Friday, November 15, 2013

TPLF security attacks peaceful protesters at the Saudi Arabia embassy in Addis Ababa, Ethiopia

TPLF security attacks peaceful protesters at the Saudi Arabia embassy in Addis Ababa, Ethiopia




አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።
Today 15/11/2013 around 5:15 AM Ethiopia local time few protesters were out on the streets and we have witnessed federal police were attacking them. Among them there were old people. What’s even more heart breaking was the Saudi Embassy people were sitting on their roof tops and smiling when the TPLF federal police beat up their own people. The idea of coming together today was not about the current government. It’s about our people who are being brutalized in Saudi Arabia.

ዛሬ 06/03/06(15/11/13) አገር ጉድ አለ። ዛሬ አገር ቤት በወገኖቻችን ለይ በሳውዲ አረቢያ የሚደርሰውን ግድያና እንግልት እንዲቆም ለሳውዲ ኢምባሲ ድምፃችን እናሰማ ባሉት የሰማያዊ ፓርቲ ልቀመበር ኢንጂነር ይልቃልንና ሁለት አመራሮችን ጨምሮ ሲያስር፤ ሕዝቡን ደግሞ ወደ ሰልፍ እንዳይሄድ በፖሊስ እያዋከባቸው ይገኛል። እንደዚህ አይነት እንደዜጋ እንኳን የዜጎቹ ቁስል የምይሰምውን ሰልፊሽ የወሮበላ ጥርቅም ነው መንግስት ነኝ እያለ እራሱን የሚጠራው።እንኳን ለለዜጎቹ ሊጨነቅ ከሳውድ አረቢያ ሊመጣ ይቅርና ከሃገርቤት ያሉትን በፍትህ እጦት እንደዚህ እያስመረረ ከሃገር ያስወጣል። ከዚህ በላይ ንቀት ምን አለ?

በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ የወገኑ ስቃይ አንገብግቦት አደባባይ የወጣው ሰላምዊ ህዝብ ላይ የመንግስት ፀጥታ አህይሎች የሃይል እርምጃ እየወስዱ መሆኑን ምንጮች ገለጹ። በባእዳን የጽጥታ ሃይሎች በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ጅዳ እና መካ በሚገኙ በመቶሺህ በሚቆጠሩ ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን አሳዛኝ ድርጊት በመቃወም አደባባይ የወጣው ህዝብ ላይ መንግስት እርምጃ እንዲወሰድ ተዕዛዝ መተላለፉ ድፍን ኢትዮጵያውያንን እያነጋገረ ነው ። ዛሬ ረፋዱ ላይ በገዛ ሃገራችን የጸጥታ ሃይሎች የተደበብደቡ የታሰሩ 
ንጹሃን እንዳሉ ምንጮች አክለው ገልጸዋል። 

ኢትዮጵያውያኑ ላይ እንደተፈጸመው አይነት ባይሆንም ቀደም ሲል የሳውዲ መንግስት በተለያዩ ህገወጥ፡ስራ ላይ ተሰማርተው በነበሩ የባንግላዲሽ ዜጎች ላይ ተመሳስይ ጥቃት ፈጾሞ እንደ ነበር የሚያስታወሱ ምንጮች በወቅቱ የዜጎቻቸውን ክብር ለማሰጠበቅ በጠቅላይ ሚንስትር ደረጃ የሚመራ ሎኡካን ቡድን ሳውዲ አረቢያ በመግባት ዜጎቹን ከስቃይ መታደግ መቻሉእና በክብር ሃገሪቷን ለቀው እንዲወጡ የሳውዲ መግስት ላይ ዲፕሎማሲያዊ ተጸኖ ማድረጋቸውን ያስታውሳሉ ።

ሰሞኑንን በክቡር አባሳደር ብረሃነ ገ/ክርስቶስ እየተመራ ሳውዲ አረቢያ ገባ የተባለው ሎኡክ ምን እየሰራ እንደሆነ ግራ የተጋቡ አንዳንድ ታዝቢዎች ዛሬ ኢትዮጵያውያን ላይ እየበረታ የመጣውን ገፍ ለማስቆም በመግስት በኩል እይተደረገ ያለው ጥረት አሳፋሪ መሆኑንን ገልጸዋል። የየተኛውም ሃገር መንግስት ለአንድ የሀገሩ ዜጋ ህይወት የሚሰጠውን ክብር እና ቦታ የሚያስታወሱ ወገኖች በቅርቡ የሃገራችን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ቃል አቀባይ ክቡር አንባሳደር ዲናሞ ሙፍቲህ በሳውዲ አረቢያ ያለው ሁኔታ የሚጋነን አለመሆኑን የሰጡት አስተያየት አብዛኛውን ወገኖቻችንን አስቆጥቷል።

ኢትዮጵያውያኑ ላለፉት ሁለት አመታት ሁለትዮሽ ስምምነት በሌለብት ወደ ሳውዲ አረቢያ በተለያዩ የግል ኤንጄሲዎች በኩል በመንግስት ህጋዊ ሽፋን ተስጥቶት ያለምንም የዚጎች ህይወት ዋስትና ኢትዮጵያውያኑ ዲፖርት ሲደረጉ በነበርበት ወቅት በቀን 1500 ያህል በወር እስከ 45 ሺህ ዜጎች ከኢትዮጵያ ወደ ሳውዲ አረቢያ ይጓጓዙ እንደነበር የሚገልጹ ወገኖች ዛሬ የህይወታቸው አደጋውስጥ የወደቁትን ወገኖች በዛው ልክ ወደ ሃገር ለመመለስ ግራ መጋባታቸው መግስት ለዚጋ ዴታ የሌለው መሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬ ለተቃውሞ አዲስ አበባ በወጣው ህዝብ ፖሊስ እርምጃ መወሰዱ የዚሁ አባባል አንዱ አካል እና ፍትሃዊነት የጎደለው ድጊት መሆኑንን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል። 

የሰልፉን መልዕክት ያልተረዳ የወያኔ ፌደራል ፖሊስ ወገኖቻችን በየበረሃው መንገላታታቸው ሳያንስ በአገሩ የነሱን ድምፅ ለማሰማት የወጣን ህዝብ እንደእባብ እየቀጠቀጡት መድረሻ አሳጡት። በወገኑ መደብደብና መገደል ድምፁን ሊያሰማ የወጣው ህዝብ ላይ ከመንግሥት ነኝ ባይ የማይጠበቅ ሰቆቃ ሲፈፀም ማየቱ ከዚህ በላይ የልብ ስብራት ውስጥ የሚከት ነገር የለም።

ዛሬ ማምሻውን ወያኔ እንደለመደው ያው "ሰልፉ ሌላ አላማ ነበረው!!" ብሎ ይወነጅላል በሽመልስ ከማል አንደበት:: ፖሊስ አሁንም ህዝቡን በማስፈራራት ላይ ነው ::ወሎ ሰፈር በሚገኘው ሳኡድኣረቢያ ኤምባሲ የተቃውሞ ድምጾች ለማሰማት የወጡ ዜጎች በፖሊስ ተደብድበዋል:: በርካቶች ታስረዋል:: ሰልፉም በፖሊስ ቆመጥ እና አላስፈላጊ እርምጃ ተበትኗል::


Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image

No comments: