Wednesday, December 24, 2014

ዳኛው ጠበቃ ተማምን አስጠነቀቁ



እነ ሀብታሙ አያለው ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የዛሬ ቀጠሯቸው መቃወሚያ ለማቅረብ የነበረ ቢሆንም ታህሳስ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በደረሰባቸው ድርጊት ፍርድ ቤቱ ሌላ ቀጠሮ ለመስጠት ተገዷል፡፡ በለቱ ሌሊት 8፡00 ላይ የእስር ቤቱ የስራ ባልደረባ ያልሆኑ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ለዛሬው ቀጧሯቸው የሚሆን የመቃወሚያና የመከራከሪያ ሰነዶቻቸውን ወስደውባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ገንዘባቸው እንደተወሰደባቸው ጠበቃቸው ተማም አባቡልጉ ተናግረዋል፡፡
ጠበቃው በገለጹት መሰረት “የተካሄደው ብርበራ ሳይሆን ዝርፊያ ነው” ያሉ ሲሆን “እስር ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ብቃት የለውም” በማለታቸው የለቱ ዳኛ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡ 
አስተያየት ሰጪዎች እንደተናገሩት ከሆነ ስርዓቱ ይህን የወንበዴ ድርጊት ለመፈፀም የተገደደው አንዲት ጠብ የምትል መረጃ ባለማቅረቡ በዛሬው ቀጠሮ በደንብ እንዳይከራከሩ ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቶታ ስጋት እንዳላቸው ገልፀው “አቤቶታችንን ለዚህ ፍርድ ቤት በማቅረባችን በቀል እርምጃ ይወሰድብናል፣ ደህንነት ስሜት አይሰማንም” ብሏል፡፡ ፍርድ ቤቱም እስር ቤቱ ታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም መልስ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ሰጥል፡፡
እነ ሀብታሙ አያሌው፣ አብረሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሽበሽ፣ የሺዋስ አሰፋ ከሀምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ቤት እየተሰቃዩ ነው፡፡

No comments: