Saturday, August 31, 2013

የሃገር ቤት ፖለቲካ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገኛል።


የሃገር ቤት ፖለቲካ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገኛል።

ድምጻችን ይሰማ ሙስሊሙ ህዝብ ሰልፉን እንዲወጣ እና በርግጥ ድምጹን 

እንዲያሰማ እየጠየቁ ሲሆን ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ በእለቱ የጠራውን የራሱን 

የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያካሄድ አሳውቋል። አንድነት ፓርቲም በቅርቡ በአዲስ 

አበባ ከሚያካሂደው ሰልፍ በፊት የክልል ተቃውሞዎችን አጠናክሮ ሲቀጥል 

ውጥረት ውስጥ ያለው ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሞባይል ስልክ አገልግሎት 

እያጠፋ ነገሩን ለማብረድ እየሞከረ ነው። በተጨማሪም የሃገር ውስጥ ደህንነት 

ምክትል ሃላፊ የነበረው ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና በሚል በቁጥጥር ስር 

መዋሉ እየተሰማ ነው።

No comments: