Thursday, March 19, 2015

የዞን 9 ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞቹ በድጋሚ ተቀጠሩ

zone9-e1398747809895
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው በእነ ሶሊያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያና ጋዜጠኞች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀርበው ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡
አቃቤ ሕግ በተከሻሾች ላይ ያቀረበው የኦዲዮ ሲዲ ማስረጃ እንዲደርሳቸው ባቀረቡት ጥያቄ ላይ ችሎቱ ብይኑን ስላልጨረሰ ለመጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ጋዜጠኛው እንዳለው ሁሉም ተከሳሾች ከችሎት መጀመር በፊት እስር በእርስ ተቀራርበው እያወጉ እና ፈገግ ሲሉ ተስተውለዋል

No comments: