Wednesday, July 10, 2013

ነካ ነካ ፖለቲካ(የጠፋው ትውልድ)
የጠፋው ትውልድ በዘመነ ደርግ ፖለቲካ የሚጠቀስ ተሳትፎ አልነበረውም።ተሰብሰብሲባል ይሰበሰባል፤ንቃሲባል ይነቃል፤ዝመትሲባል ይዘምታል አለዚያም ታፍሶ ይዘምታል፤ጫካ ግባሲባል ይገባል አለዚያም ተገዶ ይወርዳል ኢሕአዴግ ሥልጣን ሲይዝ የዚህ ትውልድ ፖለቲካዊ ፍላጎት እና እምቅ አቅም ምን ሊሆን እንደሚችል የገመተ አይመስለኝም።የብሔር ፖለቲካ”  ጨዋታው ለሁሉም የፖለቲካ ጥያቄዎች መልስ እንደሚሆን ሳያምኑም አልቀሩም። እነርሱዴሞክራሲሲሉና እኛ (የእኔ ትውልድ) ዴሞክራሲ ስንል ፈጽሞ ስለተለያዩ ነገሮች እናስብ እንደነበር የገባን ግን እየቆየ ሆነ፤ ለሁለታችንም። ለዚህም ነው ኢሕአዴግ እና ሌሎቹም ብሔር ተኮር ድርጅቶች በብሔረሰብ ፖለቲካ ሙሉ በሙሉ የሚያምኑ የትውልዱን አባላት እንኳን ማርካት ያልቻሉት። ምክንያቱም እነርሱየብሔረሰብ መብትሲሉ የምራቸውን ለዴሞክራሲ ይጠቅማል ብለው ነው፤ ኢሕአዴግና መሰሎቹ ደግሞ ገና እዚያ ገጽ ላይ አልደረሱም። በኢሕአዴግ የብሔር ፖለቲካ በመሳተፍ የመጀመሪያ ቅሬታ የደረሰባቸውም እነዚሁ የትውልዴ አባለት ነበሩ።
በሌላ በኩል የተቃውሞ ፖለቲካውን ጎራ የተቀላቀሉም የመረረ እውነታ ገጣሟቸዋል። እነዚህ ወገኖች በአንድ በኩል የኢሕአዴግ ዴሞክራሲ እነርሱ ከሚሉት የተለየ መሆኑን ቢያውቁም የአፈናው አይነትና መጠን ግን ከሚያስቡት ፈጽሞ የተለየ ሆኖባቸዋል። አንዳንዶቹምደርግ ሌላ ምን አደረገ?” ሲሉ መደመም ጀምረዋል። በሌላ በኩል በየፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ድርጅታዊ ሕይወትም ቢሆን ሌላ የትግል ሜዳ ሆኖ ጠብቃቸዋል። ፖለቲካን እንዲሸሽ፣ ከቀረበም በጥንቸል ንቃት እንዲንቀሳቀስ በሚያሳምን ድባብ ውስጥ ያደገው ይህ ትውልድ የዘመነ ኢሕአዴግን ፖለቲካ ለመሸሽ ብዙ ጊዜም ማስጃም አያስፈልገውም ነበር። እንደለመደውም የፖለቲካ ጫማውን አውልቆ  በቅርብ ተመልካችነት ተሰለፈ። ትኩረቱንም ወደ ሌሎች ዘርፎች አደረገ፤ ትምህርት፣ ንግድ፣ ቤተሰብ፣ ሃይማኖት፣ ስደት በዚህ ወቅት በፖለቲካዊ አቋሙ በማመናቸው ብቻ ኢሕአዴግን የተቀላቀሉ የዚህ ትውልድ አባላት እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው።
የጠፋው ትውልድበወሳኝ የሕይወቱ ጊዜ ከፖለቲካው መጽሐፍ ከመጥፋት የተረፈው በመርጫ 97 ዋዜማ ሆነ። ቀደም ሲል እንዳልኩት የአንድ ትውልድ አባላት ሚና የጎላ እንጂ ብቸኛ ሊሆን የሚችልበት ማኅበረሰባዊ ንቅናቄ ሊኖር አይችልም። በዚሁ እይታ ምርጫ 97 ከሞላ ጎደል የዚህ ትውልድ አዲስአብዮትአድርጎ መውሰድ ስሕተት አይመስለኝም። ይህ ማለት ትውልድ ይሁን አዲሱ ትውልድለዚህ አዲስ የፖለቲካ ጅማሮ ወሳኝ ሚና የተጫወቱ አልነበሩም ማለት አይደለም። የምርጫ 97 ወሳኝ መልእክቶች እና ሥራዎች በመሠረቱ የቀረጹት የዚህየጠፋው ትውልድፖለቲካዊ ፍላጎቶች እና ምኞቶች ናቸው። አዲሱ ትውልድየመጀመሪያ አባላትም ቢሆኑ የዚሁ መንፈስ ተቋዳሾች ሆነዋል። ይህን መልእክት በሚገባ ማንጸባረቅ የቻሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና መሪዎቻቸው ጎልተው ወጥተዋል።
ምናልባት ይህ ታሪክ ሲነሳ ብዙ ጊዜ ቀድሞ የሚታወሰውቅንጅትነው። ሆኖም በብሔረሰብ ቢደራጁምጥያቄው በኢትዮጵያ ማዕቀፍ ውስጥ በመቀራረብ መፈታት ይችላልየሚሉት ከፍተኛ ድጋፍ ማግኘታቸው መረሳት የለበትም። ይህ ደግሞ በመሠረቱ ብዙዎችቅንጅት ለመደገፍ ያበቃቸው ምክንያት ሌላ ገጽታ እንጂ ፍጹም ተቃራኒ አይደለም። ቅንጅት ውስጥም ይሁን ከደጋፊዎቹ መካከልየብሔረሰብን ጥያቄየማይቀበሉ ወይም እውቅና የማይሰጡ ሰዎች ይኖራሉ፤ አብዛኛው የዚህ ትውልድ አባል ግን የኢትዮጵያን አንድነትና የብሔር ጥያቄን ፈጽሞ የማይታረቁ ጉዳዮች አድርጎ አይመለከትም። በዚህ መነሻነት የሚቀርቡት መፍትሄዎች ሊለያዩ ይችላሉ፤ ቁም ነገሩ ግን ብዙው ሰው አጀንዳዎቹን የተረዳበት መንገድ ነው። በመፍትሔ አማራጮች ላይ መለያየቱ የዴሞክራሲን  አስፈላጊነትና ተቀባይነት ማግኘት የሚያሳይ ይሆናል።ቅንጅት የብሔረሰቦችን ጥያቄ እውቅና የማይሰጥ አድርገው የሚያቀርቡት ኢህአዴግን የመሰሉ ጠባብ ድርጅቶች እና አንዳንድ የራሱ የቅንጅት ጭፍን አባላት ብቻ ይመስሉኛል። ከዚያ ውጭ በሕዝቡ ውስጥ የነበረውየቅንጅት መንፈስየዴሞክራሲ፣ የፍትሕ፣ የነጻነት፣ የመቻቻል እና የመተማመን እንጂ የመጠራጠር፣ የጥላቻና የመናናቅ አልነበረም። እንዲዚያ ባይሆን ኖሮ የራሱ የህወሓት/ኦህዴድ/ብአዴንአባላት ሳይቀሩ ቅንጅትድምጻቸውን ባለሰጡ ነበር።
ይህንን እውነታየጠፋው ትውልድከደረሰበት ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበረሰባዊ ደረጃ አንጻርም ማየት ወደ ተመሳሳይ መደምደሚያ ሊያደርሰን ይችላል። የትውልዱ አባላት በትምህርትና በእውቀት፣ በሥራ/ገቢ እና በማኅበራዊ ኑሮ ወሳኝ የሚባል ተሰሚነት ለመፍጠር ጊዜ አግኝተዋል። ይህ ተጽእኖ በወላጆቻቸውም ሆነ በልጆቻቸው/ታናናሾቻቸው ላይ መንጸባረቁ የማይቀር ነው። የትውልዱ ፖለቲካው ምልከታ በቀኝም ይሁን በግራ የተሰለፉትን የፖለቲካ ጎራዎች መሠረታዊ ፍላጎቶች ለማስተናገድ የሚሞክር በመሆኑ በቀላሉ ለማጣጣል የሚመች አልነበረም። አሁን አሁን ሳየው ግን በቅንጅት ውስጥ ሳይቀር ይህ መንፈስ ዘልቆ ያልገባቸውትልልቅትንንሽ ሰዎች ነበሩ። ቅንጅት መንፈስግን የዚህ ትውልድ አንድ ሁነኛ የፖለቲካ ፍላጎት ነጸብራቅ ሆኖ ሊቆይ እንደሚችል እገምታለሁ፤ ግምት ነው።
ከአንድናት ኢትዮጵያ ብሎግ


ኢትዮጵያ ክብር ለዘላለም ትኑር!

No comments: