Friday, June 28, 2013

ፕሬዝዳንቱ በከባድ የማታለል ወንጀል በቁጥጥር ስር ዋሉ

ፕሬዝዳንቱ በከባድ የማታለል ወንጀል በቁጥጥር ስር ዋሉ

-የፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጎርጊስ ደብዳቤ ተቀባይነት አጥቷልdownload (1)
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ሊቀትጉሀን አስታጥቄ አባተ ትላንት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታወቀ፡፡ ፕሬዝዳንቱ ዛሬ ከቀኑ8፡00ልደታ የሚገኘው ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ የወንጀል ችሎት ይቀርባሉ፡፡
ፕሬዝዳንት ሊቀትጉሀን አስታጥቄ አባተ ሶስት የወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ከክሱ ይዘት መካከል ቤት ለሌላቸው አርበኞች ከተሰጠው የኮንደሚኒየም ቤተች ውስጥ ቤት እያላቸው እንሌላቸው አድርገው በመውሰዳቸው 2ኛ እህታቸውን ጨምሮ አርበኛ ላልሆኑና ለማይመለከታቸው ግለሰቦች “አርበኛ ናቸው” ብለው በመስጠታቸው እንዲሁም ከማህበሩ ከፍተኛ መጠን ያለው የብር ጉድለት መታየቱ ይጠቀሳል፡፡
ፕሬዝዳንት ሊቀትጉሀን አስታጥቄ አባተ ላይ የተመሰረተው ክስ እንዲቋረጥ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጎርጊስ ለፍትህ ሚኒስቴር የጻፉት ደብዳቤ ተቀባይነት አጥቷል፡፡
ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ በተለያየ ጊዜ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት በሆኑት በሊቀትጉሀን አስታጥቄ አባተ ተፈፅመዋል ስለተባሉ የተለያዩ የአስተዳደር በደልና የሙስና አቤቱታዎች መዘገቧ አይዘነጋም፡፡
finote netsanet

No comments: