Sunday, November 9, 2014

“ልማት ልማት” በሚለው ፕሮፓጋንዳ ደንዝዘን


አንዲት እናት ልጇን ለማስተኛት አሊያም መነጫነጩን እንዲተው የማደንዘዣ ዘዴ አላት፡፡እሽሩሩ….” የሚለውን ቃል መደጋገም ብቻ ነው፡፡ ልጇም በመጨረሻ ወደ ፀጥታው የእንቅልፍ አለም ይሄዳል፡፡እሹሩሩማለት ማንቃት አይደለም፡፡ የማስተኛ ማደንዘዣ ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ስማችንን/ የምናውቀውን ሰው ስም ለተወሰነ ጊዜ በተደጋጋሚ ብንጠላው ከዚህ በፊት የሰጠነው የአይነት፣ መጠን ቀለምና የመሳሰሉት ተመሳስሎሾች ይጠፋብናል፡፡ ከዚያም ብሶ ራሳችንን/ የጠራነውን ሰው ወደ አለማወቅ የሚደርስ ብዥታ ይጠፋብናል፡፡ ከዚያም ብሶ ራሳችንን /የጠላነውን ሰው ወደ አለማወቅ የሚያደርስ ብዥታ ይፈጥርብናል፡፡ እንደነዝዛለን፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ሕዝብእሹሩሩ በመደጋገም ያደነዝዛል፡፡ በመደንዘዛችን ደግሞ በየትኛውም የኑሮ ደረጃ አካባቢ እንዳለን ጭምር ይጠፋብናል፡፡ የቃሉ ድግግሞሽ የፈጠረብን ውዥንብር፣ በህልም አለም ስለሚያሰክረን ድህነት ላይ ሆነን ድህነትን እንረሳለን፡፡ አሊያም ድህነትንበልማትስም የበለጠ እንላመደዋለን፡፡ እየተለማመድነውም ነው፡፡የቸኮለ ሰው ሲቆም የሄደ ይመስለዋልበድህነት የኖረ ደግሞ ሲያወራ የበለፀገ ይመስለዋል፡፡ ጉንጭ አልፋ የማይላቀቀን የድህነት ኑሮ በልማታዊ በፕሮፓጋንዳ ድህነት ተጭኖን ደህነትን ረስተነዋል፡፡ባለፉት አምስት አመታት በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅና እጅግ የምንኮራበት ልማት ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ የዚህን ድል ታላቅነት አቃሎ ማየት ፍፁም አይችልም
“ስለልማት ሲነሳ ኢትዮጵያ እንደ አገር …. ለምሳሌ የሚጠቀስ እንኳን የሚኖርባት አገር ነበረች፡፡ ዛሬ ምሳሌዎችን ጠቅሰን አንዘልቀውም፡፡ እድገቱና ልማቱ ደግሞ ልዩ ባህሪ አለው” ይህ ዘዴ፣ ለነገሮች ያሉን የመጠን እና አይነት ግንዛቤን ያደበዝዛል፤ ያደነዝዛል፡፡ ለምሳሌ ደርቅና ርሃብ ማለት የ1966ቱ እና የ1977ቱ መጠን እና ዓይነት መሆን አለበት ብለን ካሰብን እውነትም የችጋርን አለንጋ ለምደናል፡፡ በችጋር ውስጥ ሆነን ችጋር ማለት ልክ እንደ 19977ቱ ሁሉ የሚላስ የሚቀመስ ሙሉ በሙሉ የሚጠፋበት ጊዜ እንጂ ቁርስ በልቶ ምሳ እና እራት ያለመድገም ወይም ያልተመጣጠነ ምግብ መጠረቅ ስለማይመስለን “ዲማ ከዚህ መንደር ይርቃል?” በማለት ባሰብነው ግዝፈት ልክ እንጤቃለን፡፡

ያን ባሰብኩ ቁጥር አለማወቅ ምን ጨለማ፣ ምን ከባድ፣ ምን የተምታታ ድፍን ያለ ነገር ነው? እላለሁ፡፡ እየራበን ከችጋር ላይ ቁመን፣ ችጋር እየጠበሰንልማት ልማትበሚለው ፕሮፓጋንዳ ደንዝዘን ርሃቡ ጥጋቡ፣ ደህነታችን ልማት እየመሰለን በቁማችን ሙተን ኖርን እንላለን!!


ETHIOPIAN GOVERNMENT’S WITCHHUNT AGAINST PRIVATELY-OWNED MEDIA


Ethiopian government's witchhunt against privately-owned media


Reporters Without Borders

At least six publications have had to close in recent months and around 30 journalists have fled abroad since the start of the year as a result of the biggest crackdown on the privately-owned press since 2005, one reflecting a government desire to make a clean sweep of independent media before parliamentary elections next May, local analysts say.
In the latest development, Reporters Without Borders learned on 1 November that magazine editorTemesgen Desalegn has been transferred to a prison in the town of Ziway, about 200 km away from Addis Ababa to serve the three-year jail sentence of his 13 October condemnation.
Desalegn was convicted of publishing reports about “politicians and journalists linked to terrorist groups” in the now-closed newspaper Fitih, which he edited before becoming the editor of Fact, a magazine closed in August. These charges were dropped after originally being brought against Desalegn in connection with a defamation case in 2012, but were revived last year.
“We are extremely concerned about Temesgen Desalegn’s conviction and his transfer to a prison far from his family, especially as he has chronic health problems,” said Cléa Kahn-Sriber, the head of the Reporters Without Borders Africa desk.
“This conviction is just the latest example of the witchhunt that the Ethiopian government has decided to wage against the independent press. Invoking the spectre of terrorism in order to silence critics has unfortunately become a systematic government practice.”
Desalegn’s trial and conviction have been preceded by many other acts of intimidation and harassment that have created a state of extreme fear within the Ethiopian media.
The owners of three magazines – Endalkachew Tesfaye of Addis GudayGizaw Taye of Lomi andFatuma Nuriya of Fact – were convicted in absentia of “encouraging terrorism” on 7 October and were given sentences ranging from three years and three months to three years and eleven months in prison.
The source of the charges was the justice ministry, which has brought the same charges against three other publications – Enqu, Jano and Afro-Times – whose fate is not yet known.
Even public media are not spared when they stray from the party line: in June, 18 journalists werefired by the main state-owned broadcaster in Oromia, Ethiopia’s largest region, because of their political views.
In April, six bloggers with the Zone 9 collection and three journalists – one a freelancer and the other two employed by privately-owned media – were arrested in the course of a single weekend without any explanation being given.
It was only after they had been held without charge for three months that they learned that they were to be prosecuted under the 2009 anti-terrorism law for allegedly “organizing themselves into covert sub-groups to overthrow the government by contacting and receiving finance and training from two designated terrorist groups” – a charge that carries a possible 15-year jail sentence.
Since then, all their requests to be released on bail have been denied.
“We call on the authorities to reverse these convictions of journalists and media owners on specious grounds in recent months and to withdraw all the charges against the news and information providers currently jailed or in exile,” Reporters Without Borders deputy programme director Virginie Dangles said.
Persecution campaign against independent media
A smear campaign against a number of independent newspapers began in January when the government newspaper Addis Zemen published an Ethiopian Press Agency study listing articles they had published that allegedly promoted an uprising and terrorism.
One of the journalists concerned said: “This is where the government announces its future decisions. If your name appears there, you know you are going to have problems.”
In late August, state-owned Ethiopian TV broadcast three documentaries, including one entitled “Untamed Pens,” that portrayed the staff of the magazines Lomi, Fact, Enqu, Jano, Addis Guday and the newspaper AfroTimes as enemies of the state. This documentary aims at justifying the charges brought against these publications.
In the weeks before and after this documentary aired, several media were closed down and their employees threatened or harassed.
Seals were placed on the entrance to Lomi’s office on 19 July – on the grounds that it did not have a licence to operate – and the police searched it thoroughly. Ethio Midhar, a newspaper, was closed in October and its editor was summoned for questioning by the criminal investigation division, known as Maekelawi.
The companies that print certain newspapers, such as Ethio Midhar, Addis Guday and Lomi, have also been harassed by the authorities, as a result of which they are now refusing to print them.
Many journalists have reported being summoned by the police and threatened with arrest or physical reprisals. When the police could not locate them, they threatened their relatives with arbitrary arrest or raids on their homes.
All this harassment and intimidation has created a climate of terror within the media community that has driven about 30 journalists to flee the country since the start of the year. The entire staff of some publications has fled abroad. They include Lomi, whose editor, two of its reporters and six other employees fled abroad as soon as the judicial proceedings were initiated.
Many have gone to the Kenyan capital of Nairobi, which Reporters Without Borders visited last month to interview them about their life in exile and the way they were persecuted in Ethiopia. With no source of income, they have had to endure the most appalling material and psychological conditions in Kenya, and fear being followed by the Ethiopian embassy’s agents.
“I arrived here just a few days ago,” one told Reporters Without Borders. “I am in a neighbourhood where many Ethiopians live. I don’t feel safe. I need a safer place but I don’t really know where to go.”
Despite the extremely precarious situation awaiting them, journalists are continuing to flee Ethiopia.
Another newly arrived journalist said: “Other colleagues are thinking of joining us. The legislative elections are coming and they know that the climate will continue to deteriorate.” One journalist,Million Shurube of the newspaper Maraki, fell ill during the journey and died in exile for lack of treatment.
Observers of the situation in Ethiopia say this is the worst crackdown since the one that followed the elections in 2005.
Looming parliamentary elections
Although its economic and social record has been relatively satisfactory in recent years, the Ethiopian government seems to fear any form of criticism or protest at a time when ethnic and religious-based demands are growing.
“The government has managed to eliminate much of the privately-owned press in the space of a few months, thereby curtailing public debate and the ability of ordinary citizens to discuss issues concerning them,” Kahn-Sriber said. “Such a censorship campaign in the run-up to elections is particularly disturbing.”
An Ethiopian media analyst who spoke to Reporters Without Borders on condition of anonymity said the situation is all the more worrying because it will continue until next May at least. “Even if the bloggers and journalists continue to appear in court, their case won’t advance before the elections. The government is deliberately blocking it.”
The privately-owned press is clearly experiencing its most difficult period in a decade even if some publications, such as Reporter, Addis Admas and Ethio Miska, are continuing to appear.
“It’s true that some journalists have been very critical of the government but it is important to respect the principle of proportionality,” the analyst said. “There are procedures for challenging articles regarded as defamatory. Mass arrests and forcing newspapers to close are counter-productive, especially if the very existence of these critical newspapers is a direct result of the government’s news control policies.”
Publications that did not originally intend to cover politics felt obliged to evolve because of a pressing public demand for more diverse coverage of political and social developments. And sometimes their staff took radical positions that failed to respect media ethics.
But, according to the information obtained by Reporters Without Borders, none of these media ever published articles that justified the current crackdown. The government’s aim is to clear – to install such a level of fear that it will not be challenged.
According to Reporters Without Borders’ tally, at least ten journalists and six netizens are currently detained in Ethiopia, which is ranked 143rd out of 180 countries in the 2014 Reporters Without Borders press freedom index.
Source:Reporters Without Borders 

የህወሃቱን ፖለቲካ የአዋጁን በጀሮ!

ህወሃት በተፈጥሮው የፖለቲካ ብዙህነት ወይም ብዝሃነትን ማቻቻል የሚባል ነገር አያውቅም። ሌላው ቀርቶ በራሱ በድርጅቱ ውስጥ የሚነሱ የተለዩ ሃሳቦችን ሁሉ እንደጠላት ሃሳብ ፈርጆ ሰዎችን ደብዛቸውን ማጥፋት የተለመደ የህወሃት አሰራር ነው። ይህን የህወሃት ባህርይ በቅጡ ለመረዳት በቅርቡ የቀድሞው የህወሃት አመራር አባል የነበረው አቶ ገብሩ አስራት የጻፈው መጽሃፍ ጥቂት ገጾች በማየት መረዳት ይቻላል። ተቃዋሚ ፓርቲ ሰላማዊም ሆነ አልሆነ በህወሃት እንደጠላት ነው የሚቆጠረው።
ሰሞኑን ከትግራይ የህዝብና የመንግስት ግንኙነት ቢሮ ከሚባለው መስሪያ ቤት በትግረኛ ተጽፎ ለአባለት በሚስጥር የተሰራጨ ደብዳቤ ማንኛውምንም ተቃዋሚና ከህወሃት ውጭ የሚያስብና ህወሃትን የማይከተል ሁሉ “ፀላኢቲ” ጠላቶች ሲል ይፈርጃል። በዚህ ባለ 5 ገጽ ደብዳቤ ውስጥ እነዚህን “ፀላኢቲ” እንዴት እንደሚያሳድዱ፣ እንዴት እንደሚያዋክቡና እንደሚያጠፉ የሚመክር መመሪያ የሚሰጡ ሃሳቦች ተቀምጠዋል። በደብዳቤው ላይ ከአናቱ ሆነው የሚያስተዳደሩትን ወገናቸውን እንኳን አይለይም። በአጭሩ እኛ እንዳንመርጥ የሚፈልግ፣ የሚቀናቀንና ሌሎች ሰላማዊ ፓርቲወችን የሚመራና የሚደግፍ ሁሉ ፀላኢቲ ነው።
ይህ ለ2007 ዓ.ም የክትትል ስራ የተመደበው የህወሃት ቡድን ስራውን የሚያከናውነው ከታክስ ከፋዩ በሚገኝ የመንግስት ገንዘብ መሆኑ ይታወቃል።
ዘንድሮ የምርጫ አመት መሆኑን ተከትሎ የፀላኢቲ ክትትልና አፈና ከአሁን ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ መሆኑም እየታየ ነው። ጠንካራ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ በየክልሉ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ሁሉ በመታፈንና ወህኒ በመውረድ ላይ ናቸው።
የህወሃት ኢህአዴግ መሪዎች በአለም ዙሪያ ነጻነቴን የሚል የህዝብ ድምጽ በሰሙ ቁጥር የሚሰማቸውን ድንጋጤ የሚቀንሱት ዜጎችን በማፈን፣ በመግደል፣ በማሰቃየትና በማሰር ብቻ ነው።
ለህወሃት ምርጫና መድብለ ፓርቲ መልክን አሳምሮ ተቀባይነት ወደ ምእራባውያን ለልመና ለመውጫ እምጅ ዴሞክራሲያዊ ምርጫና የህዝብ ልእልና የሚባል ነገር ባጠገባቸው እንዲያልፍ ስለሚፈልጉ የሚያደርጉት አለመሆኑን በብዙ መንገዶች አሳይተውናል።
ከህወሃት ውጭ ያልህ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ አንተ ለወያኔ/ህወሃት ፀላኢቲ ጠላት ነህ። ወገኖቼ ብለህ የምታስብ ሁሉ ይህን የሚስጥር ደብዳቤያቸውን በማየት ብቻ ሳይሆን በተግባር አይተሃልና።
ያለህ ምርጫ እንደአባቶችህ፡-
እልም እንጅ ውሃ አይላመጥም፣
ጠላት ወዳጅ ላይሆን አልለማመጥም።
ብለህ መነሳይ ይኖርብሃል።
ትእግስት፣ አስተዋይነትና የፍቅር መንገድ መመኘት ከህወሃት ፀላኢቲነት አያላቅቅም። ህወሃትን ማስወገድ በጠላትነት ፈርጆ ሊውጥህ የመጣ ጠላትን ማስወገድ ማለት ነው።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ከዚህ በጠላትነት ከፈረጀህ የዘርፎ አደሮች ቡድን እንድትላቀቅ አቅሙን በመገንባት ለወሳኝ ፍልሚያ እተዘጋጀ ነው። መላው ወገናችን ወያኔ የፈጠረልህን የክፍፍልና የልዩነት አጥር እያፈራረስክ አንድነትን አጠንክር። በያለህበት ለነጻነትህ ተነሳ። ኑሮን ለማሸነፍም ሆነ መረጃ በማጣት በወያኔ ስር ተደራጅተህ በሎሌነት እንድታገለግል የተፈረደብህ ወገን ሁሉ ወያኔ ጠላት ብሎ እንደሚቆጥርህ አትዘንጋ። የነፃነታችን ቀን ቅርብ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Saturday, November 8, 2014

በአንድነት ተሰባስበን መታገሉ ግዴታችን ነው

"የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ" እንመስርት!
unity-11

ውድ ኢትዮጵያዊ ድረገጽ፤
ከታች ያለውን ደብዳቤ ለግለሰቦች መላክ ፈለግሁና፤ ለማን ልላክ ብዬ ካወጣሁ ካወረድኩ በኋላ፤ የተወሰኑ ስሞችን ሰበሰብኩ። እኒህን ለይቶ ማውጣቱና፤ እኒህ ብቻ ናቸው ብሎ መለየቱ አሳሰበኝ። ማን ማንን ይወክላል? ሌላውስ ላለመወከሉ ምን መከላከያ አለኝ? እኒህን ለመሰሉ ጥያቄዎች፤ አመርቂ አልስ መሥጠት አልቻልኩም። ለምን በጠቅላላው በትግሉ ላይ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ፤ ይኼ ኃላፊነት አለብን በማለት አልልክላቸውም? የሚለው ውሳኔ አስታራቂ ሆነልኝ። በየቦታው ኢትዮጵያዊያን እየታገሉ ነው። ይኼን ትግል ወደ አንድ ማዕከል ማምጣቱ ነው የዕለቱ ጥያቄ። በሃይማኖት ተከታዮች በኩል የሚደርሰው በደል፣ በትውልድ ሐረጋቸው የተነሳ የሚደርስባቸው በደል፣ በተሰማሩበት የንግድ መስክ የተነሳ የሚደርስባቸው በደል፣ በመኖሪያ አካባቢያቸው፣ ለንግድ ተብሎ ከቦታቸው በሚፈናቀሉት ላይ የሚደርሰው በደል፣ በተማሪዎች፣ በአስተማሪዎች፣ በወታደሮች፣ሁሉም በኢትዮጵያዊነታቸው በደል እየደረሰ ነው። ይህ ሁሉ ኢትዮጵያዊያንን በተለያየ መንገድ ለትግል አነሳስቷል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታገሉ አሉ። ከሀገር ውጪ ባለነው ኢትዮጵያዊያን መካከል የምንታገል አለን። ይህ ለድል የሚበቃው፤ ይህ ሁሉ ኢትዮጵያዊ በሙሉ በአንድነት ተሰባስቦ ሲነሳ ነው። ይሄን ሁሉ ለማስተባበርና ባንድ ለማሰለፍ፤ የተዘጋጀ መልስ የለንም። በሂደት ማዘጋጀት አለብን። አንድ ቦታ ላይ መጀመር አለብን። ለዚህ የሚያስፈልገን፤ በትግሉ ላይ የተሰማራነው አንድ የኢትዮጵያዊያን ነፃነት ንቅናቄ መሥርተን መነሳት ነው። ባሁን ሰዓት ያለውን ተጨባጭ ሀቅ ተረድተን፤ ይሄ ተጨባጭ ሀቅ ላቀረበልን ጥያቄ ትክክለኛ መልስ መሥጠት አለብን። ጥያቄው፤ በአንድነት ሆነን ለወገናችን እንድንደርስና ሀገራችንን እንድናድን ነው። ታዲያ ለምን ይሄን አናደርግም? የሚለውን ሁላችን በያለንበት እያወጣን እያወረድን መሆናችን ግልጽ ነው። እናም እኔም የምችለውን ለማድረግ ተነስቻለሁ።
በዚህ ጽሑፍ፤ ለእያንዳንዱ ታጋይ ኢትዮጵያዊ፤ የመሰባሰቡን ግዴታ ብቻ ሳይሆን፤ መሰባሰቢያ ነጥቦቻችንን በማስፈር፤ ለመሰባሰብ ጅምሩን አስቀምጫለሁ። ጥሪዬ ለሁላችን ለታጋይ ኢትዮጵያዊ ግለሰቦችና ታጋይ ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ነው። የጥሪውን ተጋቢነት የተቀበላችሁ በሙሉ፤ መልስ በመሥጠት መሰባሰቡን እንጀምር። በሂደት ጉልበታችንን እናጠናክራለን። መስተካከል ያለበት ይስተካከላል። የጎደለው ይሞላል። መጀመር አለበት።
እናም፤ ውድ የኢትዮጵያዊ ድረገጽ አዘጋጅ፤ እባክዎትን ይሄን ለትግል የመሰባሰብ ጥሪ፤  ለርስዎ ያከልኩትን መግቢያ አድርገው፤ ለአንባቢዎ እንዲደርስ ያውጡልኝ።
ከላቀ የአክብሮት ምስጋና ጋር
አንዱዓለም ተፈራ
ለእርስዎ፤ ጊዜ ወስደው ይኼን ለሚያነቡ ታጋይ ኢትዮጵያዊ፤
በአንድነት ተሰባስበን መታገሉ ግዴታችን ነው።
ውድ ታጋይ ኢትዮጵያዊ፤
በምኞት የምንጋልበው ፈረስ፤ ከፈለግነው ቦታ በፍጥነት የሚያደርሰን፤ በምኞት ዓለም ውስጥ ብቻ ነው። እኛ አሁን በአንድነት ያጋጠመን የምኞት ችግር ሳይሆን፤ የሀገራችን ተጨባጭ ሀቅ ነው። ይህ ደግሞ ተጨባጭ መፍትሔ ይጠይቃል። ሀቁን ተረድተን፣ ማድረግ ያለብንን ለይተን፣ ከትናንት ዛሬ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ የተሻለ ግስጋሴ የምናደርግበት ትግል እንዲሆን መጣር አለብን። በተናጠል በግለሰብና በየራሱ ድርጅት ለየብቻ የሚደረገው ትግል፤ ግስጋሴው አመርቂ እንዳልሆነ ተረድተናል። ስለዚህ አንድ የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ መሥርተን፤ ባንድነት መታገል አለብን።
ይህ ጥሪ፤ ብዙ የትግል ልምድ ላካበቱትና ለአዲስ ታጋዮች፣ ከፍተኛ ትምህርት ላላቸውና የመማር ዕድሉ ላላጋጠማቸው፣ የላቀ ወታደራዊ ሹመት ላላቸውና ውትድርና ላልቀመሱት፣ ለሁሉም “ኢትዮጵያዊ ነኝ፣ እኔም ያገባኛል!” ለሚሉ ግለሰቦችና በድርጅት የተሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያን ነው። የሌሎች ቆርጦ አለመነሳት ራሳቸውን እንዲያገሉ ላደረጋቸው፣ በትግሉ መጓተት ተስፋቸው ለመነመነ፣ የኛን ፖለቲካ ጠልተው ዓይኖቻቸውን ለጊዜው ለጨፈኑ ኢትዮጵያዊያንም ጭምር ነው።
በርግጥ መሰባሰብ ቀናና ቀላል ጉዳይ አይደለም። “ማን ጠራው?” እና “መቼና የት ተጠራ?” የሚሉት ከጥሪው የበለጠ ትክረት ባገኙበት ወቅት፣ ጥሪ ትርጉሙ የጎንዮሽ በተጣለበት ወቅት፤ ተቀባይነት የሚያገኝ ጥሪ ማስተላለፍ ቀላል አይደለም። ሆኖም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሀቅ ከመቼውም በላይ አጣብቂኝ ውስጥ የገባ በመሆኑ፤ የማይቻል የሚባለውን ሁሉ ለማስቻል፤ ጊዜ የምንሻማው ሆኖ፤ ሁሉንም እንድናደርግ ግድ ብሎናል። ይህ የቅንጦት ምርጫችን አይደለም። መሯሯጫ ሰዓት ላይ ነው ያለነው። ስለዚህ፤ የመሰባሰብ ሂደታችንን ከመቼውም ባፈጠነ መንገድ ማራመዱ ግድ ሆኗል። ተግባራዊ ሆነን እስካልተገኘን ድረስ፤ ጊዜ ራሱ መፍትሔ ይዞ የሚመጣበት መንገድ የለውም። እናም ይኼን ቀጥተኛ የመሰባሰቢያ ማመልከቻ፤ ለርስዎ፣ እርስዎን ለመሰሉ ታጋይ ኢትዮጵያዊያንና ለታጋይ ድርጅቶች እንድልክ ኢትዮጵያዊነቴ አስገድዶኛል። እንደሚቀበሉት ሙሉ እምነቴ ነው።
ውድ ታጋይ ኢትዮጵያዊ፤
በሀገር ውስጥም ሆነ በስደት፤ የሀገራችን ሁኔታ በያለንበት ሁላችንንም የአእምሮ ዕረፍት ነስቶናል። እስከዛሬ በግልዎ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት መስዋዕትነት እየከፈሉ ሲታገሉ ነበር። የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅም የትግሉን መቀጠል ያለጥርጥር ግድ ይለዋልና፤ አሁንም ትግልዎ ተገቢ ነው።መታገል ግን፤ ከግብ መድረሻ እንጂ ራሱ ግብ አይደለም። ስለዚህ ለምን የሚታገሉለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ከግብ እንዳልደረሰ መፈተሹን እርስዎ ከኔ የበለጠ እያሰቡበት እንደሆነ ተቀብዬ፤ ትግሉ የኢትዮጵያዊያን በሙሉ በመሆኑ፤ እርስዎ ያለሙት ግብ አለመገኘት ለኔም በግሌ የጉዳዩ ባለቤት በመሆኔ፤ አሳስቦኛል። እናም በታጋዮቹ በሁላችን፤ በግለሰብ ባለነውም ሆነ በድርጅት በተሰባሰቡት መካከል ያለውን፤ የምናልመውን የጋራ ግብ በማውጣት፤ በአንድነት የምንሠራበትን መንገድ በዚህ መልዕክቴ ዘርዝሬያሁ። ምርጫ የሌለበት ግዴታ ከፊታችን ላይ ተጋርጧልና፤ አቤት! አለሁ! በማለት በመደጋገፍ ሀገር አድን የሆነ ትግል እንድናደርግ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። ይህ ጊዜ የሚሠጥ ጉዳይ አይደለም። ግዴታችን ነው። እንዴት ይጀመራል እና ማን ይጀምረው በሚል ጥያቄ መጓተቱ ይቅርብን። ይኼው ጀምሬዋለሁ። በኔ በኩል መገናኛ ኢሜሌ ይኸው ነው። (eske.meche@yahoo.com) እርስዎና ሌሎች በሚሠጡት መልስ እንቀጥላለን። አብረን ጀማሪዎች እንሆናለን። ኢትዮጵያዊ ግዴታችንንም እንወጣለን። ለወገንና ለሀገር እንደርሳለን።
የታወቀ ነው፤ መሰባሰብ ቀላል ጉዳይ አይደለም። የሚቻልና ቀላል ቢሆን ኖሮማ፤ ካሁን በፊት ይተገበር ነበር። አልተደረገም። አይደረግም ማለት ግን አይደለም። የአሁኑ የማይቻል የተባለ ቀውጢ ሰዓት የሚጠይቀው ደግሞ፤ የማይቻል የተባለውን ማድረግን ነው። ስለዚህ የማይቻል የሚባል መፍትሔ ማቅረብ አለብን። ተቻለም አልተቻለም፤ በአሁኑ ሰዓት ለማንኛውም ጥረት አጥር አናበጅለትም። ካለም ጥሰን እንቀጥላለን። ይህ አይደረግም! አይቻልም! ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች በፍጹም አያደርጉትም! ቢባልም፤ እኔ ይቻላል፤ ይደረጋል፤ በማለት ተነስቻለሁ። እርስዎም እንደሚተባበሩኝ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለኝም።
ጥሪዬ  በአንድነት ተሰባስበን የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ እንድንመሠርት ነው። ይኼንን በመነጋገር ገሃድ እናደርገዋለን። በመጀመሪያ ይህን ንቅናቄ ፈላጊዎች መገናኘት አለብን። ከዚህ በምን መንገድና እንዴት የሚለውን ተመካክረን እንወስነዋለን። በዚሁ የኢሜል አድራሻ፤ (eske.meche@yahoo.com ) መልስ ይሥጡኝና ወደፊት መሄዱን አብረን እንጀምር።
በምንም በኩል የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የሆነውን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ አንኳሰንና አሳንሰን ማየት የለብንም። በምኞትም ይወድቃል ብለን መጠበቅ የለብንም። ያ ከሆነ ደግሞ የበለጠ አደጋ ሊከተል እንደሚችል ለርስዎ እኔ አስገንዛቢ ልሆን አይቃጣኝም። ከዚያ ለመዳን፤ በግልጽ በአንድነት መነሳት አለብን። ይህ ቡድን በምንም መንገድ ወዶ ሥልጣኑን እንደማይለቅ ሁሉ፤ የታጋዩ ክፍል አይሎ ትግሉ ሲጠነክር፤ ያለ የሌለ ጉልበቱን በሕዝቡ ላይ እንደሚያፈሰው መገንዘብ አለብን። እናም በትክክል የዚህን ቡድን ጥንካሬና ድክመት ማወቅና ትግሉም በሚያመች መንገድ መመራት አለበት። ይህ ትግል ከግቡ የሚደርሰው፤ በአንድነት ተሰባስበን፣ የአንድነት ራዕይ ኖሮን፤ በአንድ ጠንካራ ድርጅት ሥር፤ በኢትዮጵያዊነታችን ለኢትዮጵያዊነታችን ስንታገል ብቻ ነው።
መሰባሰብ አስፈላጊነቱን ተቀብለን፤ ለመሰባሰብ ለሚደረጉ ጥረቶች ግን እጃችንን አጣጥፈን መቀመጥ፤ ታጋይነት አይደለም። መሰባሰቡ ዋና ጉዳያችን ነው ካሉ፣ መሰባሰቡ ለትግሉ መደፊት መቀጠል ወሳኝ ነው ካሉ፣ እስከዛሬ የከፈሉት መስዋዕትነት ዋጋ እንዲኖረው ከፈለጉ፤ የመሰባሰቢያ ጊዜው አሁን ነው። ለትግሉ ያለዎት ጥንካሬ፣ ለስኬቱ ያለዎት ቆራጥነት፣ የታጋይነትዎ ብስለት የሚለካው አሁን ነው። አሁን የትም ማምለጫ የሌለው ትንቅንቅ ውስጥ ነን። በልባችን የያዝነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያቸናፊነት እምነት፤ በሕይወታችን ላይ ሙሉ ቁጥጥሩን ይውሰድ። ቀኑ ሌት፣ ሌቱ ቀን መሆናቸው ትርጉም ይጡ። የሕዝቡን ድል አንግተን፤ ወደፊት መሄድ ብቻ ምርጫ የሌለው ጎዳናችን ይሁን።
የመሰባሰቢያ ዕሴቶቻችን፤
አንደኛ፤    የኢትዮጵያ ሕዝብ በገዥዎቹ ከፍተኛ በደል በየጊዜው ደርሶበታል። በዛም አነሰም ሕዝቡ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል፤ በደል ደርሶበታል። አንደኛው ክፍል ከሌለው የበለጠ በደል ደርሶበታል። ይህ የታሪክ ሀቅ ነው። ማንም ሊክደው አይችልም። ሆኖም ግን ይህ በደል የደረስውና በመድረስ ላይ ያለው፤ በገዥዎቹ የግል የሥልጣን ጥማት እንጂ፤ አንደኛው የሀገራችን ክፍል ሌላኛውን የሀገራችን ክፍል ሊወርና ሊያጠቃ በዶለተበት ሂደት አይደለም። ስለዚህ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተከታታይ ገዥዎች ተጠቂ መሆኑን መቀበል አለብን። አሁንም ወደፊት ስንመለከት፤ የኢትዮጵያን ገዥዎችና ፍላጎት ደምስሰን፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነትና ሉዓላዊነት የትግላችን መሠረታዊ ዕሴት አድርገን መነሳት ነው። ካሁን በኋላ ሕዝቡ ወሳኝነቱና የበላይነቱ ከጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቋሚ መብቱ መሆኑን ማረጋገጥ አለብን።
ሁለተኛ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ስትሰፋና ስትጠብ ለዘመናት ኖራለች። በዚህ እንኮራለን። ታሪካችን ሙሉ ለሙሉ ትክክለኛ ተግባራትን ብቻ ያስመዘገበ ነው ብሎ የሚከራከር የዋህ ነው። ገዢዎች፤ ከመንደር እስከ በዙፋኑ ላይ የተቀመጡ ሁሉ፤ ሕዝቡን ባጠቃላይ፤ እስር በርሳቸው ደግሞ በተለይ፤ ሲጣሉና ሲዋጉ፣ አልፎ ተርፎም አንዳንዶቹ ለሥልጣን ሲሉ ከባዕድ እያበሩ የሀገራቸውን መሪዎች መዋጋታቸው ሀቅ ነው። ይህ ሁሉ ታዲያ የታሪካችን አካል ነው። ልንሸመጥጥና ልንክደው አንችልም። በገዥዎቹ ፍላጎት ተመርቶ አንደኛው ክፍል ሌላውን አጥቅቷል። በተመሳሳይ መንገድ ደግሞ በተራው ሌላው ብድሩን መልሷል። ይህም ታሪካችን ነው። ይህ ሁሉ ተደምሮ ነው የአሁኗ፣ የሀገራችን፣ የኢትዮጵያ ታሪክ። ከዚህ የምንማረው፤ ማንም ገዥ ሆኖ ሰነበተ ማንም፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ አንድ ሀገር ሆና፤ ደካማም ይሁን ጠንካራ በየወቅቱ አንድ መንግሥት ኖሯት፣ ለረጅም ጊዜ እንደቆየችው ሁሉ፤ አሁንም በአንድነቷና በአንድ ሀገርነቷ መቀጠሏን ማረጋገጥ አለብን።
ሶስተኛ፤ በሰዎች መካከል ላለ ማናቸውም ግንኙነት፤ በመካከላቸው የሚያስተሳስራቸው፤ በጋር የሚስማሙበት የመተባበሪያ ሕጋቸው ነው። ይህ ሕግ ነው በመካከላቸው የሚኖረውን አብሮ የመቀጠል ሂደት የሚወስነው። እናም ሕጉ ካልተከበረ፤ በመካከላቸው ያለው አብሮነት ትክክለኛ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ በመተማመን አብሮነታቸው እንዲቀጥል፤ ሕጉን ማስከበሩ ግዴታ ነው። ይህ በሁለት ሰዎች መካከልም ሆነ በአንድ ሀገር ሕዝብ መካከል አንድ ነው። ሕጉን፤ ደንብ፣ ስነ ሥርዓት፣ በማለት እንደያስፈላጊ ቦታው ስም ሊሠጠው ይችላል። ሆኖም ግን መሠረታዊ ይዘቱ፤ በሰዎች መካከል፣ አብሮነታቸውን የሚያስረው፤ በመካከላቸው ያለው ሕግ መሆኑ ነው። ስለዚህ በሕግ መገዛትና የሕጉ መከበር፣ ግዴታ መሆኑን መቀበል አለብን። እናም በሀገራችን የሕግ የበላይነት መስፈን መሳኝ መሆኑን ማረጋገጥ አለብን።
አራተኛ፤ በአንድ ሀገር የሚኖሩ ሰዎች፤ የሀገራቸው ዜጎች በመሆናቸው፤ እያንዳንዳቸው እኩል የሀገሪቱ ባለቤቶች ናቸው። ለዚህም፤ የሀገሪቱ ሕግ ሁሉንም በእኩልነት መመልከት አለበት። ግዴታቸውም ሆነ መብታቸው በዜግነታቸው ላይ የተመሠረተ ነው። የሀገሪቱ ዜጎች በሙሉ፤ እኩል የሆነ መብትና ግዴታ አላቸው። ስለዚህ ከዜግነታቸው የሚመነጨው የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብታቸው፤ ያላንዳች መሰናክል መከበር አለበት። በአንድ መንገድ ወይንም በሌላ፤ ሁለት ወይንም አስር ሆነው እኛ ስለተደራጀን የበለጠ መብት ይኑረን የሚባልበት ጨዋታ አይደለም። ማንም ግለሰብ፤ የሀገሪቱ ዜግነት እስካለው ድረስ፤ ሙሉ መብቱ የተከበረ ነው። ይህ፤ ለሁሉም፤ የትም ቦታ የሚሠራ፤ የኢትዮጵያዊ ዜግነት መብታቸው ነው። እናም የግለሰብ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበራቸውን ማረጋገጥ አለብን።
