Saturday, April 25, 2015

በወይንሸት ሞላ ላይ የሀሰት የሰው ምስክር እንደቀረበባት ተሰማ

መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵውያን ላይ የወሰደውን እርምጃ ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ላይ ገና ሰልፉ ሳይጀመር ‹‹ለምርመራ እንፈልግሻለን›› ተብላ በደህንነቶች ከተያዘች በኋላ የታሰረችው ወይንሸት ሞላ ላይ ደህንነቶች ‹‹ሁከትና ብጥብጥ ስትፈጥር አይተናል፡፡›› ብለው እንዲመሰክሩ ሁለት የሀሰት የሰው ምስክሮች እንዳቀረቡባት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ወይንሸት ከታሰረች ጀምሮ ደህንነቶች ሌሊት ሌሊት ከፍተኛ ምርመራ እንደሚያደርጉባትም ታውቋል፡፡

ወይንሸት ሞላ በትናንትናው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርባ 6 ቀን የተቀጠረባት ሲሆን ደህንነቶች ያቀረቡባት የሀሰት የሰው ምስክሮች በሚቀጥረው ፍርድ ቤት ስለመቅረብ አለመቅረባቸው የታወቀ ነገር የለም፡፡

No comments: