Wednesday, August 17, 2016

አፈትልከው የወጡ የሕወሓት ሚስጥሮችና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች

TPLF Ethiopian Leaders

መግቢያ
ኢትዮጵያ በባንዳ መንግስት መመራት የጀመረችው መቼ ነው?
በቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት እናት ሀገር ኢትዮጵያ ከ1927ዓ.ም እስከ 1932ዓ.ም ለአምስት አመት በወራሪው የፋሺስት ጣልያን መንግስት ባልተሳካ ሁኔታ የተመራችበት ወቅት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን መሪ ሳይኖረው ዘር፤ጎሳ፤ ብሄር፤ ቋንቋና ሀይማኖት ሳይለይ እጁ ላይ በሚገኘው መሳሪያ ሁሉ ድንጋይን ጨምሮ በመዋጋት የዘመናዊ ጦር መሳሪያ ባለቤት፤ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ፤ለሁለተኛው የአለም ጦርነት በአንደኛው ጎራ ከጀርመን ጋር መሪ የነበረችው ጣሊያንን በማንበረከክ የሚታወቅ የእግዚአብሄር ባላደራ ህዝብ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ባለፈችባቸው ዘመናት በጣም በጣም አያሌ ጠላቶች የነበሯት ሀገር ብትሆንም የእግዚአብሔር ሀይል የተሰጣቸው መሪዎቿ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሀገራቸውን ብቻ በማስቀደም እስከ 1983ዓ.ም አቆይተውናል፡፡አሁን ግን ሌላ መዓት ወረደባት፤ በሀገራችን ሌላ ታሪክ ተፈጠረ፤ኢትዮጵያን አምላኳ የረሳት መሰለች ፤ ኢትዮጵያ ሰው እንደሌላት ሆነች፤ሌቦች አደንዝዘው ዘረፏት፤ይህች ውብ ሀገር የብዙ አስደናቂ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት ፤ የአለም አቀፍ ምሁራን አንኳ ስለኢትየጵያ ቢጽፉ ቃላት ይቸግራቸዋል፤ ኢትዮጵያዊ መሆን እድለኝነት ነው፤ግን ይህ እድለኝነት ዛሬ አይዋጥልንም ወያኔ የረሀብ ሀገር አደረጋት፡፡
ኢትዮጵያ ጡቷን አጥብታ ያሳደገቻቸው ልጆቿ ባንዳ ሆኑባት፤ የልጅ ኪሳራ ማለት እንዲህ ነው፤ኢትዮጵያ በድጋሚ ለ25 አመት በባንዳ መሪ ተገዛች፤ህዝቦቿ በታሪክ አይተውት የማያውቁትን ውሸት፤የሞራል ውድቀት፤በሽታ ፤ረሃብ፤ግድያ፤ወኔ አልባ መሆን፤በጭንቀትና በብስጭት በሽተኛ የሚሆን ህዝብ፤ በበሽታው ምክንያት ካቃሰተ ወደ ከርቸሌ የሚወረወር ህዝብ ባለቤት ሆናለች፡፡
የባንዳው የሕወሓት ገዥ ዋና ዋና ጭብጦች
በመጀመሪያ ባንዳው ገዥ ሲጸነስ በደደቢት በረሃ የገበሬዎች አመጽ ሲሆን ምንም አይነት ፊደል ያልቆጠሩ ከሰፈርና ጎጠኝነት አስተሳሰብ ውጭ ሌላ የማሰብ እድሉ በሌላቸው ገበሬዎችና ቀጥሎም ተማርን በሚሉ የአሁኑ ወያኔዎች የተጀመረ ሲሆን፤ የሚኖሩበትን ቀበሌ ነዋሪ ብሎም በለስ ከቀናቸው ደግሞ አንድ አይነት ቋንቋ ተናጋሪ የሆነውን ህዝብ ብቻ ነጻ ለማውጣት የታሰበ አመጽ ነበር፡፡ በጊዜው በመንግስቱ ሀይለ ማሪያም አገዛዝ ወቅት በመላ ሀገሪቱ በነበረው አመጽ መሪ ተዋናይ የነበረው የአማራው ኢሃፓ በተማረ የሰው ሀይል የተደራጀና ሀገሩን ከነበረው አገዛዝ በተሻለ ህዝቡ ሰላማዊ በሆነ መንገድ አንዲኖር ለማድረግ ከወያኔ በአመታት ቀድሞ የተወለደው ኢሃፓ፤አንድ ሰላማዊ ኢትየጵያን በህዝቧ ፍላጎት ለመምራት ደፋ ቀና በሚልበት ወቅት ነበር ከወያኔ አባላት ጋር ለመወየያት የተወሰነው፤በዚሀም መሰረት ለህዝቡና ለሀገሩ ቆርጦ የተነሳው ኢሃፓ ምንም ሳይፈራ ሳይጠራጠር ከወያኔ ጋር ውይይት አደረጉ፤በሁለቱ አካላት መካካል ውይይቱ ተደረገ ግን ባለመስማማት ተለያዩ ፤ ከዚያም ባልታወቀ ሁኔታ ኢሃፓ ፈራረሰ ፡፡ሌላው ታሪክ ደግሞ ኢትዮጵያን አንድ አድርገን በሰላም እንኑር ሲል የነበረው የሰሜን ትግራዩ ተቃዋሚ ቡድን ስለኢትዮጵያ አንድነት ሲሰብክ የአሁኑ ባንዳና ጎጠኛው የትግራይ አማጺዎች እነመለስ ዜናዊ መስማማት ተሳናቸው፤የምን ኢትዮጵያ ነው አሉ፤አኛ ትግራይን አንጅ ኢትዮጰያን አናውቅም አሉ፤በወቅቱ የመንግስቱ ሀ/ማሪያም መንግስት በመላው ሀገሪቱ በነበረው አመጽ ተዳክሞ ነበር ፤በዚያው በትግራይ ሁለቱም ወገኖች በአሁኑ ወያኔ እምቢተኝነት ቀኑ ጨለመ፤ሁሉም በስብሰባ ተዳክመው ስለነበር ወደ መኝታቸው አመሩ፤ ሲነጋ አዲስ ነገር ተከሰተ ፤የትግራዩን ተቃዋሚ የራሳቸውን ወገኖች፤ የነጻነት አቀጣጣዮች በጥይት ተረሽነው ተገኙ፤ ነገሩን ሸፋፈኑት፤ለራሳቸው ዘር ያላዘኑ ሰዎች ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ያዝናሉ፤በደም የተጨማለቀ እጅ ባለቤት ናቸው፡፡ ከዚያም በሂደት አጋጣሚውን ተጠቅመው ኢትዮጵያን ወረሩ፡፡ የኦሮሞና የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ አማፂዎችን መግደል ማስፈራራት ጀመሩ፡፡ ውሸት ፤ማስመሰል ፤ሰውን መግደል የወያኔ ህግና ደንብ ነው፡፡ ከዚያም ተቀናቃኝ ስላልነበራቸው ሌላ ሀሳብ መጣላቸው ፤ወያኔ ያላሰበውን ሲሳይ በማየቱ ስልቱን በመቀየስ የኢትዮጵያ ህዝብን በማታለል በድብቅ (በህቡዕ) መራመድ ጀመረ፡፡ ህዝቡ እርስ በርሱ ሲበላላ ሲተራራድ ድምጻቸውን አጥፍተው የእነርሱን አላማ የሚያሳካ የሕወሓት ህቡዕ ቡድን መሰረቱ፡፡
በመጀመሪያ በእግዚአብሔር ትእዛዝ በኢትዮጵያ ልጆች ደም እየተጠቀሰ የተጻፈውን የሀገሪቱን ህገ መንግስት ባንዳዎች በመሰሪና ውሸታም ፤ነፍሰ ገዳይ እጃቸው አረሙት፡፡ ያኔ ነበር ኢትዮጵያ ህዝቦቿ አንዳይፋቀሩ ፤አንዳይጠራጠሩ የሚያደርግ፤ ለታላቋ ትግራይ መወለድ መንገድ የሚጠርገውን አንቀጽ 39 የወለዱት፡፡ ወያኔ ለአማራ ያላቸው ጥላቻ የሚደንቅ ነገር ነው፤ የሰሩትን አና የመሰሩትን ስለሚያውቁ አማራን ይፈሩታል፤ አምርረው ይጠሉታል፤ በአንድ ወቅት የቀድሞው ጠ/ር መለስ ዜናዊ ጥንተ ጠላታችን ድህነት ነው በሚለው አንደበቱ ጥንተ ጠላታችን አማራ ነው፤ አማራ መጥፋት ያለበት ዘር ነው ብሎ ለትግራይ አመራሮች በትግርኛ ቋንቋ ተናግሮ ነበር፡፡ ንጹህ የኢትዮጵያ ልጅ የሆኑትን ህዝቦች በዘር እየከፋፈሉ አንተ ኦሮሞ ነህ፤አንተ አማራ ነህ፤ አንተ ሶማሌ፤ጉራጌ፤ወላይታ ወዘተ እያሉ የሚያፋጁት ሕወሓቶች ቀጥሎም ሌላ ሴራ ጀመሩ፤ በሰለጠነ ዘመን ደካማ ቃላትን እየፈጠሩ አንተ እኮ ጺላ ተብለሃል፤ ጋላ ተብለሃል፡ ወላሞ ተብለሃል፤ቅማላም ተብለሀል፡ ጨቋኝ ተብለሀል፤ትምህክተኛ፤ ጠባብ እያሉ ህዝቡን የማዘናጋት፤ግራ የመጋባት ስሜት ውስጥ ከተውት ቆይተዋል፡፡ ሌላም በሚመቻቸው መልኩ ለዘጠኝ ከፈሉና ዘጠኝ ዘር ነው ያለህ አሉት፤ህዝቡም በደካማ ጎኑ ገቡበትና አመናቸው፡፡ በዘር ማባላት እንኳ ባይሳካላቸው በሀይማኖት ስልታቸውን ቀይሰው ይመጡብሃል፡፡ይህ ሀይማኖት የኦሮሞ ነው ነው ይህ ሀይማኖት የአማራ ነው ይህ ሀይማኖት የደቡብ ነው ብለው ዘሩን ከሀይማኖት ያደበላልቃሉ፡፡ ከዚያም ህገ መንግስቱ መንግስትና ሀይማኖት የተለያዩ ናቸው በማለት ውሸት አቀነባብረው ሀዝቡ ነው ጥፋተኛ ለማለት በኢቲቪ ይዘው ይቀርባሉ፡፡ በተለይም በሙስሊሞች ላይ የሚያደርጉት ጫና አሰቃቂ ነበር ስለ እኩልነት ያነሳ ሙስሊም ሁሉ አሸባሪ ነህ እየተባለ ከርቸሌ ይወረወራል፡፡ ይህ ሌላ የወያኔ ሴራ ስለሆነ ከመሬት ተነስተው የአልሻባብ ምልምል ነው ብለው ህዝቡን እንዲነግሩት ለእነንትና በኢቲቪ ውሸት አንዲቀነባበር ትእዛዝ ያስተላልፋሉ፡፡ ይህ አማራጭ የማይሳካ ከሆነ ደግሞ በህቡዕ ቡድኑ ትእዛዝ ታማኝ ፌዴራል ፖሊስ ፤ሲቀጥል አጋዚ ጦርን በህዝቡ ላይ በመልቀቅ በስናይፐርና በመትረየስ ጠላታቸው የኢትዮጵያ ህዝብን ጭንቅላቱን እያሉ ሀገሪቱን የጦርነት አውድማ በማድረግ ማሰብ እንድታቆም ያደርጉሀል፡፡ የአምቦ፤ የወለጋ፤የጎንደር፤የባህርዳር ወጣቶች ጭንቅላታቸውን በስናይፐር አቃጠሏቸው፡፡ አዲስ አበባ የተነሱ ሰላማዊ ሰልፎች በሙሉ በሀይል እርምጃ ተቋርጠዋል፡፡
በግፍ የተጨፈጨፉ አትዮጵያውያን ምስል በትንሹ
ይህ ሁሉ ነገር መነሻው እነሱ በፈጠሩት የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 ምክንያት ነው፡፡ ይህ አንቀጽ የተጻፈው በዘረኛውና ለክልሉ ህዝብ የቆመው የሕወሓት ህቡዕ ቡድን ትእዛዝ አማካኝነት ነው፡፡ ይህ አንቀጽ ሲጻፍ የሚከተሉት ሚናዎች ነበሩት፤ የመጀመሪያው አላማ የኢትየጵያን ህዝብ ከፋፍሎ ለመግዛት፤ህዝቦችን በዘር በመከፋፈል የፈጠራና ቀደምት ታሪኮችን በማንሳት በማጣላት፤ህዝቡ አንቀጽ 39 ነጻ ያወጣኛል ብሎ እንዲያስብ በማድረግ የጎጠኝነት አስተሳሰብ እንዲኖረው ማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛውና ዋነኛው የአንቀጽ 39 አላማ የሀገሪቱን ሀብት፤ንብረት ፤ሰፊና ለም መሬት ጠራርጎ በመውሰድ ታላቋን ትግራይ በመመስረት ሂደት ላይ በመሆናቸው ነው፡፡ በስተመጨረሻም የኢትዮጵያ ህዝብ ሲጠላቸውና በቂ ሀብትና ንብረት ከወሰዱ በኋላ ቀድመው ባዘጋጁት ሴራ መሰረት አንቀጽ 39 ፍሬ ታፈራለች፡፡ ይህም እስካሁን ሲጭበረበር እንደነበረው ምርጫ የተጭበረበረ ሪፈረንደም በማድረግ ታላቋን ትግራይ ይመሰርታሉ፡፡ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ አይለቃቸውም የትግራይ ምስኪን ህዝብ እንኳ ይነሳባቸዋል ፤ውለታ ቢስ ብሎ ምራቁን ይተፋባቸዋል፡፡
የሕወሓት መንግስት የህቡእ ቡድን ታላቋ ትግራይ የራሷን ሉዋላዊ ሀገር ይዛ እንድትቀጥል በማሰብ በ1983 ተመሰረተ፡፡ህቡእ ቡድኑ የራሱን የግንኙነት ጊዜ በመወሰን የጥፋት ስራውን ይገመግማል፡፡ ዋናው አጀንዳ የድንበር ወይም ይዞታ ማስፋፋት ጉዳይ ነው፡፡ ክልል ሶስት ወይም አነሱ ትምህክተኛ ብለው በሚጠሩት፤ በሚጠሉት ክልል የተያዘውን ሰፊና ለም የመሬት ይዞታ መንጠቅ ነው፡፡ በመጀመሪያ በህገ መንግስቱ እነሱ በሌባ እጃቸው ባሰፈሩት የብሄር ብሄረሰብ እኩልነት እያሉ፤ የትግራይ አጎራባች ለም አካባቢዎችን የቀበሌ አመራሮችን የሚያሰልጥን ፤ቋንቋናባህል የሚያስተምር ኮሚቴ ማወቀር ነው፡፡ ይህ የህቡእ ቡድኑ ያሰማራው ኮሚቴ ትእዛዙን ከቡድኑ በጸጋ ተቀብሎ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ ከዚያም ውሸት መፍጠር አንዱና ዋነኛው ዘዴያቸው በመሆኑ ለተነጣቂው ህዝብ አማራ ሲበድልህ ነው የኖረ እያሉ የህዝቡ ንጹህ አእምሮ ላይ ጥላሽት በመቀባት ብሎም በማስገደድ ሴራቸውን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በዚህም መሰረት የሕወሓት ህቡእ ቡድን ተሳክቶለታል፡፡ በመጀመሪያ ቡድኑ ራሱን በድብቅ ከመሰረተ በኃላ ለም መሬት የሆነውን ራያን ለራሳቸው አደረጉ፤ቀጥሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ያሳወቃቸውን ሰሊጥ ኤክስፖርት የሚያደርጉበትን መተማን ጠቅልለው ወሰዱ፤ ከዚያም የሰሜን ወሎ የቆቦን ግማሽ ክፍል ወሰዱ፤ ሌላውን ክፍል ህዝቡ አመጸባቸው፡፡ ይህን የሚያደርጉት የአጎራባች አካባቢዎችን ተወካዮች በመምረጥና ራሳቸው የማህበረሰቡ አካል በመሆን የትግርኛ ቋንቋ በማስተማር ፤የህብረተሰቡን ተወካዮች መቀሌ ከተማ በመውሰድ አይተውት የማያውቁትን መስተንግዶ በማሳየትና በቅንጦት በማሳበድ ህዝቡን እንዲያሳምኑላቸው ያደርጋሉ፡፡ይህ የህቡእ ቡድኑ ትእዛዝ ነው፤የሰቆጣ መሬት አፈሩ የተጎሳቆለ በመሆኑ ለጊዜው ኢላማቸው አይደለም፡፡ አሁን ደግሞ
አይናቸውን በጨው አጥበው፤በፍጹም ንቀት የኢትየጵያን ሀዝብ የሚያበሳጭ ስራ ሰሩ፤ የጀግናውን የጎንደር ህዝብ ፤ለኢትዮጵያ ታላቅነት ባለውለታ ህዝብ፤ከኢትዮጵያ አንድነት ውጭ ሌላ ህልም የሌለውን የጎንደር ህዝብ፤የአማራ ህዝብ ቅስም የሚሰብር ፤ያኔ ስልጣኔ ባልነበረበት ዘመን እንኳ ከጎጠኝነት በጸዳ ስለሀገር ሲጨነቅ የነበረው የአማራ ህዝብ አሁን ሀገሪቱ ሲኦል ሆና ከዳችው፤እሱም አንደ ኦሮሞ አና እንደ አፋር መኖሪውን እየተነጠቀ ሀገሬ ናት ብሎ ሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሆዱን ለመሙላት ሲባክን በሄደበት ይገደላል፡፡ እናም የክልል ሶስት ንብረት የሆነውን ወልቃይት የሰሜን ጎንደር ሰፊ ለም መሬት ለራሳቸው አደረጉ፡፡ የአመጹ መሪ ተዋናይ ኮለኔል ደመቀ ዘውዴ በአንደበቱ እንዲህ ሲል ተናገረ ‘ ትገሬ ነኝ ብለህ ወላቃይት ለትግራይ እንደሆነች ማረጋገጫ ስጥና ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር( 2,500,000 ብር) እንስጥህ አሉኝ ፤እምቢ ሀገር በብር አይሸጥም አልኳቸው ፤ አንለቅህም ብለውኛል ፤ ህዝቤ ሆይ እኔን እንደሚገሉኝ አውቃለሁ አንተ ግን ትግልህን ቀጥልና ሀገርህን አስመልስ ፤እንደኔ ለለሀገርህ ከታገልክ እኔም እተርፋለሁ ፤አደራ ብሞትም ትግልህ እንዳይቆም ብሎ ተናገረ’ ህዝቡም ሸለመው ዳግማዊ አጼ ቴወድሮስ ብለንሃል አለው፡፡ ጎንደር፤አምቦ፤ባህር ዳር፤ሀረር ፤ደሴ፤አዲስ አበባ፤ወለጋ፤ጂማ የግብጹን ታህሪር አደባባይ ለመድገም ተዘጋጅተዋል፡፡ጎንደርና ጎጃም እንደወንድሞቹ የወለጋ፤የአምቦ፤ የሻምቡ ፤የሐረር፤የኮንሶ፤የአዲስ አበባ፤ወዘተ ህዝቦች ወጥቶ ሲያለቅስ የሕወሓት ወታደሮች ጥይት አርከፈከፉበት፤የአጋዚ ወታደሮች ምስኪኑን ህዝብ ጭንቅላቱን በስናይፐርና በመትረየስ አፈራረሱት፡፡ይህም የህቡእ ኮሚቴው ሴራ ነው፡፡ቅድመ ጠላታቸው አድርገው የሚያስቡት የክልል ሶስት ህዝብ ከሌሎች የኢትዮጵያዊነት መንፈስ አቀንቃኝ ህዝቦች ጋር አጣሉት አዋረዱት፡፡እነ አቦይ ስብሀት፤ደብረ ጽዮን ፤ ሳሞራ የኑስ እና ሌሎች የሕወሓት አመራሮች ቡድኑን በግንባር ቀደምትነት ይመሩታል፡፡ ኢትዮጵያም የምትመራው እነዚህ ሰይጣን ሰዎች በሚያስተላልፉት መልእክት ነው፤የኦህዴድ፤የብእዴን፤የደህዴን ቡችሎች እንደ መሳሪያ ወይም የሴረኞች መልእክት ማስተላለፊያ ማይክራፎኖች ናቸው፡፡ከዚህ የበለጠ ሚና ባይኖራቸውም ለህዝቡ አይን ማረፊያ መሰረተ ልማቶችና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ስለሚሰሩ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡ ነገር ግን ንጹህ ሰዎች አይደሉም ፤ካሳ ተክለ ብርሃን አማራ አይደለም፤አባዱላ ኦሮም አይደለም፤ ኩማ ደመቅሳ ኦሮሞ አይደለም፤በረከት ስምኦን ኤርትራዊ ነው ፤ ነገር ግን በብእዴን ና ኦህዴድ ስም ተገደው ይኖራሉ፡፡
የኢትዮጵያ የመንግስት መዋቅር ከ95 በመቶ በላይ የተያዘው በሕወሓት አመራሮች ነው፤ቀሪው 5 በመቶ በሌሎች ቢሆንም ምክትላቸውና ደህንነቶች የራሳቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ለአብነት ብንመለከት የሕወሓት ህቡእ ቡድን አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው፡- ቁልፉ የመከላከያ ሚኒስተር በሕወሓት አመራሮች እጅ ነው፤ከ95 በመቶ በላይ የወታደር አመራሮች በየቀጠናው የሕወሓት ሰዎች ናቸው፤ ውትድርና የተከበረ ሙያ ነው ለሌላው ግን ፈተና ነው፡፡የመረጃና ደህንነት መረብ ኤጀንሲ ውስጥ ከባለሙያ ጀምሮ የሕወሓት ሰዎች ናቸው፡፡ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ፤የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ፤አራት ኪሎ ከወታደር ጀምሮ የአንድ ቋንቋ የበላይነት ይታይበታል፡፡ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ቁልፍ የመንግስት መዋቅሮች የተያዙት በሕወሓት ሰዎች ነው፤ታጋይ ነኝ ያለ ሁሉ ባይማርም ዲግሪ ተሰጥቶት መሪ ይሆናል፤ አሁን ደግሞ ታጋይ ሲያልቅባቸው ለሰዎቻቸው ታጋይ የሚል ታፔላ እየተለጠፈ ወደ አዲስ አበባ እየተላኩ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ታላላቅ ሆቴሎች፤ታላላቅ ህንጻዎች፤የንግድ ቦታዎች፤ አስመጭና ላኪዎች፤ታላላቅ የግል ኮሌጆች፤የግል ት/ቤቶች፤ኢንቨስትመንቶች፤ የኮንስትራክሽን ተቋራጮች ፤ታላላቅ የቢዝነስ ቦታዎች ለሕወሓት ሰዎች ነው፡፡ ለኢንቨስትመንት ተብሎ የሚሰጠው ቦታ ለማንም የኢትዮጵያ ህዝብ አይሰጥም፤ማንም ጠይቆ የኢንቨስትመንት ቦታ አያገኝም፤መሰናክሎች ይበዙበታል፤የትግራይ ተወላጅ ሆኖ በሕወሓት ዘሩ የተጠና ከሆን ጉዳይ ለማስፈጸም በሚሄድበት ቢሮ ሁሉ የይለፍ ደብዳቤ ተዘጋጅቶ ይጠብቀዋል፤ይህ የኢሉሚንስቶች አሰራር በሕወሓት መንግስት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ቆይቷል፤ አብዛኛው የሕወሓት ዘር ያለው ሰው በአዲስ አበባ ውስጥ በግልም በመንግስትም የተሰጠው ከበቂ በላይ መኖሪያ ቤት አለው፡፡ከ100 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን አንኳን ቤት ሊኖረው ነገ ስለሚበላው ምግብ ሲጨነቅ ያድራል፡፡ ቢርበውም ጤና የሰጠኽኝ አምላኬ እያለ እያመሰገነ ይተኛል፡፡
አነጋጋሪው ጉዳይ ደግሞ ለሱዳን የተሸጠው መሬት አቀማመጥ ከትግራይ ተነስቶ ወደ ጎንደር 60 ኪሎ ሜትር ገባ ብሎ እስከ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ታላቁን የህዳሴ ግድብ ያለበት ስፍራ የሚነካ ቦታ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ በታላቅ ሞራልና ቁጭት የሚሰራው ግድብ ቢሆንም በአስደናቂ ሁኔታ የሕወሓት ህቡእ ቡድን እጁን ማስገባቱ ነው፡፡ የአሁኑ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን በወቅቱ የክልል ሶስት ምክትል ፕሬዝዳንት የነበረ ሲሆን የወቅቱ የክልል ሶስት ፕሬዝዳንት አቶ አያሌው ጎበዜ ከላይ የተጠቀሰው የመሬት ይዞታ ለሱዳን ይሸጥ የሚል ጥያቄ ሲቀርብላቸው አሻፈረኝ በማለታቸው በሌላ ምክንያት ወደ አሜሪካ እንዲሄዱ የሕወሓት ህቡእ ቡድን አዘዘ፡፡ ከዚያም ይህ የአሁኑ ምክትል ጠ/ሚንስተር ደመቀ መኮንን ቢሮ በመግባት የክልሉን መሬት የሽያጭ ውል እንዲፈርም ተደረገ፡፡ በጣም ለማመን የሚከብደው ግን ይህ የጎንደር ፤የቤንሻንጉል ጉሙዝ መሬት እስከ ግድቡ ድረስ ያለው በውሉ መሰረት ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ በኋላ ለሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ለትግራይ ክልል የሚመለስ እንደሆነ በተረዳ ጊዜ አቶ ደመቀ መኮንን ቅሬታ ቢያቀርብም በሳሞራ የኑስ ወታደሮች ታፍኖ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ሞትን ጨምሮ ተሰጠው፡፡ እሱ ግን በወቅቱ ከተሰጠው አማራጮች ለሱ የሚሻለውን አሁን ያለበትን ቦታ መረጠ፡፡
ይሁንም እንጅ ይህች ቅድስት ሀገር ሁሉም ሀይማኖቶች ተዋደው ተከባብረው የኖሩባት አምላክ ቃልኪዳኑን የሰጣት ሀገር ወደ ነበረችበት ታላቅነት ትመለሳለች፡፡
የትግራይ ህዝብ ሲበዛ ደግ ህዝብ ነው፤ለትግራይ ምስኪን ህዝብ ትልቅ ክብር አለኝ፤የተከበረና አምላክን የሚወድ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ አክሱም ጽዮንን ጠብቆ የኖረ፤ታላቁን የሙስሊም መስጂድ የጠበቀ፤ታታሪና ለፍቶ አዳሪ የእግዚአብሔር አምላኪ ህዝብ ነው፡፡ ነገር ግን ከእሱ አብራክ የወጡ ምንም ሳይኖረው ፤ሳይማር ያስተማራቸው ልጆቹ ሀገር ሻጭ እንደሆኑ አያውቅም በድብቅ ለእርሱ እንደሚሰሩለት እንኳን አያውቅም፡፡የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ነገር ግን ባለስልጣናትና የተማረው የትግራይ ህዝብ ይህን ስሜት አይወደውም፡፡ስለዚህ የመሰናዶ ትምህርት አጠናቀው ወደ ተለያዩ ክልሎች የሚሄዱ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የሕወሓት ህቡእ ቡድን ሚስጥር በጥቂቱ ይነገራቸዋል፡፡ከዚያም ራሳቸው ተመራምረው አላማውን ማወቅ ይችላሉ፡፡ተራውና ኗሪው የትግራይ ህዝብ በነዚህ ትንሽ ሰዎች በመላው ኢትዮጵያ እንዲጠሉ፤እንዲዋረዱ ፤አንገታቸውን ዝቅ አድርገው እንዲሄዱ፤ በቋንቋቸው እንዲያፍሩ፤ስማቸውን ከክርስትና ስማቸው ውጭ እንዲያወጡ እያደረጋቸው ነው፡፡የሕወሓት ህቡእ ቡድን በዚህ ሴራው አላቆመም ሁሉንም የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተለያዬ ታሪክ በመፍጠር ማፋጀት፤መግደል፤ማዋረድ ቀጥሎበታል፤የራሱን ወገን ጨምሮ፡፡
ከምንም በላይ የኦሮም ብሄር እየደረሰበት ያለው ግፍና መከራ ከልክ ያለፈ ነው፤ በየጊዜው የሕወሓት አመራር ከህቡእ ቡድን ጋር በመነጋገር በሚፈጥረው የጥፋት ስልት የኦሮሞ ህዝብ ለታላቅ ሰቆቃ ተዳርጓል፡፡አንደኛው በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይ ባነሱት ጥያቄ ብቻ ከ400 በላይ ንጹህ ኢትዮጵያዊ የክልል አራት ልጆች ተገድለዋል፤ ብዙዎች ቆስለው አካል ጉዳተኛ ሆነዋል፤ ሌሎቹ አሸባሪና የኦነግ ተላላኪ ተብለው ከርቸሌ ገብተዋል፤ቀሪዎቹ ታፍነው የት እንደገቡ አይታወቅም ፡፡
የሕወሓት ህቡእ ቡድን ማስተር ፕላኑ ለምን አስፈለገው?
የማስተር ፕላኑ ዋና አላማ የአዲስ አበባ ከተማን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን የሕወሓት ወገን ኢንቨስተሮችን ለመጥቀም የታቀደ ነበር፡፡አዲስ አበባ ውስጥ ለኢንቨስትመንት ምቹ አለመሆንና በቂ ቦታ አለመኖሩ በሕወሓት ህቡእ ቡድን ተለይተው የተመዘገቡ ኢንቨስተሮች ቁጥር በመጨመሩ የታለመ እንጅ የኦሮሞን ህዝብ ለመጥቀም አልነበረም፡፡ጀግናው የኦሮሞ ህዝብ ግን ደሙን አፍስሶ ቅስማቸውን ሰበራቸው፤ እንደሚታወቀው የኦሮም ህዝብ ታጋሽ፤አዋቂ፤ለፍቶ አዳሪ፤ለታሪኩ የሚጨነቅ ህዝብ ነው፡፡ ኦሮሞን ከሌሎች ክልሎች በማጋጨት በሕወሓት ህቡእ ቡድን በተመለመሉ በመቶ ሺዎች በሚቆጠሩ የደህንነት አባላት አማካኝነት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚስጥር በመዘዋወር የህዝቡን ልብ፤የህዝቡን ታሪክ በመለወጥ፤ያልሆነ ታሪክ በመፍጠርና በማሳመን እንደቀላል የታሪክ አጋጣሚ የሚታለፉ ጉዳዮችን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ትርፍ ይጠቀማሉ፡፡ይህንን ደግሞ የክልል አራት ህዝቦች በግልጽ አውቀውታል፡፡
በቅርቡ ወንድምሀ የእናትህን ጡት ቆርጧል ለምን ዝም ትላለህ ብሎ ከስር ከስር መርዛቸውን ረጩባቸው ስለዚህ አኖሌ ላይ ሀውልት በማቆም ሁልጊዜ በማሳየት የዘላለም ጠላትህ ናቸው አሉት፤ የራሳቸውን ጥላቻ ለሁሉም ማካፈላቸው ነው፡፡በአንድ ብሄርና በአንድ ሀይማኖት ተመርተሃል እያሉ 25 አመት ሙሉ ጆሯችንን አደነቆሩት ፤ በዚህ ዘመን ሌሎች ሌላ ፕላኔት ለመኖር እተዘጋጁ ባሉበት ጊዜ፤የኢትዮጵያን ህዝብ የአማራ እምነት ያንተ አይደለም ይሉታል ፤ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ሀገር ሀገር ሆና እንድትቀጥል የሆነ ትውልድ ጥረት አድርጓል፤ዛሬ ደግሞ የሁሉም ሚና ነው፡፡
ቤንሻንጉል ጉመዝ ክልልን በታላቋ ትግራይ ግዛት ስር ለማድረግ በቡድኑ የደህንነት አባላት አማካኝነት ለየዋሁ የጉሙዝ ማህበረሰብ ታሪክ በመፍጠር በሺዎች የሚቆጠሩ የአማራ ህዝቦች ተፈናቀሉ፤ ተገደሉ፤ተራቡ፡፡ በደቡብ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ የክልል ሶስት ሰዎች እንዲገደሉ ፤እንዲፈናቀሉ ተደርጓል፡፡
ለኢትዮጵያውያን ግልጽ ያልሆነው ጭቆና ደግሞ ታዳጊ ክልሎች እየተባለ አፋር፤ሶማሌ፤ ጋምቤላ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፤ የኦሞ ማህበረሰብ፤የኮንሶ ማህበረሰብ፤የአዊ ማህበረሰብ፤ የቦረና ማህበረሰብ ወዘተ ታዳጊ ወይም የአእምሮ ዝግመት ያለበት ህዝብ ነው ብለው በመናቅ ከውጭ በሚመጣ እርዳታ(ፍርፋሪ) ብቻ ሆዳቸውን እንኳ በማይሞላ ስንዴ ብቻ ደልለው ለዘላለም ተመጽዋች ሲያደርጓቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ዝም አለ፡፡ እነዚህ ክልሎች ያላቸውን አስገራሚ የተፈጥሮ ሀብት እየሄዱ ይዘርፋሉ፤ለውጭ ሀገር ዜጋ ያዘርፋሉ፤ ኢትዮጵያዊ ውስጥ ነዳጅ እንዳይወጣ የበኩላቸወን ጥረት አደረጉ፡፡ይህም የሕወሓት አመራሮች ሚስጥራዊ ሴራ ነው፡፡
ህቡእ ኮሚቴው የራሱን ሰዎች ቻይና፤ጀርመን፤አሜሪካ እና ሌሎች ሀገሮች እየላከ የሀገርን ሚስጥር ለመዝረፍ የሚያስችል ትምህርት ያስተምራል፤ሌላውን የኢትዮጵያ ልጅ አቡጊዳ ተማር ይላል፤የእርሱ አባላት የመጠቀ የቴክኖሎጅ እና ምጡቅ የሆነ ትምህርት አስተምሮ እንዲሰልሉለት ያሰማራል፡፡
እርሱ ባጸደቀው ህገ-መንግስት የብሔርብሔረሰብ መብት፤የቋንቋ እኩልነት እያለ የአካባቢውን ቋንቋ ተናጋሪ የሆነ ማህበረሰብ ወደፈለገው ክልል መሄድ ይችላል በማለት የክልል ሶስት አካባቢዎችን ትግረኛ ቋንቋ በማስተማርና የተለያዩ ሴራዎችን በመጠቀም ግዛቱን እያስፋፋ ነው፡፡ ቀድሞ የተሰረቀው የራያና የመተማ ህዝብ ከፊል ዜጋ ሆኖ ለም አፈሩን ብቻ እየተጠቀሙበት ባይተዋር ሆኖ ይኖራል፤ ሰሜኑ የትግራይ ክፍል ለነዚህ አካባቢዎች ዝቀተኛ ግምትና ከፍተኛ ንቀት አሏቸው፤ያገሏቸዋል፡፡
ክልልን በቋንቋ ማስፋፋት ቢሆንማ ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪዎች በኦሮሞ አጎራባች አካባቢዎች ይገኛሉ፤ኦሮሞ ይህን እድል ተጠቅሞ ክልሉን ለማስፋት ሴራ አልጠነሰሰም፤ በክልል ሶስት መሬት ልዩ የኦሮምያ ዞን ተብሎ በደቡብ ወሎ የሚገኙ ሰፋፊ ቦታዎች ቋንቋውንና ባህሉን ስለሚያዉቁ ተብሎ ወደ ክልል ሶስት ለማጠቃለል አይፈልግም፡፡
ስለዚህ ይህ ህገ መንግስት የሚሰራው ለሕወሓት ብቻ ነው፡፡ ግን እስከ መቼ ካልን ጊዜው አሁን ነው፤አሁን፤ዛሬ፤በቃ!!!
በኢትዮጵያ የጦር መሳሪያ ትጥቅ ህግ በተመለከተ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል መሳሪያ መስጠት አግባብ ባይኖረውም ሕወሓት ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ ለድርጅቱ ደህንነት በማሰብ የመጀመሪያው ተግባር የኦሮሞ፤የአማራ፤የአዲስ አበባ፤አፋር፤ደቡብ፤ ጉሙዝ ወዘተ ህዝቦችን ማሳሪያ መንጠቅ ታላቅ ተግባር ነበር፡፡ የአማራና ኦሮሞ ህዝቦች ያለ ምንም ቅደመ ሁኔታ እየተገረፉ መሳሪያ አንዲመልሱ ተደርጓል፡፡በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ከትግራይ ህዝብ ከመቶ እጥፍ በላይ የሚሆን መሳሪያ በሕወሓት ህቡእ ቡድን አማካኝነት ተጓጉዞ ወደ ክልል አንድ ገብቷል፤በየቀኑ ሳይፈተሹ የሚገቡ የተከለከሉ የጦር መሳሪያዎች ጭምር ይጋዛሉ፤ይህን ሚስጥር ያወጣ አንድ የፓርላማ አባል አሁን በእስር ላይ ይገኛል፡፡
ይህ ታላቅ የህዝብ ጥሪ ነው፡፡
በሊቪያ ፤በግብጽ ፤በቱኒዝያ፤በሶሪያ፤በየመን የተቀሰቀሰው አመጽ መንግስት ቀይሯል፤አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ተደገመ፡፡ መንግስት ስልጣን የሚይዘው ህዝቡን በሰላም፤በምቾት፤በእውነት እንዲመራ ነው፤በረሃብ ፤በመግደል፤በማሰቃየት፤ሀገር በመሸጥ፤የሌለውን ክልል መሬት በመንጠቅ ለሌላው በመስጠት መሆን የሌበትም፤ ወንድም ከወንድም ማጋጨት መሆን የለበትም፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር እስከዳር የተነሳው የበቃኝና የመሰላቸት ጩኸት መቀጠል ይኖርበታል፤በሐረር፤በድሬዳዋ ፤በአዲስ አበባ ፤በወለጋ፤በባህርዳር፤በጎንደር፤በደብረታቦር፤በደብረማርቆስ የተነሳው አመጽ በሁሉም አካባቢዎች ይጠናከራል፡፡
እግዚአብሔር አንድ ጊዜ ለዚህች ሀገር ቃልኪዳን ሰጥቷል፤በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ ሀያል ሀገር እንደምትሆን ቅዱሳዊ ትንቢት አለ፤ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ከአሜሪካ በላይ ሀያል ሀገር ትሆናለች፡፡
ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ተነስ ምን ትጠብቃለህ ይህን ባንዳ መንግስት በቃህ በለው!!!
***********************
ኢትዮጵያ ከሕወሓት ቅኝ አገዛዝ ትላቀቃለች ወደ ቀድሞ ታላቅነቷ ትመለሳለች!!
“ለሱዳን ተሸጠ የተባለው መሬት፤ወልቃይት፤ራያ፤አላማጣ፤መተማና ቆቦ የኢትዮጵያ ናቸው፤እነዚህ ቦታዎች ሳይመለሱ ኢትዮጵያ ዝም አትልም፤ ማሪያምን!!!” Love Ethiopia
*************************
ይህን መረጃ ኮፒ በማድረግ ለሌሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውን ይድረስ፡፡
ምንጭ፡- የወጣ ሚስጥር፤ከተለያዩ ድህረ ገጾች፤መጽሃፍትና ከወቅታዊ ጉዳዮች የተቀነጫጨበ (05/12/2008ዓ.ም ተጻፈ)
ነሀሴ 5/2008 ዓ.ም ሰላም፤ነጻነት፤አንድነትና ብልጽግና ለኢትዮጵያ!! ABTAGAAF!
ነሀሴ 5/2008 ዓ.ም ሰላም፤ነጻነት፤አንድነትና ብልጽግና ለኢትዮጵያ!! ABTAGAAF!

No comments: