Friday, April 22, 2016

ወያኔ የጋምቤላዉን ጭፍጨፋ ተገን በማድረግ የከዱ ከፍተኛ የጦር አባላቶችን እያሰሰ ነዉ!!

58ff1366-d94a-4e24-90be-a6098c7e32d0
ሎዑል አለሜ
የህወሃት መከላከያ ከፍተኛ የሰራዊት እጥረት ገጥሞታል።
በአራቱም የሐገሪቱ መእዘናት ድንበሮችን መቆጣጠር የማይታሰብ እየሆነ መጥቷል! በሰሞኑ በጋንቤላ ክልል ኢትዮጵያዊያን ላይ የተቀናበረዉን ጭፍጨፋ ወያኔ በዋና አዘጋጅነት እንደተወነዉ ምንጮች እየገለጹ በሚገኙበት በዚህ ወቅት ላይ የሐገሪቷን ድንበር ለማስጠበቅ ከመካከለኛዉ እዝ ሰራዊት ለመመልመል ቢሞከርም የመካከለኛዉ እዝ ሰራዊት በአብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ የኦሮሞ ልጆቻችን ለማጽዳት በወንጀል ላይ ይገኛል!
የምስራቅ ኮከብ የሚባል ስም የተሰጠዉ የምስራቁ እዝም እጅግ ተመናምኗል በተለይም ይህ እዝ በተተኪ ሐይሎች ምክንያት እና በሰራዊት ክዳት እጥረት ገጥሞታል!
የምእራብ እዝ የሚባለዉ ወደ ሰሜኑና ወደ ምስራቅ እዝ ክፍተቶችን ለመሙላት በብዛት በመዘዋወሩ ከፍተኛ የሰራዊት እጥረት ፈጥሯል።
ህወሃት የአየር ሐይሉን ለማመን የሚችልበት ሁኔታ እጅግ አናሳ ደረጃ ላይ ይገኛል።
አሁን የጋምበላን ድንበር ተሻግሮ ለመምታት የሚያስችል አቅም በማጠሩ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ከሱዳን ጋር ድርድር ተይዟል።
ድርድሩ በኑሜር ብሔረሰቦች የተጠለፉ ሕጻናት እንዲመለሱልን እንፈልጋለን ስለዚህም ይህን አሰሳ ለማድረግ ሱዳን እዉቅና ትስጠን ነዉ።
ደቡብ ሱዳን ዉስጥ የሚኖሩ ወገኖቻችንን በሰጡት መረጃ መሰረት ህጻናቱን ማግኘት የማይታሰብ ጉዳይ ነዉ ይላሉ።
ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ወታደሮች ድንበር ጥሰዉ ይገባሉ በሚል መነሻ ሐሳብ የመከላከያ ሐይሏን ወደ ስፍራዉ አስጠግታለች! በተቃራኒዉ ግን የወያኔ ሚዲያዎች የሐሰት መረጃዎችን ተያይዘዉታል።
በተጨማሪ የወያኔ ወታደራዊ ሰላዮች የጋምቤላዉን ጭፍጨፋ ተገን በማድረግ በድርድር ሰበብ የትግራዩን ነጻ አዉጪ ቡድን ከድተዉ ሱዳን ዉስጥ ተሸሽገዋል ያላቸዉን 6 ከፍተኛ የመከላከያ መኮንኖች እንዲሁም 11 ወታደራዊ ደህንነቶችንና 3 የፌድራል ፖሊስ አዛዦችን ማፈላለጉን የተያያዘዉ ሲሆን ነገር ግን በትናንትናዉ እለት ሁሉም በሰላም ከደቡብ ሱዳን መዉጣታቸዉን ለማወቅ ተችሏል።
ድል ለኢትይጵያ ህዝብ!!

No comments: