Saturday, August 31, 2013

በሁለት ሰልፎች ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂው መንግሥት ነው ብሏል፡፡

በሁለት ሰልፎች ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂው መንግሥት ነው ብሏል፡፡ 


ማሳወቅ ባለብን ሰዓት አሳውቀናል፤ ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ሀላፊነቱን ይወስዳል- ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ሰማያዊ ፓርቲ ሳያስፈቅድ በሚያካሂደው ሰልፍ ለሚፈጠር ችግር ሀላፊነት ይወስዳል- አቶ ሽመልስ ከማል
የሰማያዊ ፓርቲ የነገው ሰልፍ ህገወጥ ነው - ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ
በነገው እለት ሰማያዊ ፓርቲና የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ የጠሩ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት፤ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ህገወጥ ነው ብሏል
ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚመለከተውን አካል አሳውቄአለሁ ያለው ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በፊት ማሳወቁን ገልፆ፤ በሁለት ሰልፎች ምክንያት ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂው መንግሥት ነው ብሏል፡፡
“ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉ አልተፈቀደለትም ያሉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል፤ ፓርቲው ይህንን ተላልፎ በሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ሀላፊነቱን ይወስዳል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚፈልግ አካል ሰልፉን ያደራጀውን ሰው፣የሰልፉን አላማ ይዘት፣ የሚወጣውን የሰው መጠን ግምት፣የሚካሄድበትን ጊዜና ቦታ መግለፅ እንዳለበት የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህን ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን ማስፈቀድም እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡ “ማሳወቅ ማለት ማስፈቀድ አይደለም” ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ካሳወቁም በኋላ ፍቃድ መጠየቅ የግድ ነው ብለዋል፡፡ “በበኩሌ የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፅህፈት ቤት እሁድ የአክራሪነትና የፅንፈኝነት እንቅስቃሴን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማስፈቀዱን አውቃለሁ” ያሉት አቶ ሽመልስ፤ በየትኛውም አገር በአንድ ቀንና በአንድ ቦታ ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄድ ስለማይፈቀድ፣ ፈቃድ ሰጭው አካል ይህን እያወቀ ለሰማያዊ ፓርቲ ፈቃድ ይሰጣል የሚል እምነት የለኝም ብለዋል፡፡ “በመሆኑም ሰልፉን የሚያካሂደው የተፈቀደለት አካል ነው” ብለዋል፡፡ አቶ ሽመልስ አክለውም፤ “በየትኛውም አገር ፍቃድ ሳይገኝ ሰላማዊ ሰልፍ አይወጣም፣ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው ብሎ ህግን በመናቅ የትም አይደረስም፣ይህን ተላልፎ ቢገኝ ለሚፈጠረው ችግር ፓርቲው ሀላፊነት እንደሚወስድ ራሱም ያውቀዋል” ብለዋል፡፡ “በአንድ ቀን ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች የማይፈቀዱት የተለያዩ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ፣ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠርና የፀጥታ ሀይሎች ወደተለያዩ ስራዎች ሊሰማሩ ስለሚችሉ የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት ነው” ሲሉ አቶ ሽመልስ ገልፀዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው ከሶስት ወር በፊት በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ያነሳቸው የህዝብ ጥያቄዎች ካልተመለሱ፣ ከሶስት ወር በኋላ ሁለተኛውን ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚጠራ በተደጋጋሚ መግለፃቸውን አስታውሰው፤ ይህም ጊዜ ነገ መሆኑንና አስፈላጊውን መስፈርት ማሟላታቸውን ተናግረዋል፡፡ “እኛ የማሳወቂያ ደብዳቤውን ያስገባነው ከሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፅ/ቤት በፊት ነው” ያሉት ኢ/ር ይልቃል፤ መንግስት በእኛ ላይ የተደረበውን ሰላማዊ ሰልፍ መሰረዝ እንዳለበት በመግለጫ ማሳወቃቸውንና ሰልፉን ከማካሄድ የሚገታቸው እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ “ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች ሲካሄዱ ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ሀላፊነቱን ይወስዳል” ሲሉም አሳስበዋል፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት የማሳወቂያ ደብዳቤውን ካስገቡ በኋላ ፅ/ቤቱ የስብሰባውን አላማ፣የትና መቼ እንደሚያካሂዱ፣የሰው ብዛት ምን ያህል እንደሚገመት ፓርቲው እንዲያሳውቀው በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት ለጥያቄዎቹ ሁሉ በደብዳቤ ምላሽ መስጠታቸውን ኢ/ር ይልቃል አስታውሰው፤ ነገር ግን ማሳወቂያ ፅ/ቤቱ በ48 ሰዓት ውስጥ ምላሽ ባለመስጠቱ እንደተፈቀደ ቆጥረን ዝግጅታችንን አጠናቀናል ብለዋል፡፡ በመሆኑም ከሰማያዊ ፓርቲ በኋላ መጥቶ ሰልፍ የሚያካሂደውን አካል በማስቆም፣ መንግስት ሀላፊነቱን መወጣት አለበት ብለዋል - የፓርቲው ሊቀመንበር፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ፤ “እኔ የማውቀው አንድ ሰላማዊ ሰልፍ ነው፤ የሰማያዊ ፓርቲ ህገወጥ ነው” በማለት መልሰዋል፡፡ ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ በዕለቱ ስለመካሄዱ ለፓርቲው አሳውቀው እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ማርቆስ፤ “ደብዳቤ ፅፈን ስንሰጣቸው የፓርቲው ሰዎች አንቀበልም በሚል ወርውረውት ሄደዋል” ብለዋል፡፡ ጉዳዩን አስመልክተን የጠየቅናቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል፤ “ፅ/ቤቱ በቃልም በደብዳቤም ያሳወቀን ነገር የለም፤ እኛም በነገው ዕለት ሰልፉን እናካሂዳለን” በማለት የፅ/ቤቱን ምላሽ አጣጥለውታል፡፡ ትናንትና ረፋድ ላይ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጠርቶ እንዳነጋገራቸው የገለፁት ኢ/ር ይልቃል፤ “ሰላማዊ ሰልፍ እንደምታካሂዱ የደረሰን መረጃ የለም” መባላቸውን ጠቁመው፤ ማሟላት ያለባቸውን መስፈርት እንዳሟሉ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ አሳውቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ በስልክ ያነጋገርናቸው ም/ኮሚሽነር ግርማ ካሳ፤ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ከሚመለከተው አካል ደብዳቤ እንዳልደረሳቸው ገልፀው፣ ሰማያዊ ፓርቲም ሰልፉ የተፈቀደበትን ማስረጃ ማቅረብ እንዳልቻለ ተናግረዋል፡፡ “በመሆኑም የነገው የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ህገ ወጥ ነው” ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡

በገቢዎችና ጉምሩክ ተጠርጣሪዎች ላይ 8 የክስ መዝገቦች ተከፈቱ

በገቢዎችና ጉምሩክ ተጠርጣሪዎች ላይ 8 የክስ መዝገቦች ተከፈቱ


አቶ መላኩ ፋንታ እና አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ በ3 መዝገቦች ተከሰዋል
ሶስት ተጠርጣሪዎች በነፃ ተለቀዋል
የፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ፤ ከ40 በላይ በሚሆኑ የገቢዎችና ጉምሩክ መስሪያ ቤት ባለስልጣናት እና የቅርንጫፉ ጽ/ቤት ሠራተኞች እንዲሁም ከባለስልጣናቱና ሠራተኞች ጋር ተመሳጥረው ከባድ የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በተባሉት ባለሀብቶች ላይ 8 የክስ መዝገቦች አደራጅቶ ከፈተ፡፡ በምርመራ ቀጠሮ ላይ የቆዩ 3 ተጠርጣሪዎች በነፃ ሲለቀቁ፣ ቀደም ሲል በዋለው ችሎት ምርመራቸው አልተጠናቀቀም ተብለው እንደገና ወደ ምርመራ ቀጠሮ የተመለሱት ተጠርጣሪዎች ባሉበት ሆነው እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2005 የምርመራ ስራው እንዲቀጥል ተብሏል፡፡
የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ የከፈታቸው 8 መዝገቦች በሚኒስትር ማዕረግ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፋንታ እና አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ በሶስት መዝገቦች ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
የተከሳሽ ጠበቆች በየደንበኞቻቸው ላይ የቀረበው የክስ ጭብጥ እንዲሰጣቸው የጠየቁ ቢሆንም ፍ/ቤቱ እስከቀጠሮ ባለው ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳችሁ ይደረጋል የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ተከሳሾችም በቀጣይ ቀጠሮ ሲቀርቡ የክሱ ጭብጥ እንደሚነበብላቸው ተገልጿል፡፡
የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን፤ የባለስልጣኑ ሠራተኞች በነበሩት በአቶ ንጉሴ ክብረት፣ አቶ ጌታቸው አሰፋ እና አቶ ምሣሌ ወ/ስላሴ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ በማጠናቀቁና ክስ እንደማይመሰረትባቸው በማረጋገጡ በነፃ እንዲለቀቁለት ጠይቆ፣ ፍ/ቤቱ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በሌላ በኩል በእነ አቶ ገ/ዋህድ መዝገብ ተካተው ምርመራ ሲካሄድባቸው የነበሩት አቶ ሙሌ ጋሻው በመሃንዲስነት ሲሰሩ በነበሩበት የኦሮሚያ ክልል ፍ/ቤት ጉዳያቸው እንዲታይ አቃቤ ህግ አመልክቷል፡፡ ተጠርጣሪውም ፈቃደኛነታቸውን በመግለጻቸው ፍ/ቤቱ የአቃቤ ህግን ጥያቄ ተቀብሎ ጉዳያቸው በክልሉ ፍ/ቤት እንዲታይ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል የኦዲት ምርመራው ባለመጠናቀቁ አቃቤ ህግ፣ በአቶ ተክለአብ ዘረአብሩክ፤ አቶ ምህረተአብ አብርሃ፣ አቶ በእግዚአብሔር አለበል እና አቶ ፍፁም ገ/ማርያም ላይ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የጠየቀ ቢሆንም ፍ/ቤቱ ከተጠየቀው ጊዜ ቀጠሮ 8 ቀን ብቻ በመፍቀድ ተጠርጣሪዎች ባሉበት ማረፊያ ቤት ቆይተው ለጳጉሜ 1 ቀን 2005 እንዲቀርቡ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የክስ መዝገብ የተከፈተባቸውን ተጠርጣሪዎች በ15ኛ ወንጀል ችሎት በኩል ክሳቸው እንዲታይ ለጥቅምት 11 እና 12 ቀን 2005 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ደ.ኮርያ ለስልጠና ተልከው የቀሩት ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ ሊያደርጉ ነው

ደ.ኮርያ ለስልጠና ተልከው የቀሩት ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ ሊያደርጉ ነው


ለስልጠና ወደ ደቡብ ኮርያ ተልከው እዚያው ጥገኝነት ጠይቀው የቀሩት 39 ኢትዮጵያውያን፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በመቃወም የፊታችን ረቡዕ በደቡብ ኮርያ ዋና ከተማ ሴኡል የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ፡፡
በአውቶ መካኒክ፣ በዌልዲንግና በኤሌክትሪሲቲ ሰልጥነው ተመልሰው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ መንግሥት የላካቸው እነዚህ ወጣቶች፤ በችግር ላይ እንደሆኑ ተደርጐ የተነገረው ሐሰት መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰብአዊ ክብራቸውና መብታቸው ተጠብቆላቸው በሴኡል እየኖሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ወጣቶቹ የፊታችን ረቡዕ “በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ይቁም”፣ “የሙስሊም ወንድሞቻችን ችግር እኛንም ይመለከተናል”፣ “መንግሥት ከሃይማኖት ጉዳዮች ላይ እጁን ያንሳ” የሚሉ ጉዳዮችን በማንሳት በሴኡል ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂዱ ከስፍራው በስልክ ገልፀዋል፡፡

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክርቤት አስቸኳይ ስብሰባ እያደረገ ነው

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክርቤት አስቸኳይ ስብሰባ እያደረገ ነው


የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ዛሬ ነሃሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም በፓርቲው ጽ/ቤት እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ አንድነት የጀመረውን የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ክንውኖች ገምግሟል፡፡ ምክርቤቱ ቀሪዎቹ የንቅናቄው መርሀ ግብሮች በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል የፓርቲው ስራ አስፈፃሚዎችና የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ከእስካሁኑ የላቀ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ ሰጥቷል፡፡ 33ቱ ፓርቲዎች የአንድነት ፓርቲን ህዝባዊ ንቅናቄ በመቀላቀል የመስከረም 5ቱን ሰላማዊ ሰልፍ በጋራ ለማካሄድ መወሰናቸውንም ምክር ቤቱ በደስታ ተቀብሏል፡፡
ብሔራዊ ምክርቤቱ ከሰአት በኋላ በሚያደርገው ስብሰባ በመጪው መስከረም ወር መጨረሻ ለሚደረገው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ የሚቀርቡ ሰነዶች ላይ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍም ይጠበቃል፡፡   DSC02371DSC02372DSC02373
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=5537#sthash.9oNYRzch.dpuf

የሃገር ቤት ፖለቲካ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገኛል።


የሃገር ቤት ፖለቲካ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገኛል።

ድምጻችን ይሰማ ሙስሊሙ ህዝብ ሰልፉን እንዲወጣ እና በርግጥ ድምጹን 

እንዲያሰማ እየጠየቁ ሲሆን ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ በእለቱ የጠራውን የራሱን 

የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያካሄድ አሳውቋል። አንድነት ፓርቲም በቅርቡ በአዲስ 

አበባ ከሚያካሂደው ሰልፍ በፊት የክልል ተቃውሞዎችን አጠናክሮ ሲቀጥል 

ውጥረት ውስጥ ያለው ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሞባይል ስልክ አገልግሎት 

እያጠፋ ነገሩን ለማብረድ እየሞከረ ነው። በተጨማሪም የሃገር ውስጥ ደህንነት 

ምክትል ሃላፊ የነበረው ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና በሚል በቁጥጥር ስር 

መዋሉ እየተሰማ ነው።

Ethiopia arrests top security official His arrest may be a prelude to the arrest of Azeb Mesfin, aka "Mother of Corruption"....... Ethiomedia

Ethiopia arrests top security official His arrest may be a prelude to the arrest of Azeb Mesfin, aka "Mother of Corruption"....... Ethiomedia

Her liutenants are
being rounded up for
corruption ... and it may
 be a matter of time
before she joins them at Kaliti
Ethiomedia,WASHINGTON, DC - A top Ethiopian security official has been arrested on corruption charges, a radio affiliated to the ruling party said on Friday.


Woldeselassie was a close friend of Gebrewahd Woldegiorgis, former deputy head of Revenue and Customs Authority, who has been in jail for months accused of corruption.

Observers say the arrest of the ranking security official could be a prelude to the arrest of Azeb, who is billed "Mother of All Corruption" in the country. "It is a matter of time before Azeb joins the ranks of the corrupt officials now behind bars," a source said.


Azeb was recently relieved of her post as CEO of EFFORT, the business oligarchy that has never been audited despite comprising major multi-billion-dollar companies such as Sur Construction, Mesfin Engineering, Almeda Textiles, and nearly two dozen business enterprises that have been the cash cow of the Meles-Azeb family and their inner-circle liutenants.

When Meles Zenawi was alive, Azeb was the most feared and powerful woman who at party meetings lashed out at current security chief Getachew Assefa for corruption and extravagant lifestyle. Azeb had insisted that Getachew should be fired and her favorite, Woldeselassie, promoted.

The once powerful and aggressive woman is slowly turning into the most vulnerable following the death of her husband in August last year. She now doesn't have any known official job. Critics have been blaming her for being corrupt on the one hand and incomptetent on the other that she can't work as CEO of EFFORT. Though not officially reported, there were anti-Azeb protests at a number of EFFORT-affiliated companies that called for her removal.

Azeb has been counting on the political clout of Abai Woldu, a TPLF politburo official who is at loggerheads with the Addis-Ababa-based Getachew Assefa and behind-the-scene powerful man, Debretsion Gebremichael, who is deputy chairman of TPLF and minister of Communication and Information Technology.


In reality, many consider Debretsion as Number One in the power hierarchy, and his side leading the anti-corruption campaign means the days of Azeb as the spoilt brat of the palace are over.

ለመጋራት ወይስ ለመደጋገፍ?! ......!

 ለመጋራት ወይስ ለመደጋገፍ?! ......!

"ደጋፊዎች ለማግኘት ትጥራለህ" የሚል ኣስተያየት ደርሶኛል።

እንደኔ ግን ማንም ለመደገፍ ይሁን የማንም ድጋፍ ለማግኘት ኣልተነሳሁም። ጓደኞቼ ከኔጋ ተመሳሳይ የሆነ የፖለቲካ ኣመለካከት ቢያራምዱ ደስታውን ኣልችለውም፤ የራሳቸው የሆነ የተለየ ኣቋም ቢኖራቸውም ኣደንቃቸዋለሁ። 

የማልፈልገው ኣካሄድ ቢኖር (መብታቸው እንደተጠበቀ ሁኖ) በጥቅም ተደልለው (ለሆዳችው ሲሉ) ለሌሎች የፖለቲካ ተዋንያን ህሊናቸው የማይፈቅደውን የፖለቲካ ድጋፍ በመስጠት ከነፃነት (በፍቃዳችው) ባርነትን የመረጡ ሰዎች መንገድ ነው።

እኔ ኣልደግፋቹሁም፤ ሃሳባችሁ ሲመቸኝ እጋራለሁ። ከናንተ የምጠብቀውም ይህ ነው። እኔ ከሰዎች ወይ ከፓርቲዎች መርህ የሚያጣብቅ ኣቋም የለኝም። የኔ ቃል ኪዳን ከእውነት ጋር የታሰረ ነው። ስለዚ ስለደጋፊዎች ኣልጨቅም። እንደውም የኔ ምክር ማንም ሰው ማንንም መደገፍ እንደሌለበት ነው።

እኔን ማመን (ወይ ኣለማመን) የለባችሁም። ኣያስፈልግም። የሚያስፈልገው እውነተኛውን ሓሳብ መለየት ላይ ነው። ኣንድ ሃሳብ መቀበል ያለብን ከራሳችን ኣስተሳሰብ ጋር ኣብሮ እንደሚሄድና ምክንያታዊ መሆኑ ስናረጋግጥ ነው።

በሌላ ኣባባል በዚ መንገድ ከሌሎች የምንወስደው ሃስብ የለም። ምክንያቱም የተቀበልነው ሃሳብ በውስጣችን (በራሳችን ኣስተሳሰብ ውስጥ) ኣግኝተነውልና።

ስለዚ ለምንነጋገረው ይሁን ለምንተገብረው ነገር በራሳችን (በግላችን) ሃላፊነት መውሰድ መቻል ኣለብን። እያንዳንዱ ሰው የራሱን የግል ውሳኔ ሲኖረውና የብዙዎቹ ተመሳሳይ ሲሆን ውጤታማ ለውጥ ይመጣል።

ብዙ የኢትዮዽያ ዜጎች በመሪዎቻቸው መከፋፈል ተስፋ ይቆርጣሉ። "ተስፋ ቆረጡ" ማለት የያንዳንዱ ግለሰብ ሃላፊነት ለመሪዎቹ ኣሳልፎ ሰጥቶ ነበር ማለት ነው። ይህ ስሕተት ነው። የግላችን ሃላፊነት በራሳችን ትከሻ መቀመጥ ይኖርበታል።

የምንፈልገው ነፃነት ከሆነ ሃላፊነታችን ለመሪዎቻችን ኣሳልፈን መስጠት ኣይገባም። ከሰጠናቸውማ ነፃ እየወጣን ሳይሆን ኣለቆችን (ጌቶችን) እየቀየርን ነው። ስለዚ ከመሪዎች ሃሳብን (ኣቋምን) መጋራት እንጂ ደጋፊ መሆን ኣያዋጣም። መሪዎቹ ኣንድ ነገር ሲሆኑ ኣላማው በናንተ መቀጠል ይኖርበታል።

ስለዚ የምንፃፃፈው ለመደጋገፍ ሳይሆን ሃሳብን ለመጋራት ነው። ሃሳባችን ዘላቂነት እንዲኖረው በእውነት የተመሰረተ መሆን ኣለበት።

ለህሊና ነፃነት ቅድሚያ እንስጥ።