Saturday, August 31, 2013

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክርቤት አስቸኳይ ስብሰባ እያደረገ ነው

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክርቤት አስቸኳይ ስብሰባ እያደረገ ነው


የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ዛሬ ነሃሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም በፓርቲው ጽ/ቤት እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ አንድነት የጀመረውን የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ክንውኖች ገምግሟል፡፡ ምክርቤቱ ቀሪዎቹ የንቅናቄው መርሀ ግብሮች በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል የፓርቲው ስራ አስፈፃሚዎችና የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ከእስካሁኑ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ ሰጥቷል፡፡ 33ቱ ፓርቲዎች የአንድነት ፓርቲን ህዝባዊ ንቅናቄ በመቀላቀል የመስከረም 5ቱን ሰላማዊ ሰልፍ በጋራ ለማካሄድ መወሰናቸውንም ምክር ቤቱ በደስታ ተቀብሏል፡፡
ብሔራዊ ምክርቤቱ ከሰአት በኋላ በሚያደርገው ስብሰባ በመጪው መስከረም ወር መጨረሻ ለሚደረገው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ የሚቀርቡ ሰነዶች ላይ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍም ይጠበቃል፡፡   DSC02371DSC02372DSC02373
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=5537#sthash.9oNYRzch.dpuf

No comments: