Wednesday, November 4, 2015

ኢንጂነር ይልቃል ሞባይል ስልካቸው ባልታወቁ ሰዎች እጅ መግባቱን አስታወቁ


Hiber Radio Interview with Eng Yilkal Getnet
(ዘ-ሐበሻ) የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የሞባይል ስልካቸው ባልታወቁ ሰዎች እጅ መግባቱን እና ከዛሬ ጀምሮ በኢሜይል; በፌስቡክ እና በቴክስት በርሳቸው ስም የሚላክ ሁሉ የርሳቸው እንዳልሆነ አስታወቁ::
ስልካቸውን “ባልታወቁ ሰዎች እጅ ከመግባቱ” ውጭ ስም ጠርተው ተጠያቂ ያላደረጉት ኢንጂነሩ ያስተላለፉት መል ዕክት ነው::
ማሳሰቢያ!
የእጅ ስልክ (ሞባይሌ) ባልታወቁ ሰዎች እጅ ስለገባ ከዛሬ ጥቅምት 24/2008 ዓ.ም ጠዋት 2 ሰዓት ጀምሮ በፌስቡክ፣ በኢሜልና በሌሎችም አድራሻዎቼ የሚተላለፉ መልዕክቶች የእኔ አለመሆናቸውን ወዳጆቼ እንድትገነዘቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
Source: Zehabesha

No comments: