Wednesday, September 21, 2016

ጠ/ር ኃይለማሪያም እንዳቀዱት ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማን እና ወ/ሮ ሱዛን ራይስን ማነጋገር አለመቻላቸው ታወቀ።

/ ኃይለማሪያም በሀገር መሪነታቸው ያነጋገሩት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደረጃ ሶስት ደረጃ በታች የሆኑትን የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ፀሃፊ / ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ እና የምስራቅ አፍሪካ ጉዳይ ተጠባባቂ ምክትል ፀሃፊ / ሻነን ስሚዝን መሆኑ ታውቋል። #EBC ሳይቀር ይህንን ዘግቧል። 
ሌላው #አሳሳቢ ጉዳይ አሜሪካን ትልቅ አጋርነት አላት ሀገር እንደሆነች ቢነገርም ከጠቅላይ ሚኒስቴሩ / ሊንዳ እና / ሻነን ስሚዝን ሲያነጋግሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቴድሮስ አድሃኖም በቦታው አልነበሩም። በቦታው የነበሩት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ግርማ ብሩ ብቻ ነበሩ። የዶ/ ቴድሮስ አድሃኖም መሰወር ምስጢሩ ከየህዋሃት ቁንጮ አመራር ጋር አለመግባባት እንደሆነ ጭምጭምታ ሲሰማ ከርሟል። 
/ ኃይለማሪያም አሜሪካን ለኢህአዴግ መንግስት ያላትን አጋርነት ለማረጋገጥ መንግስታቸው በሶማሊያ እና በደቡብ ሱዳን ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የሚያደርገውን መስዋዕትነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማሳወቅ ያደርጉት ሙከራ ሳይሳካላቸው ቀርቷል። እነዚህ ሁለት የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናት ባለውፈው ወር ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ Yilkal Getnet እና የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ ሊቀ መንበር እንዲሁም የመድረክ /ሊቀመንበር ከሆኑት ከዶክተር Merera Gudina ጋር ኢህአዴግን የማያካትት የአደራ መንግስት ስለመመስረት ጉዳይ መወያየታቸው ይታወሳል።

No comments: