Saturday, August 20, 2016

የኢሕአዴግ መሪዎች ስብሰባ ላይ ናቸው – #ግርማ _ካሳ

13718659_10206916631415176_7092775451734766644_n
የኢሕአዴግ መሪዎች ስብሰባ ላይ እንዳሉ አይጋ ፎረም ዘገበ። ወንበር አሙቀው “እናሻሽላለን፣ ኪራይ ሰብሳቢነትም መልካም አስተዳደር …” ብቻ ብለው ያልፋሉ ወይስ ለነርሱም፣ ለድርጅታቸውም ለአገርም የሚጠቅም ዉሳኔ ይወስናሉ ? የምናየው ይሆናል።
“ኢትዮጵያ በዘር አትከፋፈልም ይለናል። በሕዝብና በሕዝብ መካከልም ምንም ችግር እንደሌለ ያክላል። አይጋ ልክ ነው። በሕብዝን በሕዝብ መካከል ችግር ኖሮም አያውቅም፣ አይኖርምም። ሆኖም ግን “በዘር አትከፋፈልም” ያለው ግን ስህተተ ነው። ኢትዮጵያ በዘር ተከፋፍላለች። ሕገ መንስቱ አገሪቷን በዘር ነው የከፋፈለው። አገራችን በዘር መከፋፈሏ የሚቆመው፡
– የዘር ክልልና የዞን አወቃቀር ሲቀየር ነው።
– አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ የትግሬ መሬት፣ የአማራ መሬት፣ የኦሮሞ መሬት ..የሚባለው ፖለቲካ ሲቆም ነው።
– ማንም ኢትዮጵያ በሁሉም የአገሪቷ ግዛቶች የመኖር መብቱ ሲረጋገጥ
እነዚህ ደግሞ ሊሆኑ የሚችሉት የህወሃት የዘር ፖለቲካ ሲቀየር ነው። ኢትዮጵያዊያን በዘራቸው ሳይሆን በምግባራቸው ሲመዘኑ ነው። ከአንድ ጎሳ የሆኑ ሰዎች የበላይ የሆኑባት ሁኔታ ሲቀየር ነው።
የኢሕአዴግ መሪዎች ስብሰባ ላይ እንዳሉ አይጋ ፎረም ዘግቧል። ወንበር አሙቀው “እናሻሽላለን፣ ኪራይ ሰብሳቢነት፣ መልካም አስተዳደር …” ብቻ ብለው ያልፋሉ ወይስ ለነርሱም፣ ለድርጅታቸውም ለአገርም የሚጠቅም ዉሳኔ ይወስናሉ ? የምናየው ይሆናል።
የኢሕአዴግ መሪዎች ምን ያህል የዘር ፖለቲካቸው አገሪቷን ቀውስ ወስጥ እንደከተታት በመረዳት፣ ሁሉም እኩል የሆኑባትን ኢትዮጵያ ለመገንባት ይቻል ዘንድ፣ በሕዝብ ዘንድም መተማመን ይኖር ዘንድ፣ እነርሱንም ያካተተ የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ቢወስኑ ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ።
የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ የአገር ችግር በሰለጠነ መልኩ እንዲፈታ ካልተደረገ፣ አገዛዙ ሌላ የሚያቀርባቸው አማራጮችም ሆነ የሚሰጣቸው ተስፋዎች የሚቀበል ማንም አይኖርም።የበለጠ ቀዉስ፣ የበለጠ ደም መፋሰስ፤ የበለጠ ብጥብጥ ነው የሚሆነው።
አይጋ የጻፈዉን ከዚህ በታች እንሆ
“All,
The extremist media may have overwhelmed you by all the, manufactured or otherwise, negative news about Ethiopia of late! Ethiopia is a stable country with a very strong and sound foundation. The challenges it is facing today are not new. The challenges are similar to what most developed democratic countries faced at one time or another. We are told EPRDF executives are in a meeting to assess current developments. Judging from past performance we are convinced the party will emerge stronger and correct any missteps there are. Above all, rest assured Ethiopians will not be divided along Ethnic lines. We do not need to remind you about the kindness and gentleness of our people. Do not believe what the extremists are telling you! There is no people to people quarrel in Ethiopia. Simply EPRDF is growing up through the challenges and it will grow up!…Aigaforum 08-19-16 “
Source:  mereja

No comments: