Tuesday, April 21, 2015

በአ. አ. አይሲኤል እና ቸልተኛው የኢትዮጵያ መንግስትን በመቃወም ድንገት የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቭዲዮ (Video + Text)


ዘ-ሐበሻ) አይሲኤል የተባለው አሸባሪ ቡድን 28 ኢትዮጵያውያንን በሊቢያ ሕይወታቸውን ካጠፋ በኋላ ዛሬ በአዲስ አበባ እየተደረገ ባለው ድንገተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሐዘኑን ሊገልጽ ክወጣው ሕዝብ መካከል ወጣቶች እየተመረጡ በቆመጥ ተደበደቡ:: ሕገወጥ ሰልፍ አድርጋችኋል በሚልም ሕወሓት የሚመራው መንግስት ወጣቶችን እያሰረ ይገኛል::
28 ኢትዮጵያውያን ነብሳቸውን በአይሲኤል ሲነጠቁ ዜጎቼ መሆናችውን አላጣራሁም ሲል በሟቾቹ ጉዳይ ግድም እንደሌለው ያሳየው ሕወሓት የሚመራው መንግስት ወታደሮቹን በማሰማራት በመስቀል አደባባይ በመሰብሰብ ላይ የነበረውን ሕዝብ መደብደቡ የሃገር ፍቅርና የወገን ፍቅር ከሌለው መንግስት የሚጠበቅ ተግባር ነው ሲሉ የፖለቲካ ተንታኞች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ::
addis ababa cherkos
ወደ መስቀል አደባባይ በአይሲኤል እና በዜጎቹ ላይ ቸልተኛ በመሆነው የኢትዮጵያ መንግስት ላይ ተቃውሞውን ለማሰማትና ለሞቱት ወንድሞች ሐዘኑን ለመግለጽ የወጣው የአዲስ አበባ ሕዝብን በመስቀል አደባባይ በብዛት እንዳይሰበሰብ የመንግስት ወታደሮች ወደ መስቀል አደባባይ በተቃውሞ የሚተመውን ሕዝብ ከየመጋቢ መንገዶች እየቆረጡ ሕዝቡን ለማስቅቅረት እየሞከሩ ነው ተብሏል::
ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን

No comments: