Saturday, September 7, 2013

ክስ ባልተመሠረተባቸው የሙስና ተጠርጣሪዎች ላይ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ በድጋሚ ተፈቀደ

ክስ ባልተመሠረተባቸው የሙስና ተጠርጣሪዎች ላይ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ በድጋሚ ተፈቀደ

ክስ ባልተመሠረተባቸው የሙስና ተጠርጣሪዎች ላይ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ በድጋሚ ተፈቀደ
እነ አቶ መላኩ ፈንታ በስህተት ፍ/ቤት ቀርበው ነበር 
ከኦዲት ምርመራ አለመጠናቀቅ ጋር በተያያዘ ክስ ሳይመሰረትባቸው በፀረ ሙስና አቃቤ ህግ ጉዳያቸው እንደገና ወደ ጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በተመለሰባቸው የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ላይ በድጋሚ የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ ተሰጠ፡፡
በትናንትናው እለት ዳኞች ተሟልተው ባለመቅረባቸው ጉዳያቸው በጽ/ቤት በኩል የታየው በእነ አምባው ሰገድ መዝገብ ተካተው የነበሩት አቶ ተክለአብ ዘርአብሩክ፣ በእነ አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መዝገብ ተካተው የነበሩት ባለሃብቶቹ አቶ በእግዚአብሔር አለበል እና አቶ ምሕረተአብ አብርሃ እንዲሁም በራሳቸው ስም በተሰየመው መዝገብ ተካተው የነበሩት ፍፁም ገ/መድህን ናቸው፡፡
የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ቀደም ብሎ በዋለው ችሎት በተሰጠው የ10 ቀን የድጋሚ ምርመራ ጊዜ ውስጥ የኦዲት ስራውን ሲከታተል መቆየቱን በማመልከት፣ አሁንም የኦዲት ስራው ባለመጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ለፍ/ቤቱ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ፍ/ቤቱም የኦዲት ስራው በምን ያህል ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የመርመሪ ቡድኑን የጠየቀ ሲሆን፣ መርማሪ ቡድኑም “በ15 ቀን ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል” የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ፍ/ቤቱም በመርማሪ ቡድኑ ከተጠየቀው የ14 ቀን ቀጠሮ ውስጥ 8 ቀን ብቻ በመፍቀድ መዝገቡን ለመስከረም 3 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡
በሌላ በኩል በትናንትናው እለት ጠዋት ክስ ተመስርቶባቸው የክሣሳቸውን ዝርዝር ለማዳመጥ ለጥቅምት 11 እና 12 ተቀጥረው የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታ እና አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾች በስህተት ፍ/ቤት ያለቀጠሮ የቀረቡ ሲሆን፣ የማረሚያ ቤቱ አጃቢ ፖሊሶችም ቀጠሮ እንዳልነበረ ካረጋገጡ በኋላ ተከሳሾቹን ወደ ማረሚያ ቤት መልሰዋቸዋል፡፡

No comments: