Sunday, September 6, 2015

አዲሱ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በይፋ ስራውን ጀመረ

አዲሱ የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት ዛሬ ጱግሜ 1/2007 ዓ.ም በይፋ ስራውን ጀምሯል፡፡ በዛሬው የአዲሱ ምክር ቤት ስብሰባ ነሃሴ 16ና 17/2007 ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ አስመራጭ የነበረው ኮሚቴ የብሔራዊ ምክር ቤትን፣ የኢዲትና ምርመራ ኮሚሽን አባላትን ውጤት ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በጠቅላላ ጉባኤው ምርጫ ከ1ኛ-50ኛ የተመረጡ አባላት እንደ ውጤታቸው 37ቱ ቋሚ እንዲሁም 13 ተለዋጭ አባላት ይፋ ሆነዋል፡፡ በተጨማሪም 5 የኦዲትና ምርመራ አባላትንም ይፋ አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ አዲስ የተመረጠው የኦዲትና ምርመራ የአዲሱን ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ አስመርጧል፡፡ ለሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢነት አቶ ይድነቃቸው ከበደ፣ አቶ አበበ አካሉና አቶ እስክንድር ጥላሁን የተወዳደሩ ሲሆን አቶ ይድነቃቸው ከበደ የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሆኖ ተመርጧል፡፡ በእስር ላይ የሚገኘው አቶ የሸዋስ አሰፋ ምክትል ሰብሳቢ ሆኖ ተመርጧል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ መስከረም 9/2008 ዓ.ም በሚያደርገው ሁለተኛ ስብሰባው የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት አዲሱን ካቢኔያቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

No comments: