ሀገራዊ ጥሪ
“የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል”
የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በትጥቅ ትግል ለማስወገድ “የግንቦት7 ሕዝባዊ ኃይል” በሃገር ወዳድና ለህዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወጣቶች፣ ምሁራን እና በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተደራጀ ኃይል ነው።
በአሁኑ ወቅት አያሌ ኢትዮጵያዉያን ወያኔን ለመታገል መሳሪያ ካነሱ ከነጻነት ታጋዮች ጋር በየቀኑ እየተቀላቀሉ ናቸው፡፡ ትግሉን የበለጠ ለማጠናከር እና የአምባገነኑን ስርአት ውድቀት ለማፋጠን ወገኖቻችን ተማሪዎች፤ ገበሬዎች፤ነጋዴዎች፤ ላብ አደሮች፤ በመንግስት ሴክተሩ እና በሌሎች ተቋማት የምትገኙ ሁሉ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይልን እንደሁሌም የውስጥ አርበኛ በመሆን የነጻነት ትግሉን በመቀላቀል፣ ራሳችሁንና ሀገራችሁን ከወያኔ የዘረኛ አገዛዝ መዳፍ እጅ ነጻ ትወጣ ዘንድ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ የአባቶቻችንን አኩሪ ታሪክ ለመድገም ትግሉን በመቀላቀል ፍርሃታችሁን በጣጥሳችሁ በመደራጀት የዜግነት ግዴታችሁን እንድትወጡ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ጥሪውን ያቀርባል።
ተባብረን ወያኔን እናስወግድ!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
No comments:
Post a Comment