Saturday, November 21, 2015

ዛሬ ብአዴን የሚያደረገው ፌሽታ ብሄራዊ ዉርድት ነው - የሚሊዮኖች ድምጽ


"የብአዴን የምስረታ በአል በፌሽታ ሳይሆን ለህዝቡ ጥያቄ ምላሽ በመስጠት ይከበራል"
ይሄን የተናገሩት አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው። የብአዴን ሊቀመንበር።
ነገ ብአዴን 35ኛ በዓሉን በባህር ዳር ያከብራል። ለዚህ በዓል ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ እንደተደረገ በስፋት እየተዘገበ ነው።
በአዴን ሲቋቋም ኢሕዴን(የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) በሚል ከኢሕአፓ በወጡ ጥቂት ግለሰቦች ፣ በሕወሃት አዝማችነት የተመሰረተ ሲሆን ፣ ህወሃት ስልጣን ሲጨብጥ "ኢትዮጵያ" የሚል ስም ያለበት ደርጅት ማየት የማይፈልጉት እነ መለስ ዜናዊ በሰጡት ትእዛዝ "ኢሕዴን" ወደ "ብአዴን"(ብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) ተለወጠ። ድርጅቱን የሕወሃት አሽከር ሆኖ፣ ኤርትራዉያን የሆኑ እነ በረከት ስምኦንን መሪው አድርጎ፣ የአማራዉን ብሄረሰብ እወክላለሁ አለ። ለምለም የሰሜን ጎንደር መሬቶች ወደ ትግራይ ተደባለቁ። በደቡብ ጎንደር ምእራብ ጎጃም ቤነሻንጉል የሚል ክልል ተመሰረተ። በዚያ ከሕወሃት ጋር ግንኝነት ያላቸው፣ ገበሬዉ እየተፈናቀለ፣ ሰፋፊ የ እርሻ መሬቶች ተሰጣቸው። ብአዴን እንወክላለን ላሉት ህዝብ መቆም ሳይሆን፣ እንወክላለን ባሉት ህዝብ ላይ ተነሱበት። የሕወሃት ዱላ ሆነው ህዝቡን ገደሉት። አሰሩት፣ አሸበሩት፣ አሰቃዩት።
ብአዴን፣ እወክለዋለሁ ያለው ማህበረሰብ፣ በተለያዩ የአገሪቷ ግዛቶች "አገርህ አይደለም" እየተባለ ሲገደል፣ ሲፈናቀል ዝምታን መርጧል። ከሌሎች ክልሎች መፈናቀልና መገደል ፣ በቅርቡ ተገድለው፣ በጆንያ ተጠቅልለው ተቀበረው እንደተገቡት ወደ አሥራ ሁለት የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን፣ እድል ፈንታ እየሆነ ነው።
ብአዴን፣ እወክለዋለሁ ያለው ማህበረሰብ፣በተከይም በአሁኑ ሰዓት፣ በወሎና በሰሜን ምስራቅ ጎንደር ለክፍተኛ ረሃብና አደጋ ተጋልጧል። ሕጻናት እየሞቱ ነው። ገበሬዎች ተፈናቅለው ወደ ከተማ እየጎረፉ ነው።
ሕዝቡ በዚህ ችግር ላይ ሆኖ እያለ ግን፣ ብአዴኖች በአል ለማክበር፣ ዉስኪ ለመርጨት፣ ዳንኪራ ለመምታት፣ ወደ ሶስት መቶ ሚሊዮን ብር እያቃጠሉ ነው።
በርግጥ ይህ ፣ ብአዴንም ሆነው ጌታው ሕወሃት፣ ለሕዝብ ደንታ እንደሌላችዉ ያረጋገጡበት አንዱና ትልቁ ማሳያ ነው።
ያ ብቻ አይደለም። ነገ ብአዴን የሚያደርገው ፌሽታ በኢትዪጵያ ታሪክ ዉስጥ ትልቅ ጥቁር ነጥብ የሚጥል፣ ብሄራዊ ዉርድት ነው !!!! ዉርደት !!!! ዉርደት !!!! ዉርደት !!!!

No comments: