Saturday, August 31, 2013

የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር ወስደዋቸዋል።Semayawi Party headquarters under siege


Semayawi Party headquarters under siege



Semayawi Party headquarters in Addis Ababa has been surrounded by a heavily armed 

Federal Police squad. Over 100 party members and organizers including the party chairman 

Eng. Yilkal Getnet have been put under siege. The party’s head of legal affairs Yidenekachew 

Kebede is reportedly arrested while talking to ESAT.


In a warning broadcast last night on the state-controlled radio and TV, the regime had 

threatened that it would take actions against any protests and agitations.  Yidenakechew told 

ESAT that the siege was illegal as is Semayawi Party was only organizing a peaceful protest. 

“It is a shame and upsetting that the government taking such an illegal measure. He said the 

party was only preparing for a peaceful protest it called for tomorrow

ከምሽቱ 1:00 ላይ የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች አራት ኪሎ 

አካባቢ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ 

ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሊቀ-መንበሩን ጨምሮ 

ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር 

ወስደዋቸዋል።በውጭም በውስጥም የሚኖረው መላው 

የኢትዮጵያ ህዝብ ድርጊቱን እንዲያወግዝና ለአለም-አቀፍ 

ተቁማትም ሁኔታውን እንዲያሳውቅ ጥሪ ቀርቧል። ሞት ለወያኔ 

ትግሉ ይቀጥላል።

Semayawi Party office in Addis Ababa is surrounded 

by heavily armed police

Today, 12:45The headquarters of an Ethiopian 


opposition group, Semayawi Party, has been 

surrounded by heavily armed Federal Police troopers 

today following an announcement by the party to call 

another peaceful demonstration. 
                   
                  የሰማያዊ ፓርቲ መግለጫ፤

ትግላችን የህግ የበላይነትን ወደ ማስከበር ተሸጋግሯል!

ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት 


ያቀረብናቸው ጥያቄዎች መልስ ባለማግኘታቸው ለሕዝብ ቃል በገባነው መሠረት በድጋሚ ተቃውሞ ሰልፍ አቅዶ 

አስፈላጊውንእንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ ለዚህም ሥራ መሳካት ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ነሐሴ 13 ቀን

2005ዓ.ም. በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ባቀረብነው ደብዳቤ ላይ ያልተካተቱ ጉዳዮችን

እንድናካትት ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈልን ደብዳቤ ተጠይቀን አስፈላጊውን መልስ አሟልተን ነሐሴ 17 

ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈ ደብዳቤ አሳውቀናል፡፡

በአዋጁ በግልፅ እንደተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ህገ መንግሥታዊ መብት እንደሆነና ማንም ሊከለክለን 

እንደማይችል በማያሻማ መንገድ ተገልጿል፡፡ ሰልፉን የማሳወቁ ዓላማ የጥበቃ አገልግሎትና አንዳንድ አስተዳደራዊ 

ድጋፎችን ለማግኘት ነው፡፡ በዚህ አሰራር ውስጥ መንግሥት የጥበቃና የቦታ ችግር ካለ ሰልፉን ለሌላ ጊዜና ቦታ 

እንዲያደርግ ለሚመለከተው አካል ደብዳቤ በደረሰው በ24 ሰዓት ውስጥ በፅሑፍ መልስይሰጣል የሚል ድንጋጌ 

አለ፡፡ ነገር ግን በመንግሥትበኩል ላቀረብነው የመብት ጥያቄ ምላሽ መሰጠት ሲገባው እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ 

የመንግሥት መዋቅር ሙሉ በሙሉ በመጠቀምና ዜጐችን አስገድዶ ሰልፍ እንዲወጡ በማስፈረም ሰማያዊ ፓርቲ 

ሰልፍ በጠራበት ቀንና ቦታ ሌላ ሰልፍ በተደራቢ በሃይማኖት መቻቻል ስም ህገ መንግሥቱን በመጣስ የሃይማኖት 

ተቋማትን ለራሱ የድርጅት ፖለቲካ መጠቀሚያና የሰማያዊ ፓርቲን ህጋዊ እንቅስቃሴ ለመግታት እየተጠቀመበት 

ነው፡፡

ይህ አሰራር እንዲስተካከል መንግሥትን በመግለጫ ብንጠይቅም የተሰጠን ምላሽ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የሀገሪቱን 

ህገ መንግሥትና የሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን 

በኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዲኤታ እንዲሁም ሰልፍ ጠሩ በተባሉ አካላት ግልፅ የሆነና የተቀነባበረ ህገ ወጥ 

ሴራ ሆኗል፡፡ ስለሆነም በነገው ዕለት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.የምናደርገው ሰላማዊ ሰልፍ ከዚህ ቀደም 

ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረብ ከመሆን አልፎ የህግ የበላይነትን ወደ 

ማስከበር አድጓል፡፡ በመሆኑም በመንግሥት የሚደረገው ዓይን ባወጣ ሁኔታ ህግን የመጨፍለቅ ተግባር እንዲቆም 

ለምናደርገው ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ከጐናችን እንዲቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ምንጊዜም የተባበረ የሕዝብ ትግል ያሸንፋል!

ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም.

አዲስ አበባ

Semayawi Party headquarters under siege

Saturday, August 31, 2013 @ 03:08 PM ed
Semayawi Party headquarters in Addis Ababa has been surrounded by a heavily armed Federal Police squad. Over 100 party members and organizers including the party chairman Eng. Yilkal Getnet have been put under siege. The party’s head of legal affairs Yidenekachew Kebede is reportedly arrested while talking to ESAT.
In a warning broadcast last night on the state-controlled radio and TV, the regime had threatened that it would take actions against any protests and agitations.  Yidenakechew told ESAT that the siege was illegal as is Semayawi Party was only organizing a peaceful protest. “It is a shame and upsetting that the government taking such an illegal measure. He said the party was only preparing for a peaceful protest it called for tomorrow

No comments: