Saturday, January 18, 2014

ሰበር ዜና!!!

መንግስት በነገው ጥምቀት በአል ላይ በሙስሊሙና 

ክርስትያኑ መካከል ግጭት ለመቀስቀስ ማሴሩን ምንጮች 

ገለፁ!!!


 ቅዳሜ ጥር 10/2006 መንግስት በነገው  የጥምቀት በአል በህዝበ ሙስሊሙ እና 

በክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ወንድምና እህቶቻችን መካከል ግጭት ለመፍጠር 

በማሴር ላይ እንደሚገኝ ምንጮች ገለፁ። ጥቃቱ ሊፈፀም የታሰበው በሐይቅ፣ 

በአርሲ፣ በአላባ ቁሊቱ እና በሌሎች የክልል ከተሞችም ላይ ሲሆን የሙስሊም 

ልብስ የለበሱ ግለሰቦች በጥምቀተ በአል ላይ ህዝበ ክርስትያኑ ላይ ጥቃት 

እንዲፈፅሙ በማድረግ መሆኑንና በተመሳሳይም መስጊዶች ላይ ተመሳሳይ ጥቃት 

ባልታወቁ ግለሰቦች እንዲፈጸም መታሰቡንም ምንጮች ጨምረው ገልፀዋል። 


መንግስት ለዚህ እኩይ አላማው እንዲረዳው በዛሬው ምሽት በኢቲቪ በሃይማኖቶች 


መካከል ግጭት ለመቀስቀስ ያለመ ዘጋቢ ፊልም ያቀረበ ሲሆን በነገው እለት 

ሊፈጠር የሚችለውን ግጭት ሰበብ በማድረግም ለፖለቲካዊ ፍጆታው ሊያውለው 

በማሴር ላይ ይገኛል። ይህን መሰል እኩይ ሴራ ከአንድ አገር አስተዳድራለሁ ከሚል 

መንግስት የማይጠበቅ እጅግ ሀላፊነት የጎደለው ተግባር መሆኑ እሙን ነው። 

በመሆኑም ህዝበ ሙስሊሙ ከማንኛውም ሁከት ፈጣሪ ተግባር በመቆጠብና 

መረጃውንም ላልሰሙ ወገኖቻችን ሁሉ በማዳረስ ሴራውን እንዲያከሽፍ፣ እንዲሁም 

የተለመደውን ከሌሎች ሃይማኖቶች ተከታይ ወገኖች ጋር በሰላምና በመከባበር 

የመኖር አኩሪ ልምዱን እንዲቀጥል ጥሪ እናቀርባለን! የመንግስትን ግጭት የመቀስቀስ 

ሴራ ተባብረን እናክሽፍ! 



ድምጻችን ይሰማ!

No comments: