Sunday, December 7, 2014

በሰላማዊ ሰልፍ ዝግጅት ወቅት የታፈኑት አባላት በሽብርተኝነት ተከሰሱ

በሰላማዊ ሰልፉ ዝግጅት ወቅት ከሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ አካባቢ በደህንነት የታፈኑ የሰማያዊና የመኢአድ አባላት እንዲሁም ሌሎች ግለሰቦች በሽብርተኝነት ተከሰሱ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ፍቅረ ማሪያም አስማማውና አወቀ ተዘራ፣ የመኢአድ አባል የሆኑት ተስፋሁን አለምነህና ሺፈራው ዋለ እንዲሁም ሌሎች አራት ግለሰቦች ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት አካባቢ በመገኘታቸው ብቻ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ ለቀናት የታሰሩበት ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡

በአሁኑ ወቅት ታሳሪዎቹ ኮተቤ ፖሊስ መምሪያ እንደሚገኙ የታወቀ ሲሆን ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ሽብር በመቀስቀስና ሁከት በመፍጠር›› ወንጀል ተከሰው ተጨማሪ 10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንደተቀጠረባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ዝግጅት ወቅት ታፍነው አሁንም ድረስ የት እንደደረሱ ያልታወቁ የ9ኙ ፓርቲዎች በተለይም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ሰላማዊ ሊጀመር ከመጀመሩ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት አካባቢ የታፈነችው ወንይሸት ንጉሴ ቤላ 18 ፖሊስ ጣቢያ ታስራ እንደምትገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ በምርመራ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) የሚገኙት ታሳሪዎች የፌስቡክና የኢሜል መክፈቻ ቁልፎቻቸውን እንዲሰጡ በግዳጅ እየተጠየቁ እንደሆነ ገልጸዋል፡ ከታሳሪዎቹ መካከል የሜሮን አለማየሁን ጨምሮ የሌሎች ታሳሪዎች ፌስ ቡክ ኦን ላይን መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል፡፡

No comments: