Saturday, December 6, 2014

ፖሊስ ሰማያዉ ፓርቲ ጽ/ቤት የተነሳውን ሰልፈኛ እየደበደበ ይገኛል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሚመሩትና ከሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት የተነሳው የሰላማዊ ሰልፉ አካል ከፍተኛ ቁጥር ባለው ፌደራል ፖሊስ እንደራሴ ላይ ቆሟል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው 
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ አለሳ መንገሻ የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ፣ ወሮታው ዋሴ፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩስ ተስፋው፣ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ፣ ወይንሸት ሞላ፣ ሳሙኤል አበበ፣ እያስፔድ ተስፋዬ፣ሜሮን አለማየሁ፣ ንግስት ወንዲፍራው፣ ወይንሸት ንጉሴ፣ ምኞት መኮንን፣ አቤል ኤፍሬም፣ ኤፍሬም ደግፌ፣ ኃይለማሪያም፣ ሜሮን፣ ኢብራሂም አብዱልሰላም፣ እና ሌሎችም የትብብሩ አመራሮችና አባላት ከፍተኛ ቁጥር ባለው ፌደራል ፖሊስ ተይዘዋል፡፡ ነዋሪውን ወደየቤቱ እንዲገባ በማድረግና መኪና መንገድ በመዝጋትሜዳ ላይ እየደበደቧቸው ነው፡፡
የትብብሩን አመራሮች፣ አባላትና የሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊ ለመደብደብ ወደየ ቤታቸው እንዲገቡ ሲታዘዙ አልገባም ያሉ፣ መንገድ ላይ የተገኙና ሌሎችም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አልፎ ሂያጆች በፖሊስ እየተደበደቡ ነው፡፡
40 ያህል አመራሮችን ፌደራል ፖሊስ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን ከሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ጀምረው ወደ አብዮት አደባባይ በማቅናት ላይ ከነበሩት መካከል 40 ያህሉ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል፡፡ አቤል ኤፍሬምን ጨምሮ በርካታ የሰልፉ አስተባባሪዎች እራሳቸውን እስኪስቱ ተደብድበዋል፡፡
መስቀል አደባባይ እንዲሁም ካሳንቺስ ላይ የታፈኑትና ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች እስካሁን የት እንደተወሰዱ አልታወቁም፡፡ ከዜግዚቢሽን ማዕከል ወደ ሌሎች ቦታዎች እንደተወሰዱ የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

No comments: