Thursday, March 26, 2015

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የትብብሩን ሰልፍ እውቅና ነፈገ

• ‹‹ህገ መንግስታዊ መብታችን ከቦሊ ቦል ስፖርት በታች ሆኗል›› አቶ አዲሱ ጌታነህ
የባህርዳር ከተማ አስተዳደር እሁድ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም የ9ኙን ፓርቲዎች ትብብር በባህርዳር ከተማ ሊያደርገው የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና እንዳልሰጠውና ሰልፉን ማድረግ እንደማይቻል የትብብሩ አባልና የባህርዳር ሰልፍን አስተባባሪ ለሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል፡፡
አስተዳደሩ ለሰልፉ እውቅና እንዳልሰጠ የገለፀው ‹‹ሁለተኛውን አገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድር እያስተናገድን በመሆኑ›› እና ‹‹የህዳሴውን ግድብ የቦንድ ሳምንት በከተማችን በየማዕከሉ እየሰራን በመሆኑ›› ሰልፉን ለመጠበቅ የሚያስችል የፀጥታ ኃይል የለም በሚል ነው፡፡
የሰልፉ አስተባባሪዎች ወደ ከተማው ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በተደጋጋሚ ባቀኑበት ወቅት አመራሮቹ ሲጠፉ እንደቆዩ የገለፀው የሰልፉ አስተባባሪ አቶ አዲሱ ጌታነህ በመጨረሻ ሁለቱን ጥቃቅንና የፀጥታ ኃይል ለመላክ የማያግዱ ጉዳዮችን ጠቅሰው ሰልፉ እንዳይደረግ ወስነዋል ብሏል፡፡
የምርጫ ወቅት እንደመሆኑ ለሰላማዊ ሰልፉ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባ ነበር ያለው አቶ አዲሱ ‹‹በሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መካከል በሚካሄድ ስፖርት ይህ ነው የሚባል የፀጥታ ኃይል አያስፈልግም፡፡ ቦንድም ቢሆን በባንኮች በኩል ነው የሚሸጠው፡፡ ያም ሆኖ ባህርዳር የክልሉ ዋና ከተማ እንደመሆኗ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ፖሊስና መከላከያ አለ፡፡ በመሆኑም ምንም አይነት የፀጥታ ኃይል እጥረት የለም፡፡›› ሲል ውሳኔው ትክክል አለመሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
አቶ አዲሱ አክሎም ‹‹በእነዚህ ጥቃቅን ምክንያቶች ሰልፉን ሆን ብለው ማገድ ፈልገዋል፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ስፖርት ውድድር ተጠቅሶ ሰልፍ እንዳይደረግ መወሰኑ ህገ መንግስታዊ መብታችንን ከቦሊ ቦል ስፖርት በታች እንዳደረጉት ትልቅ ማሳያ ነው፡፡›› ብሎአል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ትብብሩ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ጊዜ ሰልፍ ለማድረግ ባቀደባቸው 14 ከተሞች የሚደረገው ሰልፍ እንደተጠበቀ ሲሆን የአዲስ አበባው ካሳንቺስ ከሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተነስቶ በአራት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ ሸዋ ዳቦና ግንፍሌ አድርጎ ወደ ቤልየር ሜዳ እንደሚያቀና ታውቋል፡፡

Exiled Ethiopian Journalist Betre Yacob: The Freedom Chat Transcripts

by Emily Durham| SAMPSONIA WAY
The Freedom Chat is a new video series by Sampsonia Way featuring interviews with journalists and other media workers facing censorship and repression in their home countries. In these Q&A’s, conducted via video chat, journalists talk with Sampsonia Way about press freedom, anti-free speech legislation, and exile.
In the Freedom Chat Transcripts, we share the entire interview with our subjects, including material not included in the video.
Editorial intern Emily Durham spoke with Betre Yacob
Betre Yacob
Ethiopia’s governmental corruption and persecution of journalists has been the subject of much international media coverage. Currently holding the 143rd position of 180 countries in the 2014 World Press Freedom Index published by Reporters without Borders, the Ethiopian government is cracking down on journalists and members of opposing political parties in anticipation of the upcoming May 2015 elections. Video communication software such as Skype has been outlawed, and the government monitors Internet communications such that online privacy is nonexistent. The condition of free speech in Ethiopia is dire, with journalists consistently being threatened, harassed, and imprisoned for their writings.
Editorial intern Emily Durham spoke with Betre Yacob, an Ethiopian journalist and the former president of the government-disbanded Ethiopian Journalists Forum. Betre Yacob is currently fleeing government persecution for publishing articles exposing human rights conditions and corruption. He is the author of Nipo, Nipo Tu, a collection of nonfiction short stories, biographies, and investigative articles about the untold socio-economical situations in developing countries like Ethiopia. The phrase “Nipo, Nipo Tu” is Swahili for “I’m here, I’m here, I’m alive,” and was chosen to convey the message, “Life is worth living everywhere, worth fighting for, despite everything.” In this interview, Betre Yacob explains the current conditions concerning freedom of expression in Ethiopia: conditions which have forced him into exile.
Can you describe the current free press conditions in Ethiopia?
It’s a very challenging time in Ethiopia. Journalism is now almost a crime. Writing, expressing your views, writing about the current political and economic situations of the country is all very challenging. It costs you a lot. Especially when you write about sensitive issues like human rights, or the economic situation or politics, you face harassment, you may face jail. Many journalists have left the country—I am only one of them. I suffered because of my profession, like other journalists. I have tasted the wrath of the Ethiopian government. Journalists are not assisted by legal frameworks—it’s not just what government officials are doing, but also what legal documents in Ethiopia are intentionally orchestrated to allow the region to act against journalists. So it is one of the most challenging times in Ethiopian history for press, media, and journalists. Almost the entire free press has collapsed.
What do you believe are the most heavily censored topics in Ethiopia currently and why do you think this is?
There are some issues which are more sensitive than others. The human rights situation of the country is one of these sensitive issues. Corruption is another sensitive issue. The human rights situation in Ethiopia is worsening every day. So many atrocities are committed throughout the country. For example, if you go to the eastern part of the Somali region, there are people who are subjected to harassment, arbitrary arrest, torture, and unlawful killing. These issues are risky for journalists. Many journalists can’t say whatever they want on such issues. You can’t speak out freely.
What were the conditions under which you were forced to leave Ethiopia?
Since 2012, I have been under government surveillance, and I have been experiencing severe pressure from the government. I was told I would be killed if I continued writing. I was harassed several times. I had formed an association with my friends and was working to change social problems and fight for my rights and freedoms. In 2014, I was listed as a terrorist by government-owned medias, including Addis Zemen Newsaper. It’s quite stressful when you’re accused by a giant government media as a terrorist. I was accused of working for outlawed groups, opposition groups, human rights organizations including Human Rights WatchCommittee to Protect JournalistsAmnesty International, and Article 19 to elicit violence in Ethiopia, to overthrow the current government. I was contacted directly from a higher government official that I would be jailed. I was trying to tolerate all these things. But finally, I was in Angola at a meeting organized by the African Union—I was there representing my association—and there was a serious crackdown on journalists and human rights activists, and my association was one of the targets. So, there were two reasons for my leaving: one, because of my activities as a journalist, because the government didn’t want me to keep writing and exposing the situation in Ethiopia, and two, because of my activities as president of an association working for the rights of journalists. When I was in Angola, the government was investigating all the leadership of the associations. My house was searched by policemen. It was clear that the government was waiting for me, so I didn’t have the option to go back to my country. It was my plan to go back, but I finally decided to leave my country.
Now, the crime is not only writing, but working for the rights of journalists. You cannot write, and you cannot ask for your rights to write. And everyone—not only journalists, but everyone—should have the right to form an association. The government should respect the rights of journalists, and should be responsible for protecting the rights of journalists.
Do you know any journalists who have been sent back to Ethiopia?
No, I don’t know any journalists extradited to Ethiopia, but there are journalists severely beaten and attacked in exile in neighboring countries by Ethiopian government security agents. There are, however, political activists and politicians who have been taken back to Ethiopia. For example, some months ago, one of the known political figures/human rights activists named Andargachew Tsige was arrested in Yemen by Yemeni security agents and extradited to Ethiopia. And there have been others taken back from Kenya, South Sudan, Somalia, and Djibouti. We can see the case of Mr. Okello Ochalla, who is now suffering in the notorious Maekalawi prison in Addis Ababa after being taken from south Sudan. In 2010 and 2012, many political refugees were reportedly returned to Ethiopia unlawfully. The situation of political refugees in neighboring countries is grave. These people are under the protection of the United Nations, but they are being taken back to Ethiopia to face execution.
What topics did you write about that caused problems?
Well, I write mostly on the human rights situation of the country. Of course, sometimes I write on other social aspects, but mostly I write about human rights, and this was one of the reasons for my flee. But it was my job in Ethiopia, journalism, to collect information and express my views.
The current Ethiopian constitution currently guarantees freedom of press, mass media, and expression without censorship. Are there specific laws that go against the constitution that restrict free speech even though it’s supposedly guaranteed?
Yeah, this is one of the complex issues in Ethiopia. Our constitution allows everyone the right to express his view. But the problem is that the country has other legal frameworks, like the Anti-Terrorism Law [2009 Anti-Terrorism Proclamation], which has been used against journalists who dissent. This particular law totally prevents journalists, writers, and bloggers from exercising their rights which have been granted by the constitution. Expressing your views can be seen as a terrorist act according to the Anti-Terrorism Law. The current constitution in Ethiopia has been paralyzed in recent years due to this type of intentionally orchestrated legislation.
Human rights advocate Professor Mesfin Woldemariam once divided the population of Ethiopia into “those in prison, those who were in prison, and those who will be in prison.” Can you respond to this in terms of the recentcrackdown on journalists and bloggers?
He’s right. The situation can be explained in his terms. As I told you, writing and expressing your views is now almost a crime in Ethiopia. Many journalists are now in jail. Many others are also waiting to be jailed, and one day they will join their colleagues. And then sometimes they self-censor. You can’t say whatever you want, whatever comes to your mind. You can’t speak out freely. People operating as journalists and writers, writing and working in Ethiopia, are not exercising the provision for self-censorship. This is the bitter reality in Ethiopia. I tried to change this reality by establishing an association with my colleagues.
Have you ever censored yourself in your own writing?
Yes, yes. It’s sometimes very challenging to figure out what you are censoring. Because you are always in the midst of government pressure, when you write sometimes you try to take sensitive issues out unintentionally. So yes, there have been some times when I’ve self-censored. I tried many times not to do this. But I remember some occasions I intentionally censored myself. I remember when I nixed some issues from my list; I didn’t touch them at all. I was afraid of touching those issues because I knew exactly what they would do in response.
Do you write about any of those issues now that you’re not in Ethiopia?
Well, now I am abroad, but my current situation is not very safe. Still I am at risk in the place where I’m living. The Ethiopian government secret agents and officials are still operating here. For the time, I’m not writing anything, but when I get to safe places, I will keep writing on those issues.
What branch of the government is responsible for enforcing censorship? Who are the censors and how do they work?
Almost all the government bodies are working in collaboration to silence journalists, bloggers, and writers, but I can mention one particular example. The Ethiopian Communication Affairs Office is one of the biggest organizations serving the Ethiopian government to silence journalists. This organization monitors what newspapers and magazines are talking about, all the basic issues in publications and other contents which are distributed online. Every time there is a sensitive issue, they always respond. They communicate with the security apparatus of the regime, they harass you, and anytime they want, they arrest you. Of course there is also one section of the government which is called the INSA [Information Network Security Agency], which monitors the online activities of Ethiopians. This organization is very good with the current technologies, and they are working to identify who is doing what, where. They know everything you are publishing, where you are publishing, and all your other online private communications. But this government organizations is really working in collaboration with other government organizations to control and manage the views and opinions circulating in Ethiopia.
There have been several allegations recently that some high-profile human rights organizations such as the Ethiopian National Journalists Union and the National Election Board of Ethiopia are actually just fronts for the ruling government which wishes to oppress human rights in Ethiopia. Can you respond to this?
Yes, I have seen it practically. For example, we established a journalists’ association with almost forty journalists in order to work for the rights of journalists and media personnel. But one of the challenges came from journalists’ associations operating in the name of journalists. These associations were acting in cooperation with government officials in order to stop us from implementing our plans. So yes, there are organizations and associations which were established to promote freedom and the rights of people, but practically are working for the government. Some of these organizations are journalists’ associations. At this time, there are journalists’ associations, but as you know journalists are fleeing the country, and many others have been jailed. And these associations aren’t saying anything; instead they are justifying the government crackdown. In the case of our association, these associations were even calling for action against us, trying to stop us from struggling for the rights of journalists and press freedom. There are frequent raids by these associations, and the government allows it. It just shows that there are human rights organizations operating in Ethiopia, but when we go deeper we see that, practically, they are working for the government.
What are the biggest problems you’ve faced?
As I told you, there are frequent harassments. I was accused of being a terrorist by different government-owned medias, and I was told that they would kill me unless I stopped my activities. And so I was living under frustration, I was asking myself what would be my destiny… My private life was really sad. My relationships with my wife, my family, my friends were not good because of such frustration. So I eventually fled.
Are you concerned that the Ethiopian government is still monitoring your activities now?
Yes, of course. I am still under government surveillance. After I left the country, security officials were asking about my whereabouts and related information. I am now talking to you after having some discussions with my colleagues about our deteriorating security situations. Some days ago an article was published by pro-government media, and I’m sure that it was written by government officials. It says that I have to be arrested and extradited to Ethiopia to be convicted. The article says this clearly. In the past few weeks, a report and a video were published by Human Rights Watch. There was also a program aired by theBBC that features me and my colleagues. And I think the government is disappointed by these activities. But I didn’t do anything wrong. I just tried to illustrate what is actually happening in Ethiopia.
Do you have any last thoughts to share?
Yes, I do have to say something very important. You now understand the problem faced by journalists is not only getting harassed, jailed, and tortured, but also the deprivation of so many rights established by the constitution. We don’t even have the right to get together and establish an association. I want to say that the Western governments should look into this problem and address it. There should be some immediate and practical action from the West. They are promoting democracy around the world, they are working for a world where the rule of law is guaranteed. So if they are truly concerned about democracy and about the rights of people, about the rights of journalists, about freedom, then they should contribute to fix what is happening in Ethiopia. It was not my wish to leave my country. I want to be with my family, I want to do my job freely. I want to have a stronger association which works for my rights and the rights of all writers and journalists, and I want to see peace in Ethiopia.

Wednesday, March 25, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ለ8ኛ ጊዜ ተመለሰ

• ኢብኮና የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት መልሰዋል
• ‹‹አማራጫችን እንዳናቀርብ እየተከለከልን ነው›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አናስተላልፍም›› ብለው መመለሳቸውን ድርጅቶቹ ለፓርቲው በላኳቸው ደብዳቤዎች ገልጸዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ መጋቢት 16/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የብሔራዊ ራዲዮ በአማርኛ ስርጭት የሚተላለፍ ‹‹መንግስታዊ አወቃቀር›› የሚል የቅስቀሳ መልዕክት ልኮ የነበር ሲሆን ባለፉት 24 አመታት ተግባራዊ የሆነው የጎሳ ፌደራሊዝም ለግጭት መንስኤ መሆኑን በመረጃ ዘርዝሮ ማቅረቡን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ይሁንና ኢብኮ ይህን የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹በተለያዩ ጊዜያት በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ተከሰቱ ያሉትን ግጭቶች በመዘርዘር በህዝቦች መካከል ሌላ ግጭት እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ የሚያደርጉና ግጭት የሚያራግቡ፣ አንዱን ብሔር ከሌላ ብሔር የሚያገጩ ናቸው፡፡›› በሚል እንደማያስተላልፍ ገልጾአል፡፡ ከዚህም ባሻገር በመልዕክቶቹ ውስጥ ‹የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት›፣ እንዲሁም ‹የህወሓት/ኢህአዴግ ስርዓት› የሚለው አገላለጽ የፓርቲውን ህጋዊ መጠሪያ የማይወክል በመሆኑ›› በሚል እንደማያስተላልፍ ገልጾአል፡፡
በሌላ በኩል እነዚህ ግጭቶች በአሁኑ ወቅትም የቀጠሉና የጎሳ ፌደራሊዝሙ እስካለ ድረስ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍሉ መሆናቸውን የገለጸው የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ መልዕክቶቹ ከፓርቲው ማንፌስቶ የወጡ፣ ኢብኮ እንዳለው ለግጭት ሳይሆን ከግጭቶቹ መማር እንዲቻልና አሁን ያለው የጎሳ ፌደራሊዝም ከተስተካከለ ችግሮቹ እልባት እንደሚያገኙ በሚያሳይ መልኩ የተላለፈ መልዕክት ነው ብሎአል፡፡ ‹‹እኛ ያቀረብነው አማራጫችን ነው፡፡ አማራጫችን ስናቀርብ ደግሞ የጎሳ ፌደራሊዝም የፈጠረውም ቀውስም በማሳያነት ማቅረብ አለብን፡፡ ይህን እውነታ የአገር ውስጥና የውጭ ተቋማት ዘግበውታል፡፡ አብዛኛዎቹ መንግስትም ያመነባቸው ናቸው፡፡ ነገር ግን ስርዓቱ የሰራቸው ጥፋቶች ይፋ አውጥተን እንዳናቀርብ ስለተፈለገ መልዕክቱን መልሰውታል፡፡ በግልጽ አማራጫችን እንዳናቀርብ ተከልክለናል›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በተመሳሳይ የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹ከሀገሪቱ ሰንደቅ አላማ ጋር የሚጻረር፣ ብሔር ብሄረሰቦችን ወደ አላስፈላጊ ግጭት እንዲያመሩ የሚገፋፋ፣ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን ስም የሚያጎድፍ ይዘት የተካተተባቸው›› ናቸው በሚል መልሷል፡፡ ይህ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ሲመለስ ለ8ኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡

ትጥቅ ትግል ፣ ሰላማዊ ትግል ፣ ሁለገብ ትግል (ዮናታን ተስፋዬ ረጋሳ)


11075125_351890231682989_1605144358791622863_n

(አቶ ዮናታን ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ናቸው። ይህ ጽሁፍም ፓርቲን ወክለው ሳይሆን ራሳቸውን ወክለው የጻፉት ነው)
ወቅታዊ አጀንዳ እና በቁንፅል የሚተው ባይሆንኝ ነው – በትግስት አንቡልኝ
ጭቆና ሲበዛ ሰዎች ብዙ መንገድን ተጠቅመው መታገል ይሻሉ፡፡ የጭቆናውን ቀንበር ለመስበር ጨቋኙን ከመግደል አንስቶ ራስን እስከማቃጠል ድረስ የሚደርሱ በርካታ መንገዶችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡ ከአገዛዝ ሰንሰለት ራስን ነፃ ለማድረግ ብዙዎች ተጨንቀው ማሰብም አይፈልጉም፡፡ በቃ ገዢውን ወዲያ አሽቀንጥሮ ጥሎ ነፃ መሆን (end of the story end of the oppression)! በተፈጥሮ ነፃ ሆኖ የተፈጠረ ሰው በሂደት እጅግ በተወሳሰበ የህይወት መስተጋብር ውስጥ ቢኖርም የጭቆናው ለከት ሲያልፍ ግን ቀስቃሽ ሳያሻው እንደቡድንም ይሁን በግል በነሲብ ወደ ነፃነት ትግል መግባቱ አይቀርም፡፡ ነፃነት ከብዙ ምክንያታዊነትም በላይ የስሜት ሀይሉ ከፍተኛ ገፊ በመሆኑ ለነፃነት የሚደረገውም እንቅስቃሴ በራሱ ድንገታዊነት ይበዛዋል፡፡ ‘መቼ’ እና ‘እንዴት’ን አያጠይቅም፤ ‘ለምን’ የሚለው ብቻ በቂው ነው፡፡
እንግዲህ እዚህ ጋር ነው የነፃነት ትግል መሪዎች ሚና ወሳኝ የሚሆነው፡፡ ጭቆናን ከምክንያታዊነት በላይ በስሜቱ ተፀይፎ ነፃነቱን ሊቀዳጅ የተነሳን ሰው መንገዱን ማመላከት የመሪዎቹ ሚና ነው፡፡ መሪው የትግሉን ‘እንዴትነት’ ‘መቼ’ ምን መደረግ እንዳለበት አፍታቶ ማሳየት እና እምቅ የሆነውን የነፃነት ፍላጎት ሀይል በተጠናና በተገቢው ቦታ ጥቅም ላይ እንዲውል ማስቻል፤ በዚህም አኳኋን ታጋዮችን አስተባብሮ መምራት አለበት፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም የነፃነት ትግል መሪ ከስሜት በላይ እጅግ ምክንያታዊ እና በአስቸጋሪ ሁናቴዎች ውስጥም ለታለመው ግብ ሲባል በርካታ ፈታኝ ውሳኔዎችንም እንዲያሳልፍ ይጠበቅበታል፡፡
የዛሬን መጨቆን ሳይሆን የነገን የተጨበጠ ውጤት ቀድሞ ማለም ለዛም የሚከፈለውን መስዋእትነት ሁሉ መክፈል ግዴታው ነው፡፡ ከተራ ውሳኔ አንስቶ በሰዎች ህልውና ላይ እስከመወሰን የሚያደርስ ጠንካራ የዲሲፕሊን ሰው የመሆን ኃላፊነቱ የትግሉ መሪ ላይ ይወድቃል፡፡ ከሁሉም በላይ ግን ሂደቱ ከየት ተነስቶ የት እንደሚደርስ በጠራ ሁናቴ የሚያልም፤ ከግቡም ለመድረስ የቆረጠ፤ ተግባራዊ እና ለዛም ሁነኛ መላ ቀያሽ ብልሃተኛ መሪ ትግሉን ከጫፍ ለማድረስ ይቻለዋል፡፡
ትግል ተፈጥሯዊ ነው – በብልሃት ማስተባበር እና መምራት ደግሞ ትግልን ከፍሬ የሚያደርሱ ነገሮች ናቸው፡፡ ከዚህ ተነስተን በኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚካሄዱት የነፃነት ትግሎች እንፈትሽ፡፡ አዋጪነታቸውንና ኪሳራቸውን እንመዝን፡፡
NOTHING PERSONAL NOR DESTRUCTIVE!
ትጥቅ ትግል በኢትዮጵያ?
———————-
* በ21ኛው ክ/ዘመን የትጥቅ ትግል አለማቀፋዊ አንደምታው እጅግ የተወሳሰበና ከፍተኛ የሰው እና የሉዓላዊነት ዋጋ የሚያስከፍል ነው፡፡ ለነፃነት እሞታለሁ ብሎ የወጣን ሰው አስተባብረህ ከምታስጣጥቀው መሳሪያ ጀምሮ የተለያዩ ሎጀስቲክና ዲፕሎማሲያዊ ድጋፎችን ማግኘት ግድ ይላል (ከመጋረጃ ጀርባ ያለውን የዓለም ሴራ ቀመስ ፖለቲካ ትተን)፡፡ እነዚህን ድጋፎች ለማግኘት ደግሞ በዓለም ላይ ከሚገኙ ታላላቅ መንግስታት ጀምሮ ገዢ መሬት ከሚሰጡህ አካላት ጋር በበርካታ ጉዳዮች ላይ ውል መፈፀሙ አይቀርም፡፡
ህወሃት ትጥቅ ትግሉን ድል አድረጎ ስልጣኑን ለመቆናጠጥ በሀገር እና በህዝብ ላይ እስከመደራደር ደርሷል፡፡ ለትጥቅ ትግሉ ስኬት ሲባልም ብዙ ታሪካዊ ስህተቶችም መፈፀማቸው ያልሻረ ቁስል ነው፡፡
በዚህ ዘመን ደግሞ በትጥቅ ትግል ኢህአዲግን ከስልጣን ማውረድ ከዓለም ነባራዊ ስርዓት አንፃር እጅግ አስቸጋሪ እና በአደጋ የተሞላ ነው (at this point there is no near-safe deal)፡፡ ስለዚህ ጥያቄው አህአዴግን ለማስወገድ ከተለያዩ ሀይሎች ጋር የሚደረጉት ስምምነቶች በእውነት ሚዛን ይደፋሉ ወይ? የሚፈፀሙት ስምምነቶች ህወሓት (ሊያውም በዘመነ ጦርነት) ካስከፈለን ዋጋ ምን ያህል ቢሻሉ፤ ምን ያህልስ የህዝባችንን እና የሀገራችንን ጥቅም ያስቀደሙ ወይም ከግምት አስገብተው የተፈፀሙ/ሊፈፀሙ ያሉ ናቸው? እነዚህ እና መሰል ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ እስካላገኙ ድረስ በዚህ ዘመን የሚደረገው የትጥቅ ትግል ለኢትዮጵያ የሚኖረው ፋይዳ ‘ከድጡ ወደማጡ’ ከመሆን ያለፈ አይሆንም!
* ከዚሁ ጋር በተዛመደ የኢትዮጵያ ታጣቂ ሀይሎች የመረጡት ገዢ መሬት የሙግቱ ዋና ማጠንጠኛ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ የሻቢያ ግዛት ኤርትራ፡፡ እዚህ ላይ ስለ ሻቢያ እና ወያኔ ፍቅርና ጠብ – አንድነት እና ልዩነት አሁን ስላላቸው ለክፉም ለደጉም የእርስ በእርስ መጠባበቅ ማውራቱ ‘አውቆ የተኛን . . .’ ካልሆነ በስተቀር ለማንም ምስጢር አይደለም፡፡ ምንአልባትም እነዚህ ሁለት ሀይሎች በኢትዮጵያም ይሁን በቀጠናው ጉዳይ ላይ የራሳቸው ቁማር እየተጫወቱ ስልጣናቸውን ለማስቀጠል ምንም ሊያደርጉ እንደሚችሉም ለሁሉም ሰው ግልፅ ነው፡፡
ይህን ካልን ዘንዳ ኢትዮጵያ ውስጥ በትጥቅ ትግል ለውጥ እናመጣለን የሚሉ ሃይሎች ከሻቢያ ጋር በምን መልኩ ሰምምነት አካሂደው ገዢ መሬት አገኙ? በዚህ ትግል ውስጥ የሻቢያ ጥቅም ምንድን ነው? በየትኛው ስሌት የኢትዮጵያ ታጣቂ ሀይሎች ከሻቢያ ድጋፍ አግኝተው የኢትዮጵያን ጥቅም ያስጠብቃሉ? (በቀደም ለት የኤርትራው ፕሬዘዳንት ስለኤርትራ እና ኢትዮጵያ ስላለፈውና መሆን ስላለበት ሲያብራሩ እነዚህ ጥያቄዎች ይበልጡኑ አወዛጋቢና በትጥቅ ትግሉ የተሰማሩ ሀይሎች ግልፅ ሊያደርጓቸው እንደሚገቡም ጭምር ተገንዝቤያለሁ!)
ስለሆነም እነዚህ መሰረታዊ ነጥቦች ምላሽ ባላገኙበት ሁናቴ ኢትዮጵያ ልጆቿን ዳግም ወደ እርስ በእርስ ጦርነት የምትከትበት አሳማኝ ምክንያት አይኖርም (ምሬት እና ጭቆና ብቻውን ለውጥ ሊያመጣ እደማይችል ከላይ በመግቢያዬ ያሰፈርኩትን ልብ ይሏል) – የጦረኞቹ የፖለቲካ ሰዎች ይህን መሰሉን ጉዳይ አፍታተው መዳረሻውን፣ ጥቅምና ጉዳቱን እስካሁን ማሳመንም ሆነ ደፍረው ለውይይት ሊያቀርቡት አለመቻላቸው በራሱ የትጥቅ ትግሉ አዋጪ እንዳልሆነ አመላካች ነው (there is something fishy behind the silence)፡፡ (እንዲህ አይነቱ ነገር መገለፅ የለበትም የሚል መከራከሪያ እኔ አልቀበልም – ሁላችንም በሀገራችን ጉዳይ ያገባናል!)
* እዚህ ጋር አብሮ መነሳት ያለበት ነገር ደግሞ – ይህን ትግል ለመቀላቀል የሚፈልጉ ሰዎች የሚከፍሉት አላስፈላጊ መስዋእትነት ነው፡፡ ገና ሳይጀመር በባዶ ሜዳ፤ በጉዞ ላይ እየተለቀሙ ዘብጥያ የወረዱትን እግዜር ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ ያም ብቻ ሳይሆን ከምትታገልለት ህዝብ ውጪ ሆነህ ልታገኘው የምትችለው የሎጀስቲክና ሌላም መሰረታዊ ድጋፍ አናሳ ነው፤ ከናካቴውም ላይኖር ይችላል፡፡ ለምሳሌ ያህል አሁን በኤርትራ ምድር ከሌላ ሀይል ጋር ውህደት የፈፀመው የአርበኞች ግንባር በተለይ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ከፍተኛ ድጋፍን ማግኘት የቻለና በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡ ምከንያቱ ደግሞ ይታገል የነበረው በዛው በህዝቡ መሃከል ሆኖ መሆኑ ነው (ያ አደጋ የለውም እያልኩኝ አይደለም ቢያንስ ግን ከባህሩ የወጣ አሳ አለመሆን ያለው ጠቀሜታ ከጉዳቱ ይበልጣል)፡፡ በየትኛው መልኩ ጭቆናው በቃኝ ብሎ ለሚያስብ ሰው ‘መንገዱም ጨርቅ’ ለመቀላቀልም ቀና የነበረ ግንባር ነበር፡፡ አሁንስ?
* እርግጥ የህዝባችን ስነ ልቡና ለትጥቅ ትግል የቀረበ መሆኑ አይካድም፡፡ ታሪካችንም ቢሆን ስልጣን በጦረኞች እንጂ በሰላማዊ መንገድ ተቀይሮ አያውቅም፡፡ ያም ሆኖ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁናቴ የዚህን መሰሉን የህዝብ ስነ ልቡናዊ ዝግጁነት ጥቅም ላይ ሊያውል የሚችል አስማሚ አጀንዳም የለም፡፡ ለዚህ አንዱ ማሳያ ደግሞ ራሱ በትጥቅ ትግል ያሉት የተበታተኑ ሀይሎች ናቸው፡፡ ይህ ችግርም ባልሆነ ነበር ግና ለነፃነት ዋጋ የሰጠና ለዛም ለመሞት የቆረጠው ምን ያህል ነው? አምናለሁ ነገርን የሚለውጡት ሚሊዮኖች ሳይሆኑ ጥቂቶች ናቸው – ቢሆንም በኔ እምነት እነሱም ከላይ በዘረዘርኳቸው ምክንያቶች ሌላ አማራጭ እንዲጠቀሙ ይገፏቸዋል (ለዚህ ነው ብዙዎች ተስፋ ቢያስቆርጥ እንኳን ለሰላማዊው ትግል ቅድሚያ የሚሰጡት)፡፡ ወጣም ወረደ በዚህ ጉዳይ ላይ የማነሳው መሰረታዊ ጥያቄ ግን በጣም ግልፅ ነው – ይህን ታሪክ እና ባህል ይዘን እንቀጥል ወይስ እንቀይረው? እውን ትጥቅ ትግል በትጥቅ ትግል የሚቀያየርን የስልጣን አዙሪት መስበር ይችላል? የጦረኛን ህዝብ ስነ ልቡና በጦረኛ መቀየር ይቻላልን?
* ሌላው ደግሞ ጦርነት ለሰብዓዊነት ቦታ አለመስጠቱ ነው፡፡ የሰው ልጅ አንድ ጊዜ ከገደለ በኋላ – ደም ካየ በኋላ ለሌላ ሰብዓዊ መብቶች ሊቆረቆር የሚችልበት ሩህሩህነት አይኖረውም፡፡ መግደልን የተለማመደ አንድ ሰው ጭካኔን እየተለማመደ መሆኑን ማንም አይክደውም፡፡ በዚህ ሁናቴ ስብእናው የሚገነባ ግለሰብም ሆነ ቡድን ደግሞ ለወደፊቱ ህልማችን አደጋ ነው፡፡ ሰው መጨከን የለበትም እያልኩኝ አይደለም (there may come critical times in life)- ሁሉም ነገር ግን የሚቃኝበት መንፈስ እንደ ነገሩ ተጨባጭ ሁናቴ መሆን አለበት፡፡ አሁን ላይ ይህን ያህል ርቀት መሄድ ይቻላል ወይም አለብን? መቀበል ይቸግረኛል!
ይህን የበለጠ ለማብራራት ሩቅ ሳንሄድ የሀገራችንን የትናንት ታሪክ እናንሳ፡፡ የህወሓት እና ኢህአፓ ታጋዮች ብረቱን እስኪጨብጡት ድረስ እንደሁላችን ሰዋዊ ባህሪያቸው እንዳልተለያቸው ምንም አጠያያቂ አይደለም – አንዴ ሞትን ተኩሰው ከተፉ በኋላ ግን የማያባራ እልቂት ሆነ፡፡ ሰብዓዊነታቸው ተሟጦ ግፉ ለኛም ተረፈ! ትጥቅ ትግል ይህ እንዳይሆን የሚሰጠን አንድም ዋስትና የለውም! በደም የታጠበ እጅ ህሊናው ለመፅዳት ትልቅ ፈተና አለበት፡፡ እረግጥ ሰብዓዊነት በፖለቲካ አውድ ውስጥ አሻሚ ትንታኔ ቢሰጥበትም በጥቅል ግን ከትጥቅ ትግል የፖለቲካ ትርፍ በላይ በማህበረስብ ስነ ልቦና ላይ የሚኖረውን ጠባሳ ከኛ በላይ ህያው ምስክር ያለ አይመስለኝም፡፡ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ አሁንም የአንድ አገር ሰው ወንድም በወንድሙ ላይ እጁን ማንሳቱ ነው፡፡
ሰላማዊ ትግል በኢትዮጵያ?
————————
* ዓለም ዛሬ የምትመራበት መርህ እና ሴራው እየረቀቀ ቢመጣም አንድ እውነት ግን መቼም ሊሻር አይችልም! በሰላማዊ ትግል ውስጥ ማናቸውንም ሀይል ከጎን ለማሰለፍ ትለቁ ነገር አገዛዝን በህግ የበላይነት እና የሞራል ልዕልና ማጠየቅ ነው፡፡ መሳሪያ ደግኖ ሲመጣ ደረትህን ነፍተህ መጋፈጥ የመሳሪያውን ብረት በእቶን እሳት ከማቅለጥ ያነሰ አይደለም፡፡ ዛሬ አንተን ቢገድል፣ ነገ ጓድህን ቢደግመው – ቀጥሎ ቃታውን የመሰብ አቅም አይኖረውም – ምክያቱም ጓዶችህ በባዶ እጅ ገጥመው እየወደቁ ህሊናውን አሸንፈውታል፡፡ ገዳይህ ብቻም ሳይሆን ሌላውም ሀይል ይህን ቆራጥነትህን ከመቀበል እና ከመተባበር ውጪ አማራጭ የላቸውም፡፡
እርግጥ ጨካኞች የሞቀ ቤታቸው ውስጥ ናቸው፣ ይህን ቆራጥነትህን አያዩትም አይረዱትም ስሜትም አይሰጣቸውም – መጠቀሚያቸው ግን የሚልኩት ወታደርና ፖሊስ ነው፡፡
በሰላማዊ ትግልም የምታሸንፈው ይህንኑ ሀይል እንጂ ጨቋኞቹን አለመሆኑ እሙን ነው፡፡ አፈሙዙን አዙሮ ጨካኞችን ወደ ዘብጥያ እንዲያወርድ የሚገደድበት የትግል ስልት ቢኖር ሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ልትገድለው ሳይሆን ሞትን ደፍረህ ለነፃነት ከምታደርገው ትግል በላይ ልቡን አቅልጦ ከጎንህ የሚያሰልፍው ሌላ መንገድም የለም፡፡ እንግዲህ ይህ የትግል ስልት በርካታ ጨቋኞችን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ስርዓቱን ጭምር እየተፈታተነ ያለ የትግል አይነት ነው፡፡
* በሌላ በኩል ይህ የትግል ስልት በኢትዮጵያ ያልተሞከረ በተግባርም እምብዛም ያልታወቀ ነው፡፡ የህዝባችን ስነ ልቡና በራሱ ለዚህ የትግል ስልት ዝግጁ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ኢህአዴግን በሰለማዊ ትግል ከማስጨነቅ ይልቅ ገና ከጅምሩ እዚህም እዚያም ትጥቅ ትግል የተጀመረው፡፡ ለዚህም ማሳያው ከ1998 በኋላ ከተፈጠረው ቡድን ውጪ ያሉት ታጣቂዎች ከጅምሩም በረሃ ወርደው የነበሩ መሆናቸው ነው (እርግጥ አንዳንዶቹ ከህወሓት ጋርም አብረው የገቡ ናቸው)፡፡ ከ1998 በኋላ ትጥቅ ትግልን የመረጠው ቡድንም ቢሆን ሰላማዊ ትግል ለማካሄድ እምብዛም አልጣረም፡፡ ኢህአዴግ እንከን የለሽ ምርጫ አደርጋለሁ አለ፤ ፓርቲዎች ተሰባሰቡ፤ እስካሁን ተፅዕኖ መፍጠር የቻለ ቅንጅት ፈጠሩ፤ እንከን የለሽ ምርጫ ተካሄደ፡፡ ውጤቱ ግን ብዙዎችን ተስፋ አስቆረጠ፡፡ የዘመነ የምርጫ ፖለቲካም አበቃለት! ቀጠለና አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ትግል አካሂዳለሁ፤ ህዝብን የስልጣን ባለቤት አደርጋለሁ ብሎ ትግል ሲጀምር – ሌሎች ደግሞ አይ ህዝቡ የሰጠንን ድምፅ በመሳሪያ እናስመልሳለን ብለው ጦርነት አወጁ፡፡ በኔ እምነት ሰላማዊ ትግል በኢትዮጵያ ምድር ላይ አለመጀመሩን ብቻ ሳይሆን ለመጀመርም ያለውን ችግር ይህ ኩነት ሁነኛ ማሳያ ነው፡፡
ምናልባትም የዚህ የትግል ስልት ትልቁ ተግዳሮት በህዝቡ ዘንድ አዲስ መሆኑና ለመቀበል እና ለመተግበርም እጅግ ድካምን የሚጠይቅ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ አልባ ትግል ለመምራት የሚነሱ መሪዎችም መጥፋት ነው፡፡ አንዱ ወደ እስር ሲጓዝ ሌላው በስሩ ተተክቶ ትግሉን ማስቀጠል ግድ የሚል የትግል ስልት መሆኑን ብዙዎች ይዘነጉታል መሰል አንዱ ሲነካ አስሩ ወይ ቤቱ ይቀመጣል ወይ ይሰደዳል ወይ ጦር ያነሳል፡፡ ይህ ትግል በቅብብሎሽ እንጂ በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃም ላይሆን ይችላል፡፡ እስክንድር ሲታሰር ተመስገን ይተካል ተመስገን ሲታሰር ሌላው ይቀጥላል እንጂ አለቀቀ ደቀቀ ሰላማዊ ትግል አይሰራም ሊባል አይችልም፡፡ አንዷለም ሲታሰር ሃብታሙ ይተካል ሃብታሙ ሲታሰር እኛ እንቀጥላልን እኛ ስንገባ ሌላው ይከተላል፡፡ አንድነት ፈረሰ ሰማያዊ ይቀጥላል – ሰማያዊ ሲፈርስ ወይ ሌላ ፓርቲ ወይ በሌላ መልክ ትግሉ ይቀጥላል፡፡ መሪ ብቻ አያሳጣ!
* ነፍጥ አልባ ትግል በመውጣትና በመውረድ ውስጥ፤ በአድካሚና ተስፋ አስቆራች ጉዞ ዘላቂነት ያለው ድል ያስገኛል፡፡ በነፍጥ አልባ ትግል ብዙዎቻችን ሙሴን እንጂ ኢያሱን ልንሆን አንታደልም (የህወሓቶቹን ሳይሆን የቅዱስ መፅሃፎቹን)፡፡ እንቅፋቶችም ብዙ ናቸው – በመንገድ ተንጠባጥበው የሚቀሩ – በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የሚሰናከሉ በርካቶች ለትግሉ በጠላትነት ሊነሱበት ሁሉ ይችላሉ፡፡ ካዛም አልፎ በሌላው ዓለም እንደታየው ዘለግ ያለ ጊዜ መውሰዱ አሰልችነት ቢኖረውም ውጤቱ ግን በሂደቱ ሁሉ የተረጋገጠ ነውና ተመራጭ ያደርገዋል፡፡ ህዝብን የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ማስቻል ብቻ ሳይሆን አመለካከቱንና ሌሎች በርካታ ጉዳዮችንም በሂደቱ እየታገለና መልክ እያስያዘ ከግቡ ይደርሳል፡፡
አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ይህን አድካሚ ጉዞ የሚያቃልል እና መንገዱንም የሚያሳጥር ምቹ ሁኔታ አለ፡፡ ላለፉት 40 እና 50 ዓመታት በደም መፋሰስ ውስጥ ያለፈ ህዝብ በስነ ልቦና ረገድ ያን ጊዜ ዳግም ለማየት ፍፁም አይሻም፡፡ ከዛም ሲያልፍ አዲሱ ትውልድና በእርስ በርስ ጦርነቱ ያልነበረው የህበረተሰብ ክፍል አሁን ላለው ዓለምአቀፍ ስርዓት ቀረቤታ ያላቸው መሆኑ ለአዲስ የትግል ስልት ዝግጁነታቸው ከፍተኛ የመሆን እድሉ ቀላል አይደለም (የድምፃችን ይሰማን እንቅስቃሴ ልብ ይሏል)፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ጨቋኞቻችን ዘመኑን የማይመጥኑ በአዲሱም ትውልድ በዓለምም ዘንድ መቀይር እንዳለባቸው፣ በእድሜ መግፋትም ቢያንስ ጡረታ መውጣት እንዳለባቸው የጋራ ግንዛቤ መኖሩ የሰላማዊ ትግሉን የሚያፋጥን ነባራዊ እውነታ ነው፡፡
* ሰላማዊ ትግል በምርጫ ፖለቲካ የሚገደብ አይደለም፡፡ እርግጥ ምርጫን እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊጠቀም ይችላል፡፡ ሂደቱ በራሱ ከአነስተኛ ነገሮች በመጀመር እያደገና እየረቀቀ ይሄዳል፡፡ በትግሉ ውስጥ በተጠና መልኩ የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ብቻ ሳይሆን በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን የማቀፍ ባህሪም አለው፡፡ አውቀው ከሚተገብሩት ባልተናነሰ መልኩ ሳይሰማቸውና ሳያውቁት በትግሉ የሚሳተፉም እንዲኖሩ እድል ይሰጣል፡፡ በሕቡ እና በግላጭም ሊካሄድ ይችላል፡፡ ሰላማዊ ሆነው ህግን መጣስ ድረስም መሄድ ይቻላል – ለምሳሌ ያህልም በሩሲያ Pussy Riot (የሴቶች መብት ተሟጋቾች እንቅስቃሴ – በተከለከሉ ቦታዎች እና ነውር በሆነ ሁናቴ ጭምር ተቃውሞን ማሰማት)፣ በኢትዮጵያ በቅርቡ እየተደረገ ያለው በመገልገያ ብር ኖት ላይ ተቃውሞን በማስፈር ማሰራጨት . . . የመሳሰሉት . . .
* ሰላማዊ ትግል መነሻው እና መዳረሻው የታወቀ ነው፡፡ ጊዜው ምን ያህል ቢረዝም እንኳን ውጤቱ ግን ዘላቂነት ያለው ነው፡፡ ስልጣንን ከጨቋኞች የማውረጃ ትግል ብቻ ሳይሆን – የጦረኝነትን ባህልንና የህዝብ ስነልቦና መቀየር የሚችል ትግል ነው፡፡ ያለመሳሪያ ጨቋኞችን ከስልጣናቻው ማውረድ የቻለ ህዝብ በራስ የመተማመኑ መጠን ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ማንም መጣ ማን ያለምንም ስጋት የፈለገውን የመሻር የፈለገውን የመሾም አቅም እንዳለው – እንደሚችልም የሚተማመን ህዝብ ሊኖር የሚችለው በሰላማዊ ትግል በሚመጣ ለውጥ ብቻ ነው፡፡ በተለይ እንደኢትዮጵያ በበርካታ ታሪካዊ ትብታብ እና ግጭቶች ውስጥ ላለፉ ሀገራት ሰላማዊ ትግል የቱንም ያህል ተስፋ አስቆራጭ እና አድካሚ ቢሆንም አማራጭ ግን ሊቀርብበት የሚችል አይመስለኝም!
* ሰላማዊ ትግል ጭቆናን ከማስወገድ ባለፈም በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ የመተማመን፣ የመተሳሰብና የመዋደድን ባህል ያሳድጋል፡፡ ሰብዓዊነትን ያጎለብታል፤ ለዓላማ መሞት እንጂ መግደልን ስለማያበረታታ ሰዋዊ የሆኑ እሴቶቻችንን ጠብቀን ስነምግባር ያለው ህብረተሰብ እንድንፈጥር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡
ሁለገብ ትግል በኢትዮጵያ?
———————–
* ይህ አይነት ትግል በተለያዩ ሀገራት ተሞክሮ ስኬታማ ሆኗል፡፡ በጥቅል ሲታይም ህዝባዊ እምቢተኝነትን (የነፍጥ አልባ ትግል አካል) እና ህዝባዊ አመፅ (የትጥቅ ትግል ደጋፊ ‘hot spot for armed struggle’) አቀላቅሎ የሚሄድ የትግል ስልት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁናቴ ሲቃኝ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚበዛ – የጨቋኞች አፈና እንዲጠናከር ሰፊ እድል የሚሰጥ ነው፡፡
* በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁናቴ የዚህ አይነት ትግል ዋነኛ እንቅፋት ደግሞ የቆሸሸው ፖለቲካ ባህላችን ነው፡፡ መተማመን የጠፋበት፣ አንዱ አንዱን ማጥፋት የሚፈልግበት፣ ሴራ የበዛበት እና በተጠና መልኩ መንቀሳቀስ ማናናቅ አዋቂ በሚያሰኝበት የፖለቲካ ባህል ውስጥ ውስብስብነት ያለውን ሁለገብ የትግል ስልት እንጠቀም ማለት ኢህአዴግ እድሜ ልኩን ሲገዛ ይኑር ከማለት አይተናነስም፡፡ ይህ ብቻ ቢሆን ደህና፤ ነገር ግን ሁለገብ ትግልን በሀገራችን ወቅታዊ ሁናቴ ለመተግበር አስቸጋሪ የሚያደርገው ሌላ መሰረታዊ ጉዳይ “የየትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው” አይነት ለውጤቱ ብቻ ትኩርት የመስጠት ዝንባሌ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ግድ የለሽ ለሂደቱ ደንታ የሌለው አካሄድ በሁለገብ የትግል ስልት ከሚያስገኘው ውጤት በላይ ኪሳራው የትየለሌ ነው፡፡ ስለዚህ በዚሁ ዘግተነው ወደ ማጠቃለያችን እናሳልጥ!
ማጠቃለያ
———-
በዚህ ሀቲት ውስጥ ለማመላከት እንደተሞከረው ሀገራችን አሁን ባለችበት ሁናቴ ከሁሉም የትግል ስልት ይልቅ ሰላማዊ የትግል ስልት ውጤታማነቱ የሚያሻማ አይደለም፡፡ እርግጥ ማናቸውም መንገድ የራሱ የሆነ መጥፎና ጥሩ ነገሮች ቢኖሩትም ከሌሎች የትግል አይነቶች በተሻለ የተመጠነ ኪሳራ ነገር ግን ዘላቂና የሚጨበጥ ውጤት ያለው የትግል ስልት መሆኑም አያከራክርም፡፡ ትልቁ ኃይልም ህዝብ ብቻ መሆኑ ከተቀሩት በቀጠናው ላይ አይናቸውን ከጣሉ ዓለምአቀፍ ሀይሎች ጋር ሰጥቶ መቀበል ወይም በሌላ ሴራ የመጠለፍ አደጋው በእጅጉ የቀነሰ ነው፡፡
ነፍጥ አልባ የትግል ስልት በሀገራችን አዲስ ከመሆኑ አንፃር ገና ዳዴ በማለት ላይ ቢሆንም በጥቂት ጀምሮ እየሰፋና ከዳር ዳር እንደሰደድ በመስፋፋት ለሀገራችን ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት ሰፊ እድል ያለው ነው፡፡
ባጠቃላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ (በሀገር ቤትም ሆነ በውጪም) እነዚህን የተለያዩ የትግል ስልት አይነቶች ትርፍና ኪሳራ በመመርመር እና በማገናዘብ ለኢትዮጵያ የሚበጀውን መንገድ እንዲመርጥ እና እንዲደግፍ መልእክቴ ነው፡፡ ከመነሻዬም እንዳሰፈርኩት የትግል ፍላጎት፣ የነፃነት ስሜት ገፊ ሀይል እና ጭቆና ብቻውን ለለውጥ አያበቃምና ሀገራችን በተያያዘችው ከአገዛዝ ወደ ነፃነት የሚደረግ ትግልን የምትመሩ ቡድኖችና ግለሰቦች ቆም ብላችሁ መንገዳችሁን ብትመረምሩ መልካም ነው፡፡ ከታናሽ ወንድማችሁ በሚሆን ምክርም ፅሁፌን ላብቃ – ብቻ ምንም እንወስን ለውሳኔያችን ቆራጥ፣ የተግባር ሰው እና ለሀገራችን እና ለህዝባችን ስንል ከተራ ሴራ፣ በከንቱ ውዳሴ ከመኮፈስ የፀዳን እንሁን!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

 Source: Satenaw

Tuesday, March 24, 2015

አሳፋሪነቱ እየተባባሰበት የመጣው "ፍርድ ቤት" የመብት ጥሰትንም ሆነ የሲዲ ማስረጃዎች ጥያቄን አልቀበልም አለ

ሁለት የጎንዬሽ አቤቱታዎችን አስመልክቶ ዛሬ የተሰየመው ችሎት ከሌላ ጊዜው በባሰ ሁኔታ የወንጀል ስነስርአትና የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች ላይ ሲቀልድ ውሏል፡፡ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ እና ጦማሪት ማህሌት ፋንታሁን በጎብኚዎች የመጠይቅ መብታቸው መነፈጉን በቀን 20 ደቂቃ ብቻ ከሌሎች እስረኞች ከቅርብ ቤተሰብ ውጪ ሌላ አንዳይገባ እንደተከለከሉ መሰረታዊ መብቶቻቸው እስር ቤት ውስጥ አንደሚጣሱ ባለፉት ስድስት ወራት በተደጋጋሚ አቤቱታ ሲያቀርቡ የከረሙ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የመብት ጥሰቱን የሚያሳይ ምንም ማስረጃ አልቀረበም፣ ከማረሚያ ቤቱ ጋር ያለውን አስተዳደራዊ ችግርን የመፍቻ መንገድ አልተጠቀሙም በማለት በውሳኔው የህገ መንግስቱን አንቀጽ 21 ሽሮታል፡፡ አያያዛቸው መሰረታዊ መብቶቸን የሚያስጠብቅ ይሁን ብሎ የተለመደውን የለበጣ ትእዛዝ አንኳን መስጠት ያቃተው የዛሬው "ፍርድ ቤት" የሁለቱን ወጣት ሴቶች መሰረታዊ የመብት ጥያቄ እነደዋዛ አጣጥሎታል፡፡
ሁለተኛው ጉዳይ የነበረው አቃቤ ህግ የሲዲ ማስረጃዎቹን ለተከሳሾች ሊሰጥ አንደሚገባ ሲጠይቅ የወንጀሉ ኤግዚቢት ነው በማለት ያቀረበውን መከላከያ ፍርድ ቤቱ ተቀብሎ ለተከሳሾች ሊሰጥ አይገባም ሲል ሌላ አስገራሚ ብይን አሰምቷል፡፡ ብይኑን ተከትሎ የተከሳሽ ጠበቆች የወንጀል ኤግዚቢት ከሆነ ሲዲው በአቃቤ ሀግ እጅ መገኘት አንደማይገባና በህጉ መሰረት ፍርድ ቤቱ እጅ መቀመጥ አንዳለበት በመሆኑም ሲዲው የት አንደሚገኝ የጠየቁ ሲሆን "ፍርድ ቤቱ" በጠበቆች ስላልተጠየቀ ሲዲው ሬጅስትራር ጋር መሆኑ እና አለመሆኑን እነዳላጣራ አስገራሚ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ይህንን አስተያት ተከትሎ የህግ ባለሞያው ዘላለም ክብረት ለፍርድ ቤቱ አጠር ያለ የወንጀል ስነስርአት ሂደትን የሚያስረዳ ማብራሪያ ከሰጠ በኋላ "በዚህ ሂደት ፍርድ ቤቱ በግልጽ ሲዲው የማስረጃው አካል ነው ወይስ ኤግዚቢት ነው የሚለውን አሁን ይንገረን ፡፡ ኤግዚቢት ነው ከተባለም አቃቤ ሀግ የማስረጃ አካል አድርጎ እንዳያቀርበው አሁን ብይን ይሰጥልን በማለት ጠይቋል"፡፡ "ፍርድ ቤቱም" ይህንን መወሰን ያለበት አቃቤ ህግ ነው የሚል የእለቱን አስገራሚነት የጨመረ መልስ ሰጥቷል፡፡ ይህንን ተከትሎ አቃቤ ሀግ ማስረጃ ነው ካለም በማስረጃ መስማቱ ወቅት በሂደት የሚታይ ነው ያለ ሲሆን ብይኑን ከጠበቆች እና ከተከሳሾች በቀረበበት ተከታታይ ጥያቄዎች ሲያምታታ ተስተውሏል፡። ተከሳሾች ተቃውሞ ካላቸው ይግባኝ ማቅረብ ይችላሉ የተባለ ሲሆን ጦማሪ ናትናኤል በበኩሉ አቃቤ ህግ ያለውን ብቻ በመስማት ተከሳሾች ላይ ተጽእኖ እያደረጋችሁ ነው ሲል "ፍርድ ቤቱን" ከሷል፡፡
በእስር ላይ አንድ አመት ሊሞላቸው አንድ ወር የቀራቸው የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች በጠንካራ መንፈስ እና ፈገግታ ችሎቱን የታደሙ ሲሆን በፍርድ ቤቱ ውጥንቅጥ ምንም አይነት መገረም አልታየባቸው፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
ከዚህ በፌት በተደጋጋሚ አንዳልነው የዞን9 ጦማርያን ፍርድ ቤት የሚሄዱት የፍትህ ስርአቱን ህጋዊ እውቅና እና ቅቡልነት ለማሰጠት ሳይሆን በቃል ስንለው የከረምነውን የፍትህ ስርአቱን ውድቀት በተግባር ለማረጋገጥ ነው፡፡ ሁሉንም የህግ አማራጮች በመጠቀም ፍርድ ቤቱን በማጋለጣችን በእስርም ሆነ በስደት የምንገኘው የዞን9 አባላት በኩራት አንገታችንን ቀና በማድረግ የምንናገረው ጉዳይ ነው፡፡ በየቀኑ የራሱን መሰረታዊ መስፈርት እና ጥቃቅን የወንጀል ስነስርአት ህግ አንኳን መከተል ያቃተውን ፍርድ ቤት የሚመሩት ዳኞች ከችሎቱ ሲወጡ እና ከህሊናቸው ጋር በግልጽ ሲነጋገሩ የስራ አስፈጻሚው መሳሪያነታቸውን ቀን ከቀን በአሳፋሪ ሁኔታ እያጠናከሩ መሆኑን እነደሚያውቁት እርግጠኞች ነን፡፡ ራሳቸውን ከችሎቱ አግልያለው ብለው አስካሁንም ችሎቱን እየሰበሰቡ ባሉት አቶ ሸለመ በቀለ ለሚመራው ችሎት በተደጋጋሚ ጥሪ ስናደርግ እነደነበረው የፍትህ ስርአቱን ስም የማደስ እድላቸውን እየተጠቀሙበት ካለመሆኑም በተጨማሪ የነርሱ ከፍትህ እና ከታሪክ በግራ በኩል መቆም ከማሳየቱም በላይ የወጣት አስረኞቹን ልእልና ቀን ከቀን ከፍ ብሎ እነዲታይ እያስቻሉ ነው፡፡
አገራቸውን በጨዋነት የሚያገለግሉ ምሁራን የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች አምባገነንነት እና የተቃውሞ ድምጽ ማፈኛ መሳሪያ የሆነው የፍትህ ስርአት ያልፈታቸው ጨዋዎች መሆናቸውን በማስመስከራቸው እንኮራለን፡፡ የህሊና እስረኞቹ በማንኛውም መስፈርት ቢለኩ ከደረጃቸው በታች በሆኑ ዳኞች ፌት መቆም ያልነበረባቸው የቤተሰብና የአገር ኩራቶች ናቸው ፡፡
የፍትህ ስርአቱን ውድቀት ማጋለጡ ይቀጥላል፡፡
ዞን9

የጦማርያንና ጋዜጠኞቹ አቤቱታዎች ውድቅ ተደረጉ

ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው የሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ሦስቱ ወዳጅ ጋዜጠኞች መጋቢት 15/2007 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡
zone 9 bloggers
መዝገቡ ተቀጥሮ የነበረው ተከሳሾች ባቀረቧቸው ሁለት አቤቱታዎች ላይ ፍርድ ቤቱ መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡ በዚህም አንደኛ አቃቤ ህግ በተከሳሾች ላይ አለኝ ካለው ማስረጃ ዝርዝር ውስጥ 12 የኦዲዮ-ቪዲዮ ሲዲዎች አያይዞ ያቀረበ ቢሆንም፣ ሲዲዎቹ ለተከሳሾች እስካሁን ባለመድረሳቸው ተከሳሾች የቀረበባቸውን ማስረጃ ተመልክተው መልስ ለማዘጋጀት ሲዲዎቹ እንዲሰጧቸው ያቀረቡት አቤቱታ ሲሆን፣ ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ 4ኛ ተከሳሽ ማህሌት ፋንታሁን እና 9ኛ ተከሳሽ ኤዶም ካሳዬ በቃሊቲ እስር ቤት አስተዳደር ላይ ከጎብኝዎቻቸው መከልከል ጋር በተያያዘ አቅርበውት በነበረው አቤቱታ ላይ ብይን መስጠት ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱም ሁለቱንም አቤቱታዎች ውድቅ አድርጓል፡፡
የሲዲ ማስረጃውን በተመለከተ አቃቤ ህግ ማስረጃዎችን ኢግዚቪት ብሎ ስላስመዘገበ አሁን በዚህ ደረጃ ሲዲዎቹ ለተከሳሾች የሚደርሱበት አግባብ የለም በሚል ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን አቤቱታ እንዳልተቀበለው ገልጹዋል፡፡ በመሆኑም ተከሳሾች ማስረጃ በመስማት ሂደት ወቅት ማስረጃዎችን እየተመለከቱ መልስ እንዲሰጡ እንጂ ቀድሞ እጃቸው የሚደርስበት አሰራር የለም ብሏል ፍርድ ቤቱ፡፡
ፍርድ ቤቱ የቃሊቲ እስር ቤት አስተዳደር ላይ በሁለቱ ሴት ተከሳሾች የቀረበውን አቤቱታም ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በተከሳሾች የቀረበውን አቤቱታ እና የእስር ቤቱ አስተዳደር የሰጠውን መልስ መመልከቱን የገለጸው ፍርድ ቤቱ፣ ‹‹ለቀረበው አቤቱታ ማስረጃ ተያይዞ ያልቀረበ በመሆኑ…›› በሚል አቤቱታውን ቅድቅ አድርጓል፡፡ ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከሰኞ መጋቢት 21/2007 ጀምሮ ለሦሰት ቀናት ይሰማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Monday, March 23, 2015

የመከላከያ ሰራዊት አባላት በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዘዙ

Ethiopian Defense
መጋቢት ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ሰሞኑን በሰሜን ጎንደር አካባቢ የታየውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ የአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ካለፈው ሃሙስ ቀን ጀምሮ በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዛዋል።
የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የአየር ሃይል አባላት ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ ከግቢ እንዳይወጡ ሲታዘዙ የተወሰኑት ደግሞ ከደብረዘይት እና ድሬዳዋ አየር ሃይል ወደ መቀሌ አምርተዋል። ብዛት ያለው የእግረኛ ሰራዊትም ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች አቅንቷል።
ወታደራዊ ልምምዶችና አዳዳስ ምልመላዎችም እየተካሄዱ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል።
ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የተቃዋሚ ሃይሎች ጎንደር ከተማ ውስጥ የሚሊሺያ አዛዥ የሆነውን ኮማንደር ተፈራን ገድለው ካመለጡ በሁዋላ፣ እነሱን ለመያዝ መጋቢት 12 አርማጭ ልዩ ቦታው እንኮይ ተራራ ላይ በተደረገ ጦርነት ፣ ከተቃዋሚዎች በኩል ሻምበል ይርዳውና
አዲሱ የተባሉ ሲገደሉ፣ ከመንግስት ታጣቂዎች በኩል ደግሞ የልዩ ሃይል አባል የሆነው እባበይ እንዲሁም አንድ ስሙ በውል ያልታወቀና ሁለት የሚሊሺያ አባላት ተገድለዋል። ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ጀምሮ እስከ ምሽት በቀጠለው የተኩስ ልውውጥ፣ አንድ ተማሪ በመንግስት
ሃይሎች ተገድሏል። የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ምሽት ላይ አካባቢውን ጥለው መውጣታቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስትን አስተያየት ለማካተት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።
Source:: Ethsat