በጎንደር መተማ አቅራቢያ ልዩ ስሙ ሸዲ እና ገንዳ ውሃ በሚባሉ ቦታዎች የፌደራል ፖሊስ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ በከፈተው ተኩስ አምስት ሲሞቱ ስድስት ክፉኛ ቆስለው ወደ ጎንደር ሆስፒታል መወሰዳቸውን የደረሰን ዜና ተቁሟል::
የግጭቱ መንስኤ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል አንድ የአካባቢውን ነዋሪ በህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ሳቢያ በተፈጠረ ግርግር ይገድለዋል:: የአካባቢው ነዋሪዎችም በሰላማዊ ሰልፍ ገዳዩ የፖሊስ አባል ለህግ እንዲቀርብላቸው ለመጠየቅ ሲወጡ: ሌሎች ማህበረሰባዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም አብረው ይዘው ወጡ:: ፌደራል ፖሊስም በወጣው ህዝብ ላይ ቶክስ በመክፈት አራት ተጨማሪ ሰዎችን ሲገድል ስድስት ክፉኛ ቆስለዋል::
የዚህ ዜና ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን የምናደርስ ይሆናል::
Violence in Metema - May 01, 2014 - 2 Violence in Metema - May 01, 2014 - 4 Violence in Metema - May 01, 2014 - 5 Violence in Metema - May 01, 2014 - 6 Violence in Metema - May 01, 2014 - 7
http://www.ethiotube.net