መቻሉ እንደስኬት ይቆጠርለታል፡፡

የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ማኅበር (USUAA)

የኢትዮጵያ ዩንቨርስቲዎች ማኅበር (ከቀኃሥ - ዩንቨርስቲ በተጨማሪ የሌሎች ሁለት ራስ ገዝ አካባቢዎች ዩንቨርስቲዎችን የሚጨምር ሲሆን) የነበረው አቅም ግን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ማኅበር ያነሰ ነበር፡፡ ሆኖም የተማሪዎች ሚና ጉልህ ነው በሚል እስከዛሬም ‹‹የተማሪዎች እንቅስቃሴ›› ውጤት ሆኖ የሚታወሰው የ1966ቱ አብዮት በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ማኅበር (ESUNA) እና የኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ማኅበር በአውሮፓ (ESUE) የታገዘ ነበር፡፡

የዩንቨርስቲ ተማሪዎች እንቅስቃሴ እስካሁንም ድረስ በተቃዋሚ እና ገዢው ወገን ያሉትን አንጋፋ ፖለቲከኞች ያነሳሳ እና ለአብዮቱ ምልከታዎችን ለግሶታል፡፡ አንጋፋዎቹ የ‹‹መሬት ላራሹ›› እና የብሔሮች እኩልነት ጥያቄ ቦታ የተሰጣቸው ያኔ - በተማሪዎቹ አማካይነት ነው፡፡ USUAA (በ1966 መባቻ ላይ የታገደባቸውን) ‘ስትራግል’ የተሰኘ ጋዜጣ በማሳተም የብሔሮች መብት እስከመገንጠል ድረስ የመዝለቅ ጥያቁዎችን ሳይቀር አንስቷል፡፡ መኢሶን፣ ኢሕአፓንና ሕወሓትን የመሰሉ ለተከታዮቹ ረዘም ላሉ ዓመታት ተጽዕኖ ፈጣሪ ፓርቲዎችም የተፈጠሩትም ከተማሪዎች እንቅስቃሴ ነው፡፡

በተማሪዎቹ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጉልህ ሚና ኖሮት ነገር ግን ብዙም ያልተወራለት ‹‹Crocodiles Society›› (የአዞዎቹ ማኅበረሰብ) የሚባለው ነው፡፡ ይህ ቡድን የዩንቨርስቲውን እንቅስቃሴ ያጋግሉ የነበሩትን ‹‹ዜና እና አስተያየቶች›› የታተሙበትን በራሪ ወረቀቶች የማዘጋጀት/የማሰራጨት ሚና የነበረው ሲሆን ‹‹መሬት ላራሹ›› የሚለው አጀንዳም የፈለቀው ከዚያ እንደሆነ የባሕሩ ዘውዴ Documenting the Ethiopian Student Movement: An Exercise in Oral History ይጠቃቅሳል፡፡

የተማሪዎች ኅብረት ለአብዮቱ መፋፋም የሐሳብ መዋጮ፣ እና የፓርቲ መመስረት የመጨረሻው ውጤት ቢሆንም የትምህርት ክፍለጊዜዎችን ክፍል ባለመግባት እና የተቃውሞ ሰልፍ በማስነሳትም ጭምር የወቅቱ ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ ተግተው ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የተማሪዎቹ እንቅስቃሴም ፈተና ነበረበት፡፡ የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዚደንት ጥላሁን ግዛው ባልታወቁ ሰዎች (በዝግታ በምትነዳ መኪና ውስጥ በተተኮሰ ጥይት) ተገድሏል፡፡ ጆን ያንግ Peasants Revolution of Ethiopia በተባለ መጽሐፋቸው ጥላሁን ‹‹ከገንጣዮች እንቅስቃሴ ጋር ትተባበራለህ›› በሚል ዩንቨርስቲውን ለቅቆ እንዲወጣ ማስጠንቀቂያ እንደደረሰው ገልጾ ነበር ሲሉ ጽፈዋል፡፡

ከነዚህ በተጨማሪም የ5 ሣንቲም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን ተከትሎ የተጠራው የታክሲ ማቆም አድማም ለአብዮቱ መጧጧፍ እና ለንጉሡ ስርዐት የኢኮኖሚ ፈተና ለመሆን በቅቷል፡፡

ትላንት ይማረኝ?

ደርግ ሁሉንም ማኅበራት በራሱ መልክ ለማዋቀር ሞክሮ ነበር፡፡ የነጋዴዎች፣ የከተሜዎች፣ የገበሬዎች… እየተባለ ማኅበር በማኅበር አገሪቱን አጥለቀለቃት፡፡ አንዳርጋቸው ከላይ በጠቀስነው ጥናታዊ ጽሑፋቸው “ከሞላጎደል ሁሉም ዜጋ አንዱ፣ ወይም ሌላኛው ወይም ከአንድ በላይ የሆነ ማኅበር/ራት ውስጥ መታቀፉ የማይቀር ነበር፡፡ ዕድሜዋ ከ18 እስከ 30 የሚደርሳት ሴት ለምሳሌ የገበሬች ወይም የከተሜዎች ማኅበር (እንደምትኖርበት ቦታ ሁኔታ) እና የወጣት አብዮተኞች ማኅበር አባል ትሆናለች፡፡ እንዲሁም፣ የነጋዴዎች፣ የነርሶች፣ የዶክተሮች ብሎም የፓርቲ አባልም ልትሆን ትችላለች፤” በማለት የደርግን ዘመን ማኅበር የረከሰበት ቢሆንም ሁሉም የመንግሥታዊ ስርዐቱን ከማስፈፀም በላይ ፋይዳ እንዳልነበራቸው አመላክተዋል፡፡

በኢሕአዴግ ዘመነ መንግሥት ደግሞ የተለየ አጨዋወት እናገኛለን፡፡ ኢሕአዴግ በጥቅሉ በመደራጀት (communalism) ያምናል፤ ሆኖም እያንዳንዱን ማኅበር የመቆጣጠር ኃላፊነቱን ግን ካድሬዎቹ እንዲወስዱት ይፈልጋል - እስካሁን ባለው ሁኔታ ተሳክቶለታልም፡፡

የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ማኅበር በ1993 የገጠመው የነጻነት ማጣት ችግር እና የዩንቨርስቲው ቀውስ እስከዛሬ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ በወቅቱ የዩንቨርስቲ ተማሪዎቹ 4 ጥያቄዎችን በማንሳት ያመጹ ቢሆንም ከወቅቷ ሚኒስቴር ያገኙት የመጨረሻው መልስ ‹‹ካልፈለጋችሁ ግቢውን ጥላችሁ ውጡ›› የሚል ነው፡፡ ተማሪዎቹ በእምቢተኝነት አድማቸውን በመቀጠላቸው ደግሞ በአድማ በታኞች ብዙዎች ሲጎዱ ለሞት የተዳረጉም እንዳሉ በወቅቱ የኢትዮጵያ ሰብኣዊ መብቶች ጉባኤ ዝርዝር መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ የዩንቨርስቲው ማኅበር በኢሕአዴግ ዘመን ‹ሕሊና› የተሰኘ ጋዜጣ ሦስት ጊዜ ያህል ብቻ ያሳተመ እና ያሰራጨ ቢሆንም ከዚያ በኋላ ታግዷል፡፡ አሁን ሁሉም ሊባል በሚችል ሁኔታ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ማኅበራት ፕሬዚደንቶች በውስጠ ታዋቂነት ካድሬዎች ናቸው፡፡

የመምህራን ማኅበሩን የነጻነቱ ዘመኑ በ1999 ከማብቃቱ በፊት ፕሬዚደንቱ የነበሩት ታዬ ወልደሰማያት ታስረው ሲፈቱ ከአገር ተሰደዋል፡፡ የግጭቱ መንስኤ ነው የሚባለው መንግሥት የሚያምነውን ማኅበር አዲሱ ኢመማ በማለት ለመፍጠር መሞከሩ ነው፡፡ ጉዳዩ ፍርድቤት የደረሰ ቢሆንም መንግሥት ግን ዕውቅናውን ለአዲሱ ሰጥቶ የቀድሞውን አፈራርሶታል፡፡ የመምህራን ማኅበሩ የውድቀት ምልክት ነው ብዬ እዚህ ልፈርድበት የሚያስደፍረኝ በ2004 የመምህራን ደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ለዲፕሎማ ምሩቅ 31 ብር፣ ለዲግሪ ምሩቅ ደግሞ 73 ብር እንዲሆን ሲወሰን ማኅበሩ - ውሳኔውን ማድነቁን በማጣቀስ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት ማኅበራት የቆሙለትን አካል ጥቅም በማስጠበቅ ፈንታ የመንግሥትን ፊት እያዩ ማዳነቅ ወይም ማራከስ ሲይዙ ፋይዳቸው ዋጋ ያጣል፡፡

በሌላ በኩል በሕግ ባይከለከልም ሌላ የመምኅራን ማኅበር ለማቋቋም እንደቀድሞው ምቹ የፖለቲካ ሁኔታ እንደሌላ የሚናገሩም አሉ፡፡ The Status of Governance, Academic Freedom, and Teaching Personnel in Ethiopian Higher Education Institutions በሚል በFSS ርዕስ በተደረገ ጥናት ላይ ነጻ የመምህራን ማኅበር ለማቋቋም ማሰብ በጅማ ዩንቨርስቲ መምህራን ‹‹unattainable luxury›› ተብሎ ሲገለጽ የባሕር ዳር ዩንቨርስቲ ተወያዮች ደግሞ ‹‹You never think of forming teachers’ association since the political environment is complex and ambiguous›› በማለት የመምህራን ማኅበር ማቋቋምን እንደተአምር ገልፀውታል፡፡ ይህንኑ በሚያጠናክር መልኩ ያለፈውን ከመፍረሱ በፊት እና አዲሱ እየተቋቋመ ሳለ የነበራቸውን አቋም ሲተቹ፣ አሰፋ ፍስሐ የተባሉ ጸሐፊ Ethiopia's Experiment in Accommodating Diversity: 20 Years’ Balance Sheet ባሉት መጣጥፋቸው ላይ ‹‹ሁለት የመምህራን ማኅበራት አሉ፤ አንዱ ገዢውን ፓርቲ ሌላኛው ተቃዋሚዎችን ይደግፋሉ›› በማለት ከፖለቲካ አጀንዳ የፀዱ (ነጻ) እንዳልሆኑ መስክረዋል፡፡

አዲስ አበባ የወጣቶች ማኅበር አላት፤ የወጣቶቹ ማኅበር ከኢሕአዴግ ደጋፊዎች ወጣቶች ሊግ የሚለይበት አንዳችም ባሕሪ የለውም፤ የቀድሞ የወጣቶች ማኅበሩ ፕሬዚደንት የነበሩት አቶ ታጠቅ አሁን ሁነኛ ሹመት በመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የአሁኖቹም ‹‹ወጣትነታቸው›› ሲያልፍበት ይሾማሉ፡፡ ማኅበራቱ የመንግሥትን ሥርዐት መደገፋቸው እንደጥፋት ላይቆጠር ይችላል፤ ሆኖም በመንግሥታዊ ሥርዐቱ ውስጥ የሚወክሏቸውን የኅብረተሰብ አካላት ጥቅም በሕጉ ውስጥ በአግባቡ ካላስጠበቁ ቅቡልነት ያሳጣቸዋል፡፡ አሁን እየሆነ ያለውም ይኸው ነው፡፡

የሴቶች ማኅበርም አለ፣ ከኢሕአዴግ ደጋፊ የሴቶች ሊግ የሚለይበት የለም፤ በጥቅሉ ሁሉም ማኅበር (የንግዶቹን ጥቃቅን እና አነስተኛ ማኅበራት ጨምሮ) በኢሕአዴግ እና በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ክበብ ውስጥ የተቀነበቡ እና አሻግረው ማየት እንዳይችሉ ተደርገው የተሠሩ ናቸው፡፡ በተጨማሪም ሌሎቹንም በገለልተኛ ወገኖች የሚመሠረቱ ማኅበራት ካድሬዎች በግራም በቀኝም ብለው የፕሬዚደንትነቱን ስፍራ ይቆናጠጡ እና የመንግሥትን ሕልም ማስፈፀሚያ ያደርጉታል፡፡ በካድሬዎች የማይመሩትም የባለሙያዎች ማኅበራት ሳይቀሩ ኢሕአዴግን ላለማስቀየም ወይም ለማኅበሩ ሕልውና ሲሉ እውነትን ለመናገር ከመቆጠብ ጀምሮ የሠሩትን ጥናት ውጤት ለሕዝብ ይፋ ሳያደርጉ የመደርደሪያ ማሞቂያ አድርጎ እስከማቆየት ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ በጥቅሉ አሁንም ማኅበራት አሉ፤ ማኅበራቱ ግን እንኳን የሥርዐት መሻሻልና ለውጥ ሊጠይቁ ቀርቶ ቢሳሳትም ባይሳሳት መንግሥትን ከመደገፍ የተለየ ተግባር የላቸውም - የኔ መደምደሚያ ነው፡፡
------
ማስታወሻ፡-
ይህ ጽሑፍ ‹‹ስለለውጥ›› በሚል የሚቀርቡት ተከታታይ ጽሑፎች አካል ነው፤
-----
ተጓዳኝ ጽሑፎች፤
    -----
    የዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጂ በኢትዮጵያ እንዳይነበብ በታገደው የዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ይገኛል፡፡

    ፍርድ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ

    የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር በአካል ተገናኝታችኋል›› የሚል ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሾቹ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችኋል ከተባለ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ታስረው የሚገኙ በመሆናቸው መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ይታዘዝልን›› የሚል ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
    የፌደራል አቃቤ ህግ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ አይችሉም ብሎ ተቃውሟል፡፡ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህዝባዊ መብት በመሻሩ ለፍርድ ስራ ልዩ አዋቂ ወይንም ነባሪ ሆነው መስራት አይችሉም ያለው የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በተጨማሪ ምስክርነት ቀርበው መመስከር አይገባቸውም ሲል የተከሳሾቹ ጥያቄ ውድቅ እንዲሆን ለፍርድ ቤቱ አመልክቶ ነበር፡፡
    ሆኖም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር ለምስክርነት በመሆኑ፣ ምስክርነትም ግዴታ እንጅ መብት በመሆኑ ሰኞ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ለተከሰሱት ተከሳሾች ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲመሰክሩ ወስኗል፡፡ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው የት እንደሚገኙና ማዘዢያው የት ተብሎ ሊፃፍላቸው እንደሚገባ ተጠይቀው ለቃሊቲ ማረሚያ ወይንም ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ሊጻፍላቸው እንደሚገባ፣ ካልቀረቡላቸውም ክሳቸው ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር የተገናኘ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡
    ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው በጠየቁበት ወቅት በዳኞችና በአቃቤ ህጎች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ መፈጠሩንና ከአቶ አንዳርጋቸው ይልቅ ሌሎች መከላከያ ምስክሮችን ማቅረብ እንደሚችሉ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት ለማቅረብ መሞከር እንደሌለባቸው እንደገለፁላቸው ታውቋል፡፡ ዳኛው በድንጋጤ ‹‹እኛ እዚህ ጉዳይ ላይ የለንበትም›› ማለታቸውን ተከሳሾቹ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ ላነጋገራቸው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ገልጸውለታል፡፡
    በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር 

    “እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር 1 “



    ባለፉት 14 ወራት መንግሰት በቂ ማስረጃ አለኝ እያለ ተከሳሾች ደሞ “እንኳን የሽብርተኛነት ድርጊት ወንጀልን አንዳች ደምብ መተላለፍ እንኳን የሚያስረዳ ወንጀል የለም” እያሉ ሂደቱ ቀጥሏል ፡፡ ብይኑ በመጪው ሰኞ ሃምሌ 13 ዓ/ም ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል፡፡ ከመጪው ብይን አስቀድሞ ቀረቡትን የማስረጃዎች ምንነት ማየትም ጉዳዩን ግልጽ ያደርገዋል፡፡ 
    ብርጋዴር ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “ የማስረጃ መሰረተ ሃሳቦች በሚለው መጽሃፋቸው የማስረጃን ምንነት ሲገልጹ “ ማስረጃ ማለት የአንድን አከራካሪ ነገር መኖር ወይም አለመኖር የዳኛው አእምሮ አንዲያምን የሚያደርግ ነገር ነው በአጭሩ ዳኛው ከፊቱ የቀረበለትን ጥያቄ እውነት ወይም ሃሰት መሆኑን ለመረዳትና ከውሳኔ ላይ ለመድረስ ግምት ለመውሰድ አእምሮው የሚመራበትን ነገር የያዘ ነው፡፡ ይህም ነበሰው ምስክርነት እና በልዬ አዋቂ ምስክርነት የሚሰጥ ማስረጃ፣ በሰነድ ማረጋገጫ የሚሰድ ማስረጃ እንዲሁም ተጨባጭ ወይም በኤግዚቢትንት የሚሰጥ ማስረጃን ከነአቀራረቡ ያለውን አሰራር የያዘ ነው” በማለት ነው ፡፡ የ5ስቱን ክሳቸው የቀጠለው ጦማርያን ጉዳይም ከዚህ ልዩ ትርጉም አንጻር መመልከት ጉዳዩን የበለጠ ለመረዳት ይጠቅማልና ጉዳዬን እንደሚከተለው እንመልከተው ፡፡ 
    ከሳሽ በተከሳሾች ላይ ያቀረባቸው ማስረጃዎች ሙሉ ለሙሉ የሰነድ ማስረጃዎችን ብቻ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህም ማለት በከሳሾች የቀረቡት ሁሉም የሰው ምስክሮች ( 22 ምስክሮች) የሰነድ ማስረጃው በፍተሻ ሲገኝ የተመለከቱ በመሆን የሰነድ ማስረጃውን እውነተኛነት ለማረጋገጥ የተገኙ ናቸው ፡፡ በፍተሻ ወቅት የተገኙ ላፕቶፕ ስልኮች ሲዲዎች ፍላሽና ሃርድ ዲስኮች በአጠቃላይ ከሳሽ ላቀረባቸው ሰነድ ማስረጃዎች ማረጋገጫ በመሆን የቀረቡ ናቸው፡፡ በተከሳሾች ላይ የተመሰረተው ክስ ያስረዳል በማለት የቀረቡት ሁሉም ማስረጃዎች የሰነድ ማስረጃዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው፡፡ በአስገራሚ ሁኔታ “ ማስረጃ” ይሆናሉ ተብለው ቀረቡት ሰነዶች ተከሳሾቹ መሆናቸው ተከሳሾቹ መሆናቸው ታምኖ እያለ ምስክር ሊኖር የሚገባው በአንድ ወገን የተካደን ጉዳይ ለማስረዳት ቢሆንም ለክርክሩ አስፈላጊነት የሌላቸው ታዛቢዎች ከሳሽ አቅርቦ ለወራት የፍትህ ሂደቱን ጊዜ በልቷል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የሚሰጠው ቀረበለትን “የሰነድ ማስረጃ “ ብቻ መሰረት አድርጎ ነው ማለት ነው ፡፡
    1. “Human rights underpin the aspiration to a world in which every man, woman, and child lives free from hunger and protected from oppression, violence, and discrimination, with the benefits of housing, health care, education, and opportunity.” 
    Navi Pillay, የቀድሞው United Nations High Commissioner for 
    Human Rights ከፃፉት የተወሰደ
    2. “ስሜ በፍቃዱ ሃይሉ ነው፡፡ አዲሱ አመት ሲጠባ በአዲስ መንፈስ አዲስ ህልም ለአገሬ ማለም እና የነበረኝንም ማጠናከር እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዬጵያችን የብሄር የሃይማኖት የሃብት የትምህርት የፓለቲካ አመለካከት እና ሌሎችም ልዬነቶቻችን አብሮነታችንን የማያደናቅፉባት ከነልዬነታችን በጋራ ለታላቅነት የምንጠቀምባት ፣ ለሁላችንም እኩል እድል እና ተጠቃሚነት የሚቀርብባት፣ ሁላችንም እንደችሎታችን ለጋራ ደህንነታችን ፣ ነጻነታችን እና ብልጽግናችን የምንሰራባት ብቻ ሳይሆን በጋራ ስኬታማ የምንሆንባት ፣ እንዲሁም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል የሚያፈቅራት ኢትዮጵያ አንድትሆን እመኛለሁ ይህ የእኔ ኢትዬጵያዊ ህልም ነው፡፡ “ 
    በፍቃዱ ሃይሉ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ቡድን ከነሃሴ 30/2005 - ጷጉሜ 02/2005 ድረስ ካደረገው ኢትዮጵያ ህልም በይነ መረብ ዘመቻ ላይ ከጻፈው የተወሰደ 
    3. Micro – Economics Theory 11
    Chapter 4 
    Factor market and income distribution 
    4.1 Perfectly competitive factor market 
    4.1.1 Demand for factors of production
    Demand for single variable factor 
    Assumptions 
    a. A farm produce a single good in a PCM 
    b. A farm objective is profit maximization
    c. Production and good requires one variable factor , the price of each constant 
    d. Technology is fixed 
    VMPc= PA * MPP
    VMPc= Value of marginal production 
    PCM= perfectly competitive market 
    MPP= Marginal Physical production 
    ከአጥናፍ ብርሃኔ ማክሮ ኢኮኖሚክስ ደብተር የተወሰደ
    4. “በአገራችን ሚዲያ መልክአምድር ላይ ሚገኙት እድሜ ጠገብና ሰፊ ጂኦግራፊያዊ ተደራሽነት ያላቸው የመገናኛ ብዙሃን ኢቴቪ፣የኢትዬጲያ ሬዲዬ እና አዲስ ዘመን ጨምሮ በየክልሉ የሚገኙትን መገናኛ ብዙሃን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው መንግስት ነው ፡፡ ይህም በአዋጅ የተረጋገጠ መብቱ ነው፡፡ ነገር ግን ግለሰብም ሆነ መንግሰት በባለቤትነት የሚያስተዳድረው የትኛውም መገናኛ ብዙሃን ደግሞ ኢኮኖሚያዊ ትርፉን ከማጋበሻነት በተጨማሪ የባለቤቱን የፓለቲካ አቋም ማራመጃ ለመሆን ምቹ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ መገናኛ ብዙሃንን ፓለቲካዊ ኢኮኖሚ ( political economy of the mass media ) በመተንተን እውቅ የሆኑት ናሆም ቾምስኪን እና ኤድዋርድ ሃርማን በ1988 “ይሁንታን ማምረት”( manufacturing consent , the political economy of the mass media ) በሚል ርእስ ካሳተሙት መጽሃፍ የፕሮፓጋንዳ ሞዴል የሚለው ጽንሰ ሃሳብ ሃገራችን የመገናኛ ብዙሃን መልከአምድርና ፓለቲካዊ ኢኮኖሚ በደምብ አድምቶ ስለሚገልጽልኝ ዋቢ አደርጌ ከዚህ አንደሚከተለው እጠቅሰዋለሁ፡፡ “
    እንዳልካቸው ሃይለሚካኤል በነሃሴ 2005 በዞን9 ጦማር ላይ ልማታዊ ጋዜጠኝነት ወይስ ይሁንታን ማምረት በሚል ከጻፈው ጽሁፍ የተወሰደ
    ከዚህ በላይ ከተራ ቁጥር 1 – 4 ላይ የተጠቀሱት ጉዳዬች የሚያነብ ሰው አንድ ሚያደርጋቸው ነገር ምንድነው ብሎ መጠየቁ አይቀርም ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የቀድሞው ከፍተኛ ኮሚሽነር ወይዘሮ ናቬይ ፒሌይ ከሙሁሩ ናሆም ቾምስኪ ጋር አንድ ላይ መጠቀሳቸው ግራ የሚያጋባ ሊመስል ይችላል፡፡ ጉዳዩ እነዲህ ነው ከተራ 1-4 ድረስ ተጠቀሱት ጽሁፎች ከሳሽ የፌደራል አቃቤ ህግ በቀን 08/11/2006 ጽፎ በሰባት የዞን9 ጦማሪዎች እና በሶስት ጋዜጠኞች ላይ ባቀረበው ክስ ( አሁን ክሱ በአምስት ጦማርያን ላይ ብቻ ሆኗል) በማስረጃነት ካቀረባቸው ሰነዶች የተወሰዱ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰነዶች ያስረዱታል የተባለው ወንጀል ድርጊት ደግሞ
    “ ……የፓለቲካ የሃይማኖታዊ ወይም የአይዲዬሎጂ አላማን ለማራመድ በማሰብ በመንግሰት ላይ ተጽእኖ ለማሳደር ህብረተሰቡን ወይም የህብረተሰቡን ክፍል ለማስፈራራት ወይም አገሪቱን መሰረታዊ ፓለቲካዊ ህገ መንግስታዊ ኢኮኖሚያዊ ወይም ማህበራዊ ተቋማትን ለማናጋት ወይም ለማፍረስ ( በማሰብ) ህብረተሰቡን ወይም የህብረተሰቡን ከፍል ደህንነት ወይም ጤና ለከፍተኛ አደጋ ለማጋለጥ ( ማቀድ መዘጋጀት ማሴር ማነሳሳትና መሞከር) …….” ነው ፡፡
    ይህ ብዙ ሰዎች ቀልድ ሊመስል ይችላል ፣ ነገር ግን በእውነት የሽብርተኛነትን ወንጀል ለማስረዳት በ5 የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ቀረቡ ማስረጃዎች ናቸው( ክሱ ከመቋረጡ አስቀድሞ የተከሳሾች ቁጥር 10 አንደነበር ይታወሳል)፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች በዞን 9 የተሰሩ አራቱም የበይነ መረብ ዘመቻዎች የማስረጃው አካል ሆነው ቀርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ እነዚህ ሰነዶች ለሽብር ክስ መዘጋጀት ማሴር እና ማቀድ መሆን አለመሆናቸውን ይመረምራል፡፡

    Source: Zone9

    Wednesday, July 15, 2015

    ሰቆቃ በማዕከላዊ



    ‹‹እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡››
    አበበ ካሴ
    እኔ አበበ ካሴ እባላለሁ፡፡ የሰሜን ጎንደር ተወላጅ ነኝ፡፡ በማዕከላዊ እስር ቤት ከ5 ወር በላይ ታስሬለሁ፡፡ ከዚህ መካከል 4 ወር ከ25 ቀናት በጨለማ ቤት ተቆልፎብኝ ቆይቻለሁ፡፡ ማዕከላዊ በነበርኩበት ወቅት የሁሉም እግርና እጆቼ ጥፍሮች ተነቅለዋል፡፡ አንዳንድ ቀን እጄ ላይ የሆነ ነገር ስለሚወጉኝ ጥፍሮቼ ሲነቀሉ አላውቅም፡፡ ስነቃ ነው መነቀላቸውን የማውቀው፡፡ ከዛም ቁስሉን እየነካኩ ያሰቃዩኛል፡፡ ማደንዛዣ ለምን እንደሚወጉኝ አላውቅም፡፡ ጥፍሮቼን ሲነቅሉኝ ብቻ ሳይሆን ሌላ ጊዜም ራሴን እንድስት ያደርጉኛል፡፡ እጅና እግሬን አስረው እንደ ፍሪጅ ያለ እቃ ውስጥ ያለ በረዶ ውስጥ ያስቆሙኛል፡፡ ለብዙ ሰዓት በጣም ቀዝቃዛ የሆነ ቦታ ላይ እስክደነዝዝ ቆሜ እውላለሁ፡፡ እስኪበቃቸው ከደበደቡ በኋላ እጅና እግሬን አስረው ከምርመራ ክፍሉ በታች በሚገኝ ምድር ቤት ክፍል ውስጥ ያለ ጉድጓድ ላይ ጥለውኝ ይሄዳሉ፡፡ ጉድጓዱ ጉንዳንን ጨምሮ ተባዮች ያሉት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እግሬንና እጄን አስረው ዘቅዝቀውኝ ይሄዳሉ፡፡ የመጣው ሁሉ ዝዋዥዌ እንደሚጫወት ህፃን ወዲያና ወዲህ ያደርገኛል፡፡ ገልብጠው አስረው ሲዘቀዝቁኝ በአብዛኛው ራሴን እስታለሁ፡፡ እግርና እጄን ከወንበር ጋር ያስሩኛል፡፡
    ከወንዶች በተጨማሪ ሴቶችም ይመረምሩኛል፡፡ ሴቶቹ የሚመረምሩኝ ራቁቴን አርገው ነው፡፡ እነሱም ራቁታቸውን ሆነው ነው የሚመረምሩኝ፡፡ አሁን ለመናገር የማልደፈርው አፀያፊ ነገርም ፈፅመውብኛል፡፡ ይህን አፀያፊ ነገር የሚፈፅሙት አደንዛዥ እፅ እየተጠቀሙ ነው፡፡ ይህን ሲያደርጉ በአይኔ አይቻቸዋለሁ፡፡ መርማሪዎቹ ሰውነቴን በኤሌክትሪክ አቃጥለውኛል፡፡ ኤሌክትሪኩን የሚሰኩት ደረቴና የውስጥ እግሬ ላይ ነው፡፡ በዚህም የውስጥ እግሬ ተገልብጦ ሌላ ሰውነት አምጥቶ ነበር፡፡ እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡ ይህን ያህል አሰቃይተው ከጥቅም ውጭ ስሆን ቂሊንጦ አምጥተው ጣሉኝ፡፡ 11 ወር ያህል አልጋ ላይ ነበርኩ፡፡ በኤሌክትሪክ ግርፊያው ምክንያት ግራ ሰውነቴ ሽብ ሆኖ ነበር፡፡ ግራ እግሬ መንቀሳቀስ አይችልም ነበር፡፡ በምርኩዝ ነበር የምሄደው፡፡ አሁን እያነከስኩ ነው የምሄደው፡፡
    በተለይ ማዕከላዊ ውስጥ ይህን ያህል የሚሰቃዩኝ አንደኛ የሚያግዛችሁ አገር ማን ነው በሚል ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አማራ ክልል ውስጥ እንድትንቀሳቀሱ የሚተባበሯችሁን የብአዴን ባለስልጣናት ስም ተናገር እያሉ ነው፡፡ በሶስተኛ ደረጃ የሚያሰቃዩኝ የት የት ቦታ ነው የሰለጠንከው እያሉ ነው፡፡
    እዚህ ቂሊንጦ ከመጣሁ በኋላም ያሰቃዩኛል፡፡ ወጣቶች እንዳይቀርቡኝ ያስፈራሩዋቸዋል፡፡ ማንም ጠርቶ እንዳይጠይቀኝ እየተደረገ ነው፡፡ ጨለማ ክፍል ወስደውም አስረውኝ ያውቃሉ፡፡ እነሱ ደብድበው ከጥቅም ውጭ ካደረጉኝ በኋላ የምደገፍበትን ምርኩዝም ቀምተውኛል፡፡ ‹‹ይህኮ የጦር መሳሪያ አይደለም፡፡ እንጨት ነው፡፡ ለምን ትቀሙኛላችሁ? ደግሞም እናንተ ናችሁ እንዲህ ያደረጋችሁኝ፡፡›› ብያቸው ነበር፡፡ የሚሰሙ ሰዎች አይደሉም፡፡ የታሰርኩበት ክፍል ውስጥ እንድተኛበት የተሰጠኝ ቦታ ሽንት ቤቱ አጠገብ ነው፡፡ ሽንት እየሸተተኝ ነው የምተኝው፡፡ ‹‹ወደ ሌላ ቦታ ቀይሩኝ!›› ስላቸው ‹‹ደግሞ ለአንተ ይህ አንሶህ ነው?›› ይሉኛል፡፡ ያ ሁሉ ድብደባ ደርሶብኝ አልጋ ላይ በነበርኩበት ወቅት ወጣቶቹ ህክምና እንዳገኝ ወደ ሀኪም ቤቱ ወሰዱኝ፡፡ እነሱ ግን ‹‹ለአንተ ህክምና ሳይሆን ጥይት ነበር የሚገባህ›› ብለው መለሱኝ፡፡ እንዲህ እያሉ ለምን እንደማይገድሉኝ ይገርመኛል፡፡
    በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ልጆችዋ ለእልቂት፣ ለስደት፣ ለግድያ እየተዳረጉ ነው፡፡ በአካልም ሆነ በስነ ልቦና ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ዓለም ለሰው ልጅ ምቹ በሆነችት ከዓለም ውጭ ሆነናል፡፡ የመገናር፣ የመሰብሰብ፣ የመደራጀት በአጠቃላይ ሰው የሚያደርጉንን መብቶች ተነጥቀናል፡፡ ከሰው የማንቆጠርበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ገዥዎቻችን ህዝብን እየገደሉና ከሰው በታች አድርገው እየገዙም ቢሆን ግን ዓለምን እያታለሉ ነው፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ሁሉ የሚደረገው የአንድን ቡድን የበላይነት ለማስፈን መሆኑ ነው፡፡ እንዲጠፋ ሆን ተብሎ ጥቃት የሚደርስበት ህዝብም እንዳለ እያየን ነው፡፡ ግን ኢትዮጵያ የ95 ሚሊዮን ህዝን ሀገር ናት፡፡
    አሁን ያለው ስርዓት የአንድ ቡድን ስርዓት ነው፡፡ ለእሱ መኖር ደግሞ ሌሎቹን ገድሎ፣ አሰቃይቶ፣ አሳድዶ መኖር ይፈልጋል፡፡ ለስሙ የብሄር ብሄረሰብ መብት እናከብራለን ቢባልም እውነቱ ግን ኢትዮጵያውያን የመናገር፣ የመፃፍ፣ የመደራጀትና ሌሎች መብቶችን ተነፍጎ ከሰውነት ወጥተው ይገኛሉ፡፡ በዓለም ደረጃ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ቋንቋና ዘርን አይለይም፡፡ ይህ የሚደረገው በህወሓት ስርዓት ብቻ ነው፡፡ እኔ በርካታ ሰቆቃ የደረሰብኝ ሰው ስለሆንኩ ስርዓቱ የሚፈፅመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ለመመስከር እችላለሁ፡፡ እኔን ሰቆቃ ያደረሱብኝ ሰዎች ማንነታቸው መታወቅ ስላለባቸው እንደሚከተለው ስማቸውን እዘረዝራለሁ
    1. አቶ አሸነፍ ተስፋሁን ላቀው
    2. አቶ አብርሃም አይሸሽም
    3. ሙሉጌታ ወርቁ
    4. አቶ ደረሱ አያናው
    5. የአማራ ክልል ደህንነት ኃላፊ የሆነው አቶ ተሾመ
    6. የሰ/ጎ/መ/የታክቲክ ኃላፊ አቶ ሙላ እንየው
    7. የማዕከላዊ ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር ተክላይ
    8. የማዕከላዊ ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር ጌትነት
    9. አቶ አሰፋ አትንኩት (ምርመራበ ኃላፊ)
    10. መቶ አለቃ ተስፋዬ (መርማሪ)
    11. ሳጅን ፍሬ ህይወት (መርማሪ)
    12. ሳጅን ፅጌ (መርማሪ)
    ከላይ የጠቀስኳቸውን በስምና በአካል የማውቃቸው ሲሆኑ ከእነዚህ በተጨማሪ ከደህንነት መስሪያ ቤቱ እየመጡ የሚያሰቃዩን ስማቸውን የማላስታውሳቸውና በመልክም የማውቃቸው የህወሓት ደህንነቶች አሉ፡፡
    እዚህ እኛን እንደዚህ ሲያሰቃዩ ሀገሪቱን ገንዘብ መዝብረው የታሰሩ ሰዎች ምንም አይሆኑም፡፡ ተመችቷቸው ነው የሚኖሩት፡፡ ቂሊንጦ ውስጥ ሰው እንዳይቀርበኝም ቢፈልጉም ሰው ግን በጣም ይወደኛል፡፡ አሁን ጥፍሮቼ በቅለዋል፣ መራመድ ችያለሁ፡፡ አንድ ሽህ አመት አይኖርም፡፡ በጣም ብዙ ወገኖቻችን ሞተዋል፡፡ እኔ አለሁ፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ባለስልጣናት እኔ ላይ የደረሰውን ጨምሮ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ በፈፀሙት ወንጀል መጠየቃቸው የማይቀር ነው፡፡
    ይህ ሁሉ በደል ደረሰብኝ ስል ዝም ብዬ አይደለም፡፡ ማንኛውም ሰው መጥቶ የተሸማቀቀውን እግሬን፣ ቅጥ ባጣ ድብደባ የተጎዳው ሰውነቴን ማየት ይቻላል፡፡ ጥፍሮቼንም ለመስክርነት ይዤያቸዋለሁ፡፡ እነሱ ነቅለው ጥለው ሲሄዱ እኔ ስነቃ ሰብስቤ አስቀምጣቸዋለሁ፡፡ የተወሰኑትን ለመረጃነት አስቀምጫቸዋለሁ፡፡ ይህን ስል ግን እኔ ላይ የደረሰው ስቃይም የማይጠበቅ ሆኖ አይደለም፡፡ እነዚህ ሰዎች እንኳንስ ግለሰብ ሀገርም ገንጥለዋል፡፡ ከ40 አመት በፊት የነበረው የኢትዮጵያ ካርታ ተሸርፏል፡፡ እንኳን ሰው ሀገርም ለማጥፋት እየሰሩ ነው፡፡ ታሪካቸው፣ አመጣጣቸውም የሚያሳየው ይህን ነው፡፡ ይህን ሁሉ የምለውም መታወቅ ስላለበት ነው፡፡