በነዚህ አራት ነጥቦች ዙሪያ፤ ሁላችን ለንቅናቄው እንሰባሰብ። እኒህ መታገያችን ናቸው። እኒህ የኢትዮጵያዊያን መታገያ ዕሴቶቻችን ናቸው። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ፤ እኒህም ሊቀየሩ፣ ሊያንሱ፣ ሊበዙ፣ ሊቀየጡ ይችላሉ። ይኼን በአንድነት በምንሰባሰብበት ጊዜ እንወስነዋለን። አሁን ለመጀመር መንደርደሪያችን እናድርገው። ይህን ወራሪ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ልንጥለው የምንችለው፤ በኢትዮጵያዊነት ብቻ ነው። እሱ ፀረ-ኢትዮጵያዊያን ነው፤ እኛ ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ነን። የምንታገለው ለኢትዮጵያዊነታችን ነው። በዚህ ተደራጅተን መታገል አለብን። የምንደራጀው በየኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ ነው።
ይህ ትግል ወደፊት ሊሄድ የሚችለው፤ ይህ የምንመሠርተው ደርጅት፣ አደረጃጀቱና የአባላቱ የትግል ፍላጎት ከትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ድርጅት ጥንካሬና ጥረት ልቆ ሲገኝ ብቻ ነው። ይህ ትግላችን፤ የተለዩ አርቆ አሳቢ መሪዎችን ይጠይቃል። አሁን በየድርጅቶች የመሪነቱን ኃላፊነት የጨበጡት ሁሉ፤ ከድርጅቶቻቸው በላይ ሀገራቸውንና የሕዝቡን ትግል ተሸክመው፤ ለዚህ ትግል ድልና ለዚህ ትግል ድል ብቻ ድርጅቶቻቸውን ተገዥ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ነገና ተነገ ወዲያ የሚመጣውን አስቀድመው በማየት፤ በሥራቸው የተሰባሰቡ ታጋዮችን በትክክለኛው መንገድ ሲያዘጋጇቸውና ሲመሯቸው ነው ትግሉ ወደፊት የሚሄደው። በትግሉ ሂደት፤ እንደሁኔታው መለዋወጥ፤ እነሱም ራሳቸውን እና ደርጅቶቻቸውን፤ ትግሉ በሚጠይቀው መሠረት ማሳደግና ማስተካከል አለባቸው። መሰባሰቡና በአንድነት ሁላችን መታገላችን የዕለቱ ጥያቄ ነው።
ለትግሉ የምንሰለፍንበት የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ የሚጠነክረው፤ በኢትዮጵያዊነታችን አምነንና ሀገራችን ባለችበት አሳዛኝ ሁኔታ ተቆርቁረን፤ የሀገራችንን ነፃነትና ለሕዝቡ ነፃነት የሚሆነውን መፍትሔ በተለያዬ መልክ የምንመለከት ሁሉ፤ በአንድነት ተቀምጠን፤ በመካከላችን ባለው ስምምነት፤ የጋራ የሆነ አቋማችንን ለድርጅቱ ምሰሶ ስናደርገው ነው። አንድ አመለካከት ያለው አንድ ድርጅት ብቻውን ሥልጣን ላይ ባሁኑ ሰዓት ከወጣ፤ መልሰን መደንከር ነው።
ይኼን የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ የሚመሩት፤ ከግለሰብ ማንነታቸው በላይ፤ ኢትዮጵያዊያንን እና ኢትዮጵያን ያስቀደሙና ብቃታቸውንና ችሎታቸውን ያለምንም ስስት ለትግሉ የሚያውሉ መሆን አለባቸው። የትግሉ ስኬት በነዚህ መሪዎች ችሎታና ጥረት ይወሰናል። ከመጀመሪያው በሥራቸው ተተኪ የሚሆኑትን አዘጋጅተው፤ ቀጣይነትን የሚያስተማምኑ መሆን አለባቸው። የሀገሪቱን ምርጥ ታጋይና አታጋይ መሪዎችን፤ ትግሉን ወደፊት የሚገፉ ወጣት ታጋዮችን ማሰባሰብ አለባቸው። እኒህ ደግሞ፤ አሁን በትግሉ በተሠማሩ ድርጅቶችና በትግሉ ዙሪያ ባሉ ግለሰቦች መካከል ነው የሚገኙት። ሌላ ከሰማይ የሚወርዱ መሪዎች የሉንም። እናም በትግሉ ዙሪያ ያለነው በሙሉ መሰባሰብ አለብን።
ባሁኑ ሰዓት ስለያንዳንዱ ሀገራዊ ጉዳዮች ባንድ ላይ መጨነቅ የለብንም። የጉዳዮች ቅደም ተከተል ማድረግ አለብን። መጀመሪያ ሀገራችን እንደመዥገር እየመጠመጠ ያለውን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ማስወገድ ነው። በሂደቱ በሀገር ቤት ያለውና ከሀገር ውጪ ያለው የታጋይ ክፍል በአንድነት የሽግግር መንግሥት ማቋቋምና ህዝቡ ሉዓላዊነቱ፣ ሀገራችን አንድነቷ፣ ሕግ የበላይነቱና የኢትዮጵያዊያን የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚከበሩበትን ሁኔታ ማዘጋጀት ነው። ከዚህ በተረፈ፤ የዓለም አቀፍ ስምምነቶች፣ ውሎችና ደንቦች ሊከበሩ የሚገባቸው፤ የኛን ጥቅም የሚያስጠብቁ ሆነው እስከተገኙ ድረስ ብቻ ነው። እኒህ መታሠሪያና መታነቂያ ገመድ ሆነው፤ አንገታችን እንድናስገባ የሚጠብቁ መሆን የለባቸውም። ታሪካችን ብዙ አስተምሮናል። እናም ማንኛውም ስምምነት፣ ውልና ደንብ፤ በዚህ መነፅር ይመረመራል።
አሁን ማድረግ ያለብን፤ ትክክለኛውን የትግል መስመር ተከትለን፤ ትክክለኛ የሆነ የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ መመሥረት ነው። ኢትዮጵያዊው ትግል፤ በሰላምም ሆነ በሌላ መንገድ በትክክለኛ እየተመራ አይደለም። ይኼ የሆነው፤ ታጋዮች ጠፍተው ሳይሆን፤ አንድነትን ያሰመረ የመታገያ ማዕከል በቦታው ኖሮ፤ ትግሉን አቀናጅቶ የሚመራ ንቅናቄ ባለመገኘቱ ነው። መሠረታዊ የሆነውን የትግሉን ምንነት በደንብ ተረድተን፤ ለዚሁ ትግል ተመጣጣኝ የሆነ ትብብርና ድርጅት ስለሌለን ነው። ትግሉን በትክክል ለመምራት ደግሞ፤ የአንድነት ትግል መሆኑን መረዳታችን፤ መቅደም ይገባዋል። እናም ይሄን የማራመድ ኃላፊነቱ አለብን። መሰባሰብ ይገባናል። ለዚህ የርስዎን መልስ እጠብቃለሁ። የርስዎን ሃሳብ እፈልጋለሁ። ይኼው የኔ የኢሜል አድራሻ፤ ( eske.meche@yahoo.com )
አክባሪዎ
አንዱ ዓለም ተፈራ

Friday, November 7, 2014

የመኢአድ አባላት በፀጥታ ሃይሎች መወሰድ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) የቀድሞ ዋና ጸሃፊ እና አባላት በጸጥታ ሃይሎች ተወስደው ያሉበት አለመታወቁን ፓርቲው አስታወቀ።የአቶ ተስፋዬ ታሪኩ በጸጥታ ሃይሎች ሲወሰዱ በቦታው ነበርኩ የሚሉት ባለቤታቸው ቤታቸው ሲፈተሽ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመያዛቸውን ተናግረዋል።

12.06.2013 DW Online Karten Basis Äthiopien Englisch
አቶ ተስፋዬ ታሪኩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ዋና ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል። በፖለቲካ ተሳትፏቸው በ1997 ዓ.ም. ጭምር ተደጋጋሚ እስር እና እንግልት ገጥሟቸዋል የሚባሉት አቶ ተስፋዬ ጥቅምት 28/ 2007 ዓ.ም. ከደጀን ከተማ በጸጥታ ሃይሎች ሲወሰዱ አጠገባቸው እንደነበሩ ባለቤታቸው ወ/ሮ መለሰች ዋሴ ይናገራሉ።
''ቤት ነበርኩኝ። ሰባት ሰዓት ላይ ገቡ ስምንት ሰዓት ላይ ቤት እንፈትሻለን አሉ። የፍርድ ቤት ወረቀት አላችሁ ወይ ስል የፍርድ ቤት ወረቀት የላቸውም። የፍርድ ቤት ወረቀት ከሌላችሁ ግን ቤቴን መበርበር አትችሉም ሲላቸው ለመማታት ሞከሩ። ከአካባቢው ፖሊሶች በመጥራት ፍተሻ ጀመሩ።ምንም ነገር አላገኙም። አስራ ሁለት ሰዓት ተኩል ከቤት ይዘውት ወጡ። ሶስት ሰዎች አሉ እኔ የማውቃቸው ሌሎቹን ግን አላውቃቸውም።''
ወ/ሮ መለሰች ዋሴ ባለቤታቸው በጸጥታ ሃይሎች ሲወሰዱ ለምርመራ መሆኑን እና እንደሚመልሷቸው እንደተነገራቸው ተነግሮኛል ብለዋል። ሆኖም ቤታቸው ካለ ፍርድ ቤት ማዘዣ የተፈተሸበትን፤ባለቤታቸው የተፈለጉበትን እንዲሁም የተወሰዱበትን ቦታ እንዳልተነገራቸው ተናግረዋል።
ወ/ሮ መለሰች ዋሴ ባለቤታቸውንና የሁለት ልጆቻቸውን አባት አቶ ተስፋዬ ታሪኩን ፍለጋ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ፕሬዝዳንት አቶ አበባው መሃሪ ከአቶ ተስፋዬ ታሪኩ በተጨማሪ ሶስት የፓርቲው አባላት በአማራ ክልል በጸጥታ ሃይሎች እንደተወሰዱ ይናገራሉ።
''ከደብረ ታቦር ሁለት አባሎቻችን ተይዘዋል። ከባህር ዳር መቶ አለቃ ጌታቸው ተይዟል። ደጀን አቶ ተስፋዬ ታሪኩ ተይዟል።ልናጣራ በየቦታው ዞረናል። ያሉበትን አላወቅንም። የመንግስት አካላትን ለመጠየቅ ሞክረን ነበረ ሃላፊነት የሚወስድ አካል ማግኘት አልቻልንም።
በዚህ ዘገባ የአማራ ክልል ፖሊስን ምላሽ ለማካተት ያደረግንው ጥረት አልተሳካም።የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ከአንድነት ለነጻነትና ለፍትህ ፓርቲ አንድነት ጋር የጀመረውን ውህደት ለመፈጸም እንዲያስችለው ጠቅላላ ጉባኤውን አርብ እና ቅዳሜ በአዲስ አበባ ያካሂዳል። የውህደት ሂደቱ ስምምነት ላይ የተደረሰበት ቢሆንም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ኮሚሽን ፓርቲው የጠቅላላ ጉባኤው አልተሟላም በሚል እንዳቆየው አይዘነጋም።
እሸቴ በቀለ
ሸዋዬ ለገሰ
Source: dw

የፌደራል ሚኒስቴር እና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ለቀረበባቸው ክስ መልስ እንዲሰጡ ታዘዙ



በ2005 ዓ.ም በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ይኖሩ የነበሩ የአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ህገ ወጥ የሆነ ማፈናቀል ተፈጽሞባቸዋል፣ ንብረታቸው ወድሟል በሚሉ እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ በሰማያዊ ፓርቲና በአንድነት ፓርቲ አሳሳቢነት በእነ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም እና በአቶ ዓለሙ ጌቤቦ ክስ የተመሰረተባቸው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ የቤኒሻንጉል ጉምዝ እና የመተከል ዞን ላይ የተመሰረተው ክስ ዛሬ ጥቅምት 28 ቀን 2007 ዓ.ም በልደታ የፌደራል ፍታብሄር ችሎት ቀጥሎ ውሏል፡፡
በዛሬው የፍረድ ቤት ውሎ ተከሳሾች የቀረበባቸው ክስ አግባብ እንዳልሆነ በማውሳት ክሱ እንዲነሳላቸው ጠይቀው የነበር ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ሳይቀበላቸው እንደቀረ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች ለጥር 15/2007 ዓ.ም በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ መልስ እንዲሰጡ አዝዟል፡፡
ክሱ የተመሰረተው ባለፈው ዓመት 2006 ዓ.ም መሆኑ የሚታወስ ሲሆን፣ የክሱ ይዘት ተብራርቶ መቅረቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹ተፈናቃዮች ወደ ቦታቸው ባስቸኳይ ይመለሱ፣ ለጠፋው ንብረትና ጉዳትም ካሳ ይሰጣቸው›› የሚል አቤቱታ መቅረቡንም ጉዳዩን የሚመሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡
የተፈጸመው የማፈናቀል ተግባር የኢትዮጵያን ህገ መንግስትም ሆነ ዓለም አቀፍ ህግጋትን የጣሰ ነው ያሉት ዶ/ር ያዕቆብ፣ አሁን የተመሰረተው ክስ ለውጤት ከበቃና ፍርድ ቤቱ ለተፈናቃዮች ከወሰነላቸው ከዚህ በፊት በተመሳሳይ በደል የደረሰባቸው ዜጎችም ፍትህ እንዲያገኙ በር የሚከፍት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

Wednesday, November 5, 2014

እነ ሀብታሙ አያሌው ለህዳር 2 ተቀጠሩ



በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 ቀን 2007 ዓ.ም ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዳንኤል ሺበሺ ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና በተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱ ሌሎች 5 ግለሰቦች ጠበቆቻቸው የሚያቀርቡትን የዋስትና ጥያቄ ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለህዳር 2 ቀን 2007ዓ.ም ከቀኑ 5 ቀጠሮ እንደሰጠ በስፍራው የተገኙት የፍኖተ ነፃነት ዘጋቢዎች አስታወቁ፡፡
ዛሬ ጠዋት ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡትን የእነሀብታሙ አያሌውን መዝገብ የተመለከተው ፍርድ ቤት ለህዳር 2 ቀጠሮ የሰጠው የተከሳሽጠበቆች ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ነው፡፡ የወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዳንኤል ሺበሺ ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ በክስ ቻርጁ ላይ የከሳሽ አቃቢህግ ስም ያለመቀሱንና የማስረጃ ዝርዝር መግለጫ ያለመኖሩን በመግለፅ “ደንበኞቼ ላይ የቀረበው ማስረጃ ስንት ገፅ እንደሆነ እንኳን አላውቅም” በማለት ለፍርድ ቤቱ አሳውቀዋል፡፡ የሌሎቹ ተከሳሾች ጠበቆችም ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ አቃቤህግ በበኩሉ “ማስረጃዎቹ በየጊዜው ስለሚጨምሩ ነው ያላካተትነው፡፡ ሆኖም ሁለት ገፅ መግለጫ አለ” ