Wednesday, March 19, 2014

የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የሠማዕታት ወይስ የቅሱፋን?

የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የሠማዕታት ወይስ የቅሱፋን?

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
anole



ሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ በመቶዎች ሚሊዮኖች (አእላፋት) የሚቆጠር የሀገሪቱን ሀብት በማፍሰስ በመጠናቸው በሀገሪቱ ታይተው በማይታወቁ መልኩ በተለያዩ ሥፍራዎች “የሠማዕታት” የመታሰቢያ ሐውልት በማለት አስገንብቷል እያስገነባም ይገኛል፡፡ በምሳሌነት መቀሌ፣ ባሕርዳር፣ ናዝሬት፣ የተገነቡ የመታሰቢያ ሐውልቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ እነዚህ ሐውልቶች እንዲዘክሩ እንዲያስቡ የሚፈለገው ሕውሓት ኢሕአዴግ በትግል ላይ በነበረበት ወቅት “የተሠው” ታጋዮቻቸውን እንደሆነ ከየሐውልቶቹ ስር ያለው የማስገንዘብያ ጽሑፍ ይገልጻል፡፡
ለመሆኑ በእርግጥስ እነዚህ ጓዶች ሠማዕታት ናቸውን ከሆኑስ ሠማዕትነታቸው ለማንነው?
በበኩሌ እነኝህን ታጋዮች ሠማዕታት ብዬ ልዘክራቸው ሳስባቸው ክብር ልሰጣቸው የምችለው ኢትዮጵያንና ጥቅሞቿን በተመለከተ አሁን በሕይወት ካሉት የሕወሓት ኢሕአዴግ ባለሥልጣናትና ታጋዮች የተለየ ማለትም የኢትዮጵያንና የሕዝቧን ጥቅም፣ ክብር፣ ሉዓላዊነት የሚያስጠብቅ አቋም የነበራቸው እንደሆነ እርግጠኛ መሆን ከቻልኩ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ያለፉ ታጋዮች በሕይወት ቢኖሩ ኖሮ አሁን በሕይዎት ካሉት የተለዩ ሊሆኑ እንደማይችሉ አጠራጣሪ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ከሕወሓት ኢሕአዴግ ታሪክ እንደምንረዳው አሁን ሥልጣን ይዘው ያሉት የፈጸሙትና እይፈጸሙት ያለው ክህደት፣ የሠሩትና እይሠሩት ያለው በደል፣ ያደረጉትና እያደጉት ያለው ግፍ ሁሉ ለምሳሌም ኤርትራን ማስገንጠል፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ እንድነት በብሔር ብሔረሰቦች መብት ሽፋን እንዳልነበረ አድርጎ ማፈራረስ፣ የሀገሪቱን ታሪክ መካድና በመቶ ዓመታት ብቻ ማሳጠር፣ ነፍጠኛ ትምክህተኛ ወዘተ እያሉ በማሸማቀቅ የዜጎችን የሀገር ፍቅር ስሜት ማጥፋት፣ በተይ አማራውን ሕዝብ በጠላትነት በመፈረጅ እንዳያንሠራራ አድርጎ መሥበር ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ እነዚህን ድርጊቶች እዚያው በረሐ እያሉ ጀምሮ በዐቅድ ደረጃ ይዘውት የነበርና የሞቱ ታጋዮቻቸውም ይሄንን አምነውበት ለስኬታማነቱ ሲታገሉ የሞቱ በመሆናቸው በሕይዎት ቢኖሩ ኖሮ አሁን በሕይወት ካሉትና ሀገር ከሚያምሱት የተለዩ ሊሆኑ እንደማይችሉ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡
በመሆኑም የእነዚህ ሙታን ሠማዕትነታቸው ለሕወሓት ኢሕአዴጋዊያን እንጅ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ አይደለም ማለት ነው፡፡ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧስ ምንድን ናቸው ያልን እንደሆነ ቅሱፋን የሚለው ቃል ማንነታቸውን የሚገልጽ ይሆናል፡፡ ደማቸውም ለልማት ሳይሆን ለጥፋት የፈሰሰ በመሆኑ ደመ ከልብ ነው፡፡ ከዚህም አንጻር ለእነሱ መታሰቢያ ተብለው የቆሙት ሐውልቶች ዕድሜ ይህ “መንግሥት” እስካለ ጊዜ ድረስ ብቻ መሆኑ እርግጥ ነው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ሀገሪቱ እንደ አሁኑ ሁሉ ተገዳ ካልሆነ በስተቀር ወዳና ፈቅዳ ጠላቶቿን ልታስብ ልትዘክር የምትፈቅድበትና የምትገደድበት እንዳችም ምክናያት ስለሌለና ስለማይኖር፡፡
ሕወሓት/ኢህአዴግ አሁን ደግሞ ይግረማቹህ አለና ዐፄ ምኒልክ 2ኛ ግዛት በሚያስፋፋበት ወቅት አሉ በአሩሲ ዞን ሔጦሳ ወረዳ ላይ እንቢ አንገብርም የኢትዮጵያ አካል መሆን አንፈልግም ያሉ የኦሮሞ ተወላጆችን እጅና ጡት በመቁረጥ ግፍ ፈጽመውባቸዋል የሚል የፈጠራ ወሬ በመፈልሰፍ እነሱን ለማሰብ በሚል ከ 20 ሚሊዮን ብር በላይ በፈጀ በጀት መታሰቢያ ሐውልት አስገንብቶ እነሆ ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ወሬዎች የፈጠራ ወሬ ወይንም አንዷን እልፍ የማድረግ ያህል የተጋነነ መሆኑን ለማረጋገጥ የወያኔን ወያኔነት ማለትም ለዚህች ሀገርና ሕዝብ ያላቸውን ይጥፋት ዓላማና ግብ መለስ ብሎ ማሰቡ በቂ ነው፡፡ መቼም ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ዜጋ ሁሉ ሕወሓት ኢሕአዴግ ይሄንን ሥራ ሲሠራ ታሪክን ለመዘከር ካለው ቅን አመለካከት የመነጨ ነው ወይንም ለመልካም ነገር ነው ብሎ ያስባል ለማለት ይከብደኛል፡፡
ሕወሓት/ኢሕአዴግ ላሰበው ዓላማ ሲል ድርጊቱን ዘግናኝ ገጽታ እንዲኖረው ጡትና ብልት መቁረጥ የምትል ፈጠራ ጨመረባት እንጂ በእርግጥ እጅ የመቁረጥ ቅጣት በሀገራችን ታሪክ ወንጀለኞች የሚቀጡበት የቅጣት ዓይነት እንደነበር በግልጽ ይታወቃል፡፡ ፍትሐ ነገሥትቱም ይሄንን የደነገገ ነበር፡፡ ይህ ጡትና ብልት እጅ ከመቁረጥ ጋር አብሮ የተፈጸመው እዛው ኦሮሞዎች ውስጥ እርስ በእርስ በሃይማኖትና በሌሎች ጉዳዮች ሳቢያ በምሥራቁ ያሉቱ በምዕራቡ ያሉቱን በጨፈጨፉበት ወቅት ነበር፡፡ ይህ ታሪክ በኦሮሞዎቹ ዘንድ በሚገባ የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ ለዚህስ የመታሰቢያ ሐውልት ያቆሙ ይሆን? አይ አናቆምም ይሄንን ማንሣት ማስታወስም አንፈልግም ካሉ ለምን? ይህ ግፍ የተሞላበት የጭካኔ ድርጊት የተፈፀመው በአንድ ብሔረሰብ ውስጥ ስለሆነና ቁርሾንን ቂም በቀልን እንዳይፈጥር? ወንድማማችነትን እንዳያሻክር? አንድነትንና መግባባትን እንዳያፈርስ?ሰላምንና መረጋጋትን እንዳያናጋ? ውጤቱ ለብሔረሰቡ አልፎም ለሀገሪቱ ስለማይጠቅም ነው አይደል?
General_Hayelom_Monumentዐፄ ቴዎድሮስ ለሀገርና ለሐበሻ ክብር ሲሉ የሐበሻ ንጉሥ ተማረከ ከሚባል ብለው ራሳቸውን ካጠፋ በኋላ በዝብዝ ካሣ (ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ) ለእንግሊዝ በባንዳነት አድረው የእንግሊዝን ጦር እንዲደግፉና መንገድ እየመሩ እንዲወስዷቸው የላኳቸው ባንዳ ወገኖቻቸው በዐፄ ቴዎድሮስ አስከሬን ላይ ሌሊቱን ሁሉ ከበሯቸውን እየደለቁ አስከሬናቸውን ሊገልጹት የሚከብድ አረመኔያዊ ድርጊት እየፈጸሙ የዐፄ ቴዎድሮስንም ቤተሰቦች ሰቆቃ እየፈጸሙ በማስገደድ እንዲህ አድርጉ እያሉ እንዲህ እንዲህ ዓይነቶችን ግፍና ነውር ፈጽመዋል ብየ ብናገር ማንን ይጠቅማልይሄንን ግፍ የፈጸሙት አሕዮች ድርጊትንስ አሁን ያሉት ወገኖቻቸው ድርጊት ነው ብዬ ማሰብ መውሰድ ይገባል ወይ? ይቻላል ወይ? እነዚያ በፈጸሙት በደል ምንም የማያውቁት ምናልባትም ያንን ድርጊት የሚኮንኑ ልጆቻቸው ተጠያቂ መሆን አለባቸው ወይ? ይሄንን የዘቀጠ፣ የወረደ፣ የደነቆረ፣ የበከተ አስተሳሰብ ይዘን እንዴት ሆኖ ነው ለሀገርና ለሕዝብ ሰላምን ልማትን እድገትን ልናመጣ ልናረጋግጥ የምንችለው?
ወደ ርእሰ ጉዳዩ ስንመለስ ታሪክ መዝግቦ እንዳስቀመጠው ዐፄ ምኒልክ በእንደዚህ ዓይነት ምክንያት አልባ የጭካኔ ተግባር የሚታሙ ባይሆኑምና እጅግ ታጋሽ ይቅር ባይ አዛኝና ሩሕሩሕ እንደሆኑ ቢታወቅም በሌሎች ገፋፊነት እጅ በመቁረጥ የቀጧቸው ወገኖች ነበሩ፡፡ በ 1888ዓ.ም ሀገራችንን ቅኝ ለመያዝ ጠላት ሊወረን በተነሣ ወቅት አድዋ ላይ ይህን ሙከራውን እናት አባቶቻችን ድባቅ መተው ሲያመክኑበት ለተማረኩት የጣሊያን ምርኮኞች ፍርድ በተሰጠ ጊዜ በጣሊያን በኩል ከተሰለፉት ለሊቢያዉያን ዓረቦችና ለጣሊያኖች ምሕረት ሲደረግ ከጣሊያን ጋራ ተሰልፈው የገዛ ሀገራቸውንና መንግሥታቸውን ለውጉ የኤርትራ ተወላጆች ባንዳች ግን የትግሬ ገዥ በነበሩት በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ልጅ በራስ መንገሻ ዮሐንስ ወትዋችነት እጆቻቸውን እየተቆረጡ ወደ ሀገራቸው እንዲሸኙ በመወሰኑ ይሄው ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ይህ ድርጊትም አሁን ላለው ፖለቲካዊ (እምነት አሥተዳደራዊ) ገጽታ የራሱን ከባድ ጫና እንዲያሳድር አድርጓል፡፡ ከዚያ ይልቅ ሞት ተፈርቶባቸው ቢሆን ኖሮ እነዚያ እጀ ቆራጦቹ ባንዶች ሀገራቸው ገብተው ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚወራረስ መርዘኛ ስብከታቸውን የመስበክ ዕድል ባለገኙና ሀገሪቱንም ባልቆረጧት የአባቢውም ፖለቲካዊ ገጽታ እንዲህ የተበለሻሸ ባልሆነም ነበር፡፡
ከዐፄ ምኒልክ በፊትም ዐፄ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን መልሰው አንድ ለማድረግ ሲማስኑ በዘመቱበት ሀገር ሁሉ ለሁለተኛና ለሦስተኛ ጊዜ የሚከዷቸውን ከሀዲያን እጅ በመቁረጥ ይቀጡ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ወያኔ አሩሲ ሔጦሳ ላይ ለጥፋት ዓላማው ሲል በኦሮሞ ተላጆች ብቻ የተፈፀመ አስመስሎ እንደሚያወራው ተፈጽሞም እንኳን ቢሆን እጅ የመቁረጥ ቅጣት አዲስ እንግዳ ያልነበረና አስቀድሞ ሲፈጸም የነበረ የቅጣት ዓይነት ነበር፡፡
እዚህ ላይ እጅግ የሚገርመው ነገር ሕወሓት ኢሕአዴጎች ዐፄ ምኒልክ ከአሳዳጊያቸውና ከአስተማሪያቸው ከዐፄ ቴዎድሮስ የተቀበሉትን የተቻላቸውን ያህል ኢትዮጵያን እንደገና መልሶ አንድ የማድረግ ዓላማ አንግበው ሲዘምቱ ጡትና እጆቻቸውን ቆርጠውባቸዋል የሚሏቸውን ወገኖች ያቅጣት ሊደርስቦቸው የቻለው አንዋሐድም፣ የኢትዮጵያ ግዛት አካል አንሆንም፣ ለመንግሥት አንገብርም በማለታቸው እንደነበር ሳያፍሩ ይናገራሉ፡፡ ይባስ ብለውም መሥዋዕትነት የከፈሉ ወገኖች ሲሉ ይገልጿቸዋል፡፡ ይታያቹህ ኢትዮጵያ አንድ እንዳትሆን ሲታገሉ ተገቢ እርምጃ የተወሰደባቸው የሀገር ጠላቶች የአንድነት እንቅፋቶች ሆነው እያለ መሥዋዕትነት የከፈሉ ይሏቸዋል፡፡ አዬ ወያኔ! ይህ ምን ማለት ነው? የእነዚህ ወገኖች ዓላማ ትክክል ነበረ ማለት ነው? ኢትዮጵያ መመለስ አልነበረባትም ማለት ነው? በየመሳፍንቱና ባላባቱ ለሠላሳና ለአርባ እንደተበጣጠሰች መቅረት ነበረባት ማለት ነው? ለምን? እንዲህ መሆኗ ይሄንን ለሚፈልጉ ወገኖችም ቢሆን እንዴት አድርጎ ነው ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው? እነዚያ ሠላሳና አርባ ጎጦች እንዴት አድርገው ነው እንደሀገር እራሳቸውን ችለው መቆም የሚችሉት? ለነገሩ  እነዚህ የጥፋት ኃይሎች የዚህን ያህል ጠልቀው ማሳብ የሚችሉ አይደሉምና ይህን ጥያቄ ማንሣቴ ተገቢ አይደለም፡፡ ነገር ግን ይሄ አጥፊ ሐሳብ እንዴት ነው ዜጋ ከሚባሉት ሊፈልቅ የቻለው? ጤነኞችስ ናቸው ማለት ይቻላል ወይ? ካልሆኑስ በእብደታቸው በሚሠሩት ጥፋት ለአደጋ እንዳንዳረግ ሳንዘገይና ጉዳዩን መቀልበስ ከማንችልበት ደረጃ ሳንደርስ ምን ማድረግ ይኖርብናል?
በዚህ አጋጣሚ ሕወሓት ኢሕአዴግ ለሀገርና ለሕዝብ አንድነት የማይሠራ ይልቁንም ለማፍረስ የሚማስን መሆኑን ይሄን ሲያደርጉ ለነበሩ ጠላቶች ድጋፍ በመስጠት ስላረጋገጠልን ለግልጽነቱ ላመሰግነው እወዳለሁ፡፡ ምንም እንኳን ይህ የወያኔ ዓላማ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰወረ ባይሆንም ቅሉ፡፡
ወያኔ/ኢሕአዴግ በዚህ አሩሲ ዞን ሔጦሳ ወረዳ የገነባው የአኖሌን ሐውልት ሲገነባ ታሪክን ከመዘከር ኃላፊነት የመነጨ ተግባር እንዳልሆነ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ወያኔ ታሪክን በመዘከር ፍቅሩ የሚታማ አይደለምና እንበል ይሆን? የታሪክን ምልክት አሻራ እንኳን ቆሞ ማየት የማይፈልግ የታሪክ የማንነትን ጠላት፡፡ ሕወሓት ኢሕአዴግ በዚህ በገነባው ሐውልት ብዙ ሥራ ሊሠራበት አቅዷል፡፡ ከገነባው ሐውልት አብሮት ባለው ሙዚየም (ቤተመዘክር) አስቀድሞ ፈልስፎ ካስወራው በተጨማሪ ሌሎች በርካታ የፈጠራ ታሪኮች ጨምሮበት በሙዚየሙ የኦሮሞ ሕዝብ እነዚህን የልብ ወለድ ገጸ ባሕሪያትንና ዓላማቸውን ምሳሌ አርአያ እንዲያደርጉ የሚወተውቱ የኦሮሞን ሕዝብ ሊያሳስቱ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ያለውን አንድነትና ዝምድና ሊያራርቁ ሊሸርሽሩ ሊያሻክሩ የሚችሉ መርዘኛ የፈጠራ ወሬዎች የሚሰበክበት የጥፋት ማዕከል እንደሚያደርገው በቀላሉ መገመት ይቻላል፡፡mekele
ለመሆኑ እነዚህ ሕወሓት ኢሕአዴግ ሠማዕታት ሲል የጠራቸው የጠላት ጭፍሮች ኢትዮጵያ ከስምንት ዐሥርተ ዓመታት በላይ ቆይቶ በነበረውና ማዕከላዊ መንግሥቱን ሽባ አድርጎት በነበረው በትግሬው መስፍን በራስ ሥሑል ሚካኤል ሸር በተፈጠረው ዘመነ መሳፍንት ማዕከላዊው መንግሥት ግዛቱን መቆጣጠር ግብር መሰብሰብ አቅቶት የተፈጠረውን ክፍተት ተጠቅመው ኢትዮጵያን ለመቀራመት የፈለጉ እንግዶች ማዕከላዊው መንግሥት እንደገና ተጠናክሮ ግዛቱን ለመመለስ ወይም ለማጠናከር ፈልጎ ሲንቀሳቀስ አንቀላቀልም አንዋሐድም አንገብርም የማለት መብት ነበራቸው ወይ ብለን መጠየቅ ተገቢ ይሆናል፡፡
በእግጠኝነት ለመናገር ይህ አቋም የኦሮሞ ሕዝብ አቋም አይደለም አይሆንምም፡፡ የኦሮሞ ሕዝብ ብዙ ባለ አእምሮ ዜጎች ያሉት አስተዋይ የሕዝባችን አካል ነው፡፡ ይህንን ሕዝብ የጥፋት ኃይሎች ስሙን መጠቀሚያ በማድረጋቸው እጅግ ኃዘን ይሰማኛል፡፡ ስሙን መጠቀሚያ በማድረጋቸውም ብቻ አይደለም ጥቂቶቹን የብሔረሰቡን አባላት አሳስተው ከጎናቸው ማሰለፍ ስለቻሉም እንጅ፡፡ በመሆኑም እነዚህ የሳቱ የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላትን ወደ አእምሯቸው ለመመለስ ስል እውነቱን ለማስታወስ እገደዳለሁ፡፡
በታሪክ እንደሚተወቀው የኦሮሞ ሕዝብ ኢትየጵያ ውስጥ የገባው በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የግራኝ መሐመድ ወረራ የፈጠረላቸውን ምቹ ሁኔታ ተከትሎ ነው፡፡ ይህ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ ከ 15 ዓመታት በኋላ የግራኝ መሐመድ ወረራ ተቀልብሶ ግራኝና ሠራዊቱ ድል ተመቶ ዐፄ  ገላውዴዎስ ወደ ሀገራቸው በግራኝ ከመፈናቀላቸው በፊት የሟቹ አባታቸው መንግሥት መቀመጫ ወደ ነበረው ሸዋ ሲመለሱ ሀገሩ ሁሉ በእንግዶች ተይዞ አገኙት፡፡ የኦሮሞ አለቆችና ሽማግሎች (ልሂቃን) ሀገሬውን መስለው እንደ ሀገሬው ሁሉ እየገበሩ ለመኖር ቃል በመግባታቸው የሕዝባቸው ቁጥር የተመናመነባቸው ዐፄው ለማካካሻነት በማሰብ ለኦሮሞዎቹ ባሉበት ሆነው በሀገሪቱ እንዲኖሩ ፈቀዱ፡፡ ይህ ሥርዎ መንግሥት ግን ከዚያ ብዙ ሳይቆይ መቀመጫውን ከሸዋ ወደ ጎንደር አዛወረ፡፡ ከዚያ ወዲህ ባለው የሀገራችን ታሪክ የኦሮሞ ሕዝብ የራሱን ሚና መጫወት ሲጀምር ብዙ አልቆየም አቤቶዎችና አቤትሁኖች ነገሥታቱም ሚናቸውን ተጠቅመውበታል፡፡ ለምሳሌ ዐፄ ሠርፀ ድንግል የከዳችውን የባሕረ ነጋሽ (ባዕዳን ኤርትራ ያሏትን) ገዥ የይስሐቅንና ደጋፊውን ምጽዋን ወሮ ይዞ የነበረውን የቱርክን ጦር እንቲጮ ላይ በ 1571ዓ.ም ገጥመው በደመሰሱ ጊዜ የኦሮሞ ተዋጊዎች ዐቢይ ሚና ተጫውተዋል፡፡ አቤቶ ሱስንዮስ በካቶሊክነት የተጠረጠሩትን ዐፄ ያዕቆብን ወግተው ሥልጣን ሲጨብጡ ከሸዋ ይዘውት ከመጡት ሠራዊታቸው በተጨማሪ ከወለጋ ያመጧቸው የኦሮሞ ተዋጊዎች ሚና ታላቅ ነበር፡፡ ይሄን ውለታቸውን ለመክፈል ሲሉም ጎንደር የአንዳንድ አብያተክርስቲያናትን ርሥትና ጉልት እየነጠቁ ከወለጋ ላመጧቸው የኦሮሞ ተወላጆች እያከፋፈሉ አድለዋል፡፡ ይሄም ድርጊታቸው አስቀድሞ በጦርነት ጊዜ ጳጳሱ አቡነ ጴጥሮስ ባንድ ወታደራቸው በመገደላቸው ከፈጠረው ቅሬታ ጋር ተደምሮ ከቤተክህነት ጋር ለመጋጨትና በኋላም ሃይማኖታቸውን ቀይረው ሕዝቡንም ካቶሊክ እንዲሆን አስከማስገደድ አድርሷቸው ለሞት ላበቃቸው ችግር መንስኤ ሆኗል፡፡ ከዚህ በኋላም  የኦሮሞ ተወላጆች ለምሳሌ በኢዮአስ ዘመን መንግሥትን በተደጋጋሚ ያጠቁበት ዘመን ሁሉ ነበር፡፡ በጋብቻ ከነገሥታቱ ጋር ለመተሳሰርም የቻሉበት አጋጣሚ ሁሉ አለ፡፡
ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት ባለው የሀገራችን ታሪክ ግን የሌሎቹ ብሔረሰቦች በሀገሪቱ መኖር በአንድም በሌላም አጋጣሚዎች ተጠቅሶ ሲገኝ የኦሮሞዎቹ ግን ጨርሶ የለም፡፡ ይህም የሆነት ምክንያት በግልጽ መረዳት እንደሚቻለው በሀገሪቱ ስላልነበሩ ነው፡፡ የግራኝ ወረራ በፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ከገቡ በኋላ ግን በሀገሪቱ ፖለቲክዊ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ላይ ሚና ለመጫወት ሲበቁ እንደ እንግድነታቸው አልነበረም፡፡ በጣም ፈጥነው ነው ተሳትፎ ማድረግ የጀመሩት፡፡ እንግዲህ ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ይህ እንደሆነ የሀገራችን ታሪክ ያስረዳል፡፡ ያለው እውነት ይህ ሆኖ እያለ በኦሮሞ ሕዝብ ስም የሚነግዱት የጥፋት ኃይሎች ኦሮሚያን እንገነጥላለን ነጻ መንግሥት እንመሠርታለን ገለመሌ ሲሉ እራሳችንን ለትዝብት እንዳርጋለን ብለው ማሰብ አልነበረባቸውም? የቅርብ ጊዜ እንግዶች እንደሆኑ የግድ ማስታወስ ይኖርብናል እንዴ? የማንን ሀገር ነው የሚገነጥሉት ከዐፄ ገላውዴዎስ ጋር የገባችሁትን ውልና ግዴታ አስቡ እንጂ ጃል?
በመሆኑም ዐፄ ምንልክ ተፈጥሮ በነበረው ክፍተት የራቀውን ወይም የተረሳውን የሀገሪቱ ግዛት ለመመለስ ለማጠናከር ለማጽናት በሞከሩ ጊዜ ኦሮሞ ነን ከሚሉ ጥቂት የጥፋት ኃይሎች የገጠማቸው ተቃውሞና እንቅፋት ፈጽሞ የማይጠበቅና ክህደትም ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ካሉ ሀገሪቱን ለቀው ጥለው ወደ መጡበት የመመለስ መብታቸው የተበቀ ነበር፡፡ እነሱ ግን በእንግደነት ያደሩበትን ቤት ባለቤቶቹን አስወጥተን ካልወረስን አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ዐፄ ምኒልክ አደረጉት የሚባለው ነገር እውነት ቢሆንም እንኳን ይሄንን ከማድረግ ውጪ ምን አማራጭ ነበራቸው? ማሰብ የተሳነን ካልሆንን በስተቀር የዚህ እርምጃ ኢፍትሐዊነት ምኑ ላይ ነው? በየትኛው የዓለም ክፍልስ ያለ ሕዝብና ምንግሥትስ ነው እንዲህ ዓይነቱን ጉዳዩ ታግሶ እንዳሻችሁ ይሁንላችሁ ያለ? በእግጥ ለሌቦች ለቀማኞች ለዘራፊዎች የተወሰደው እርምጃ በየትኛውም መመዘኛ ፍትሐዊ ቢሆንም ለእነሱ ግን ኢፍትሐዊ ነው፡፡ በራሱ ላይ የሚፈርድ ጠላት የለምና፡፡ ነገር ግን ሌባና ዘራፊ እንዲህ አሉ ተብሎ ከቁም ነገር ልንጥፈው አይገባም፡፡ እንርሳቸው ማለቴ ግን አይደለም በፍጹም፡፡ በጣም በንቃትና በጥንቃቄ ልንከታተላቸው ይገባል፡፡ ሀገራችን እንደ ሀገር ሕዝባችንም እንደ ሕዝብ በአንድነቱ ጸንቶ መቀጠል ካለበት እንደነዚህ ያሉትን ጠላቶቹን ልንታገስና እንደፈቀዳችሁ ልንል ከቶውንም አንችልም አይገባምም፡፡ ዛሬም ቢሆን ወደፊት የሀገራችንንና የሕዝባችንን አንድነትና ሕልውና አስጠብቀን ልንቀጥል የምንችለው እኛም እንደአባቶቻችን ሁሉ ከውጭም ይሁን ከውስጥ የሚነሡብንን የሀገራችንንና የሕዝባችንን አንድነትና ሕልውና ጠላቶች ከተቻለ በማግባባት ካልተቻለ በአይቀጡ ቅጣት መደምሰስ ማጥፋት እስከቻልን ጊዜ ብቻና ብቻ ነው፡፡ ዋነኛ የመንግሥት ተግባርም ይሄው ነው ሀገርንና ሕዝብን ከውስጥና ከውጪ ጠላቶች መጠበቅ፡፡ መንግሥት ይሄንን ተግባሩን ግዴታውን በሚወጣበት ጊዜ ለምን የሚል አካል ካለ ይህ አካል ጠላትነቱን እያረጋገጠ ነውና ሳይቃጠል በቅጠል የማለት የዜግነት ግዴታ አለብን፡፡
ሕወሓት/ኢሕአዴግ ይሄንን የጥፋት ሥራ ሲሠራ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ ነውን?
ይህ የጥፋት ሥራ ሲሠራ ይሄ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደምም በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ አንድ ብሔረሰብን ቂም በቀል እንዲቋጥር ለማድረግ እኒሁን መከረኛ ዐፄ ምኒልክን እየጠቀሱ ፈጅተዋቹሀል የጅምላ መቃብሩም ይሄው እያሉ የአዲስ ለቅሶ ያህል ሙሾ በማስደርደር ሲያስለቅሷቸው ነበር፡፡ ስለድርጊቱ ታሪካዊ ዳራ ለማሳየት ያህል፡- እንደሚታወቀው ግብጾች አስቀድሞ ሀገራችንን የመውረር ሀሳቡና ፍላጎቱ ቢኖራቸውም እንኳ በዐፄ ቴዎድሮስ ጀግንነትና ኃይለኛነት ፈርተውና ተሰብስበው ሥጦታና ማባበያ እየሰጡ የቆዩትን ያህል ልክ ዐፄ ታዎድሮስ እንዳረፉላቸው የታሰረውን እግራቸውን በመፍታት በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ለ17 ጊዜ ያህል ሀገራችንን የመውረር ሙከራ በተለያየ አቅጣጫ ሲያደርጉ ቆይተው ነበር፡፡
ቱርክ ግብጽን ቅኝ ትገዛ በነበረበት ጊዜ ኢስማኤል የተባለው ቱርካዊ የግብጽ ንጉሥ የዓባይን የውኃ ምንጭነት ዋስትና ለማረጋገጥ ኢትዮጵያን አስከወዲያኛው ወሮ ለመያዝ አስቦ በሦስት አቅጣጫ በምጽዋ በታጁራ (ጅቡቲ) እና በዘይላ በኩል ሠራዊቱን ልኮ ነበር፡፡ የመጀመሪያው በምጽዋ በኩል የገባው በ 1866ዓ.ም ሁለት ሺህ የሚሆን ወታደር በርካታ መድፍና የነፍስ ወከፍ መሣሪያ የታጠቀውን የግብጽ ወራሪ ጦር ዐፄ ዮሐንስ ጉርአ ላይ ደምስሰዋል፡፡ በዚህ የተበሳጨው እስማኤል ኃይሉን እጅግ አጠናክሮ በምጽዋ በኩል ለሁለተኛ ጊዜ 25 ባታልዮን ጦር በላከ ጊዜም ዐፄ ዮሐንስ በሀገሪቱ በሙሉ የክተት አዋጅ በማስነገር በ 1868ዓ.ም አሁንም ጉርአ ላይ ደምሰውታል፡፡ በታጁራ (ጅቡቲ) በኩል የመጣውን የግብጽ ወራሪ ጦርንም አፋሮች አሰል ላይ ደምስሰውታል፡፡ በታች በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል የገባው የግብጽ ወራሪ ጦር ግን ሰተት ብሎ ገብቶ የሀገራቸው መንግሥት ከመዳከሙ ጋር በተያየዘ በራሳቸው ጊዜ ለቀው እስኪሄዱ ድረስ ከ 10-12 ለሚደርሱ ዓመታት ቆይቶ ነበር፡፡
በዚህ የቆይታው ጊዜ ከላይ ወያኔ የለቅሶ ሙሾ ካስወረዳቸው ወገኖቻችን ጋር የሃይማኖታቸው መመሳሰል ምክንያት ሆኗቸው ከግብጽ ጦር ጋር ተስማምተው ተዋሕደው ተዋልደው ኖረው ነበር፡፡ ዐፄ ምኒልክ የሀገሪቱን ግዛት እንደገና በሚያጠናክሩበት ጊዜ የራስ መኮነን ጦር ወደ ቦታው ሲዘምት እነዚህ ወገኖቻችን ይህ የግብጽ ግዛት ነው ግብጻዊያን ነን በማለት በእንቢተኝነት ጸንተው የቻሉትን ያህል የገዛ ሀገራቸውንና መንግሥታቸውን በመክዳት ተዋግተዋል፡፡ በዚህ ሁኔታ የተደመሰሱ የግብጽ ባንዶችን ነው እንግዲህ ወያኔ ዐፄ ምኒልክ ያስፈጃቸው ወገኖቻችሁ በማለት የጅምላ መቃብራቸው ነው እያለ በግድ ቁርሾና ቂም በቀል እንዲቋጥሩ ኢትዮጵያዊ ስሜታቸውን አጥፍተው ባንዳዊ ስሜትና አስተሳሰብ እንዲኖራቸው ሲወተውታቸው ልባቸውን ሲያወልቅው የነበረው፡፡ የወያኔ ነገር ግን አይገርማችሁም?
መልእክት በኦሮሞ ሕዝብ ስም እየነገዱ ላሉ የጥፋት ኃይሎችና ለሌሎችም፡-
ለሌሎቹም ማለቴ የሕወሓቶችም ችግር ተመሳሳይ በመሆኑ ነው፡፡ ከረጅሙ የሀገራችን ታሪክ የነበራቸውን ድርሻ አሳምረው ያውቃሉና ከባዕድነት ከሚመነጭ ስሜት ነው ለዚህች ሀገር ታሪክ ተቆርቋሪነት ያጡትና በጠላትነት እንዲሰለፉ ሀብታችን እንዳይሉ ያደርጋቸው፡፡ እናም ለእነዚሁ ወገኖቻችን ልለግሳቸው የምሻው ቢያደርጉትም የሚቅማቸው ነገር ቢኖር የታሪክን እውነታ ሸምጥጦ በመካድና ሐሰት በመተካት የሚያንጽ፣ የሚገነባ፣ የሚጠቅም፣ መሬት ላይ ጠብ የሚልን እሴት መፍጠር አይቻልም፡፡ የሚጸናን መሠረት ያለውን እሴትና ማንነት መገንባት የሚቻለው በትክክል መሬት ላይ ባለና በነበረ ተጨባጭ እውነታ ላይ ብቻ እንጂ በሌለና ባለነበረ ልብወለደ ቅዥትና የተረት ተረት ታሪክ አይደለም፡፡ ይህ ተግባር አሸዋ ላይ ቤትን እንደመሥራት ይቆጠራል፡፡ ነፋስ ሲነፍስ ጐርፍ ሲጎርፍ ተጠራርጎ እንደሚወሰደው፡፡ መሠረት የለውምና፡፡ የኦሮሞ ብሔረሰብ ወደ ኢትዮጵያ የገባው ከ 16ኛው መቶ ክፍለ ዘን በኋላ እንደሆነ ሲነገር ብዙዎቹ በጥፋት ኃይልነት የተሰለፉት የኦሮሞ ተወላጆች ሲከፉ ይስተዋለሉ፡፡
ቢሆንም ይሉና መሠረታችን እዚሁ ከምሥራቅ አፍሪካ ውጭ አይደለምና እንደ ባዕድ መቆጠር የለብንም ተወላጆችን ነን ይላሉ፡፡ ይሄ ባልከፋ ዓለም ያወቀውንና ፀሐይ የሞቀውን በሀገራችን አራቱም አቅጣጫዎች አሁንም ድረስ በዓይን የሚታዩ በእጅ የሚዳሰሱ ቅርሶችና መረጃዎች ያሏትን ኢትዮጵያንና ታሪኳን ዐፄ ምኒልክ ግዛት ለማጠናከር ካደረጉት ዘመቻ ነው የሚጀምረው ብሎ ማለት ግን ከከፍተኛ በራስ ያለመተማመነና የሚረብሽ የበታችነት የዝቅተኝነት ስሜት የሚመነጭ ቅዥት፣ እውነታን ለመቀበል ከማይችልና እጅግ ከሚቸገር ደካማ በሽተኛና የደነቆረ ስብእና፣ የራስ ያልሆነን ለመንጠቅ ለመዝረፍ ለመስረቅ ከሚመለጭ የቀማኛነት የሌብነት ርካሽና ወራዳ ግብር የመነጨ አስተሳሰብ ነው፡፡
ሀገሪቱ እንደተበተነች መቅረት ነበረባት ግዛቷ መመለስ አልነበረበትም ከሆነ ለማለት የተፈለገው የዋሀን መሆናቸውን ልነግራቸው እወዳለሁ ለሽዎች ዓመታት ይህችን ሀገር ለመገንባት ስንት መሥዋዕትነት እንደተከፈለባት ካለማወቅና ለዚህ ጽናት ጥረት ቁርጠኝነት ሥልጣኔ ክብርና ዋጋ መስጠት የሚችል በሳል ሰብአዊና ሞራላዊ አቅም ከማጣታቸው የተነሣ እንደሆነም እገምታለሁ፡፡ እሴቱ የማንም ይሁን በሞራል የተገነባ ሰብእና ያለው ሰብአዊነትም የሚሰማው ሰው ለዚህ እሴት ዋጋ ከመስጠት አይታቀብም፡፡ አሁን አሁን ላይ አንዳንድ የኦሮሞ “ምሁራን” የኦሮሞ ብሔረሰብ ከ16ኛው መቶ ክ/ን በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ነበረ በማለት አንዲትም ተጨባጭ መረጃ አይደለም ሊመስል የሚችል እንኳን የሌለው ልብ ወለድ ድርሰት እየደረሱ ያንንም እውነት ለማስመሰል የሚጥሩ ብቅ ብቅ እያሉ ነው፡፡ ከዘመን በፊት ኢትዮጵያዊ አሻራ ያላቸው ሆኖ ለመገኘት ያላቸውን ቅን ፍላጎት ብናደንቅም ማንነት ባልነበረና በሌለ ታሪክ ላይ አይመሠረትምና እናዝናለን፡፡
ባጠቃላይ ይህ ዓይነት የጥፋት አስተሳሰብ የመከኑና የታመሙ ዜጎች አስተሳሰብ ነው፡፡ ወደ ሥነ-ልቡና ሐኪም ዘንድ ጎራ ብለው ሕክምና እዲያገኙ እመክራለሁ፡፡ በነበረው በተጨባጩ ነገር ላይ ምንም ነገር ለመለወጥ በማይቻልበት ሁኔታ ከእውነታ ጋር መላተም መጋጨት እብደትን ያስከትላል፣ የውስጥ ሰላምን ያውካል ያሳጣል፣ ጤናን ይነሳል፡፡ ለዚህ መድኃኒቱ ያለውን እውነታ እንደ እውነታነቱ ሁሉ ተቀብሎ ያ እውነታ የሰጠውን ድርሻ ተቀብሎ እሱን አክብሮና አመስግኖ መያዝ መጠበቅ ማጣጣም ሰላምን ደኅንነትን ጤናን ደስታን ፍቅርን ይሰጣል ይፈጥራል፡፡ በሥነልቡና ሁከት መታወክ ሳያስፈልግ በነበረውና ባለው እውነታ ላይ ራስን መገንባት ማነጽ ማሳደግ ይቻላል ይሄን የሚከለከል ማንም የለም ለራሳችን ለውስጣችን ሰላም ስንል ከእውነታ ጋር አንጣላ አንላተም አንጋጭ ለኅሊናችን ተጠያቂነት ይኑረን እንደ ሰው ይሄን ማድረግ ካልቻልን ጤና አይኖረንም፡፡
በመጨረሻም፡- ዛሬ የታሪክና የሀገር ጠላቶች ፍጹም ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ ለቢጤዎቻቸው የመታሰቢያ ሐውልት ቢያቆሙም ነገ የኢትዮጵያና የሕዝቧ ቀን ሲወጣ አሩሲ ሔጦስ በተገነባው የአኖሌ የጥፋትና የክህደት ሐውልት ላይ በዚያው በአሩሲ አርባጉጉ አቦምሳና በደኖ ላይ ያለምንም ኃጢአታቸው አማራ በመኖናቸው ብቻ እንደ በደል ተቆጥሮባቸው በሕወሐት ኢሕአዴግ ዘመን በሚያሳዝን ሁኔታ ከሕፃናት እስከ አረጋዊያን አረመኔያዊ በሆነ ጭካኔ ለተጨፈጨፉት ወይም የዘር ማጥፋት ወንጀል ለተፈጸመባቸው ንጹሐን ዜጎች ትክክለኛውና እውነተኛው የሰማዕታት የመታሰቢያ ሐውልት ይቆማል፡፡ የጨለማ እድሜ ፀሐይ እስከትወጣ ድረሰ ነው፡፡ ምንም እንኳን ይህ የጥፋት ሐውልት ዓላማው በንጹሐን ኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ኢሰብአዊና አረመኔያዊ ግፍ በፈጠራና ልብወለድ ድርሰት ለማጣፋት ለማዳፈን ለማስረሳት ለመሸፈን ቢሆንም ይህ የዘር ማጥፋት ወንጀል የተፈጸመው በእኛው እድሜ በመሆኑና በትኩስ የትውስታ ርቀት ላይ ያለ ጉዳይ በመሆኑ የፈለጋቸውን ነገር ቢያደርጉ ከቶውንም ይሄንን ማድረግ እንደማይችሉ ላረጋግጥላቸው እወዳለሁ፡፡
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ከዚያ ይልቅ ግን ማለትም ጥፋትን ለመሸፈን ሲባል ወደ ሌላ ጥፋት ከመግባትና ለሀገርና ለትውልደ ሌላ የጥፋት ጥንስስ ከመጠንሰስ ትክክለኛውንና ጤነኛውን መንገድ በመጠቀም ለተፈጸመው ዘመንና ታሪክ የማይረሳው አረመኔያዊ ግፍ ፍጹም ከልብ በሆነ ጸጸት ሕዝብን ይቅርታ በመጠየቅ ልብን የማጽጃ ሳላምና መግባባትን ፍቅርን የመመስረቻ አማራጭ ቢጠቀሙ ለሥጋም ይሁን ለነፍስ ለእነርሱም ይሁን ለሀገር ብቸኛውና ጠቃሚው አማራጭ መሆኑን ላስገነዝባቸው ላመለክታቸው እወዳለሁ፡፡ ልባችሁ ቀና ካሰበና በሳል ከሆናችሁ ይሄንን እንዳታደርጉ የሚከለክላችሁ ምንም ማንም የለም፡፡ ይሀንን ማድረግ የምትችሉበት ወርቃማው ጊዜያችሁ ግን ዛሬ ነው ነገ የናንተ አይደለምና፡፡ ዛሬያችሁ ከለፈ ይሄም ዕድል አብሮ ያልፋል ዳግመኛ ልታገኙትም አትችሉም፡፡ ያኔ የሚኖራችሁ ዕድል የዘራችሁትን ማጨድ ብቻ ይሆናል፡፡ በእግጠኝነትም ትጸጸታላችሁ የደም እንባ ታነባላችሁ ነገር ግን የሚጠቅም እንባ አይሆንላችሁም፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ልቡናውን ይስጣችሁ አሜን፡፡ በሉ እንግዲህ ወገኖች ጭራቆቹ በዚህ ጽሑፍ ተቆጥተው ከበሉኝም ደኅና ሁኑ፡፡ ዘለዓለማዊ ክብር እንደሻማ ቀልጠው ይህችን ሀገር ከነጻነቷ ጋር ላቆዩልን ለአርበኞቹ እናት አባቶቻችን ይሁን!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ዕንቁ መጽሔት ቅጽ 6 ቁጥር113 መጋቢት 2006 ዓ.ም.
amsalugkidan@gmail.com
http://www.goolgule.com/

No comments: