Wednesday, September 25, 2013

ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ አሰረ Ethiopian former Presidant and UDJ's current Chair Man Dr. Negasso Gidada is arrested by Ethiopian government

Ethiopian former Presidant and UDJ's current Chair Man Dr. 

Negasso Gidada is arrested by Ethiopian government

አንድነት ፓርቲ መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር 

ለሚያደርገው ሰላማዊሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የማነ አሰፋ፣ዳንኤል ሙላት፣ 

ወንድምአገኝ አስፋው ፣ መሳይ ትኩ፣ አብርሀም ታደለ፣ እስማኤል ዳውድ ፣ወርቁ 

እንድሮ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን ተከትሎ ወደ ጉለሌ 

ሽሮሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ያመሩት የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ 

መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ለፖሊሶቹ “እነዚህን ልጆች ለቅስቀሳ ያሰማራሁት 

እኔ ነኝ፤ እነሱን ለቃችሁ እኔን እሰሩኝ” ብለዋል፡፡ ፖሊሶቹም “አባሎቻችሁንም 

አንለቅም እርሶም አይወጡም” በማለት የቀደሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት 

አስረዋቸዋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩት ሽሮሜዳ አካባቢ 

ሲቀሰቅሱ የታሰሩ አባላት እንዲፈቱ ለመጠየቅ ሄደው ነው 

የታሰሩት"

#Millionsofvoices

No comments: