Thursday, September 26, 2013

የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው በፖሊስ እየተዋከበ ነው

የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው በፖሊስ እየተዋከበ 

ነው


ለቅስቀሳ ዛሬ ማለዳ ወደ ፈረንሳይ አካባቢ ተንቀሳቅሶ የነበረ መኪና በፖሊስ ቁጥጥር 

ስር መዋሉን መግለጻችን አይዘነጋም፡፡እውቅና ለተቸረው ሰላማዊ ሰልፍ 

የሚደረገውን ቅስቀሳ ለመቅረጽና የህዝቡን ስሜት ለመመልከት ካሜራና ላፕ ቶፕ 

በመያዝ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የተጓዘው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው 

ከሌሎቹ የተለየ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ በስፍራው የሚገኙ ምንጮቻችን 

ገልጸዋል፡፡

ፖሊሶች በሶሻል ሚዲያው ህዝቡን እየቀሰከስክና የተለያዮ ምስሎችን በመለጠፍ 

የመንግስትን ስም የምታጠፋው አንተ ነህ በማለት አሸናፊን ማዋከባቸውንና አካላዊ 

ጉሸማ እንዳደረሱበት ለማወቅ ተችሏል፡፡አሸናፊን ጨምሮ በኣሁኑ ሰዓት በፖሊስ 

ጣብያው ሰባት ሰዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

#Millionsofvoicesforfreedom #Ethiopia #UDJ

No comments: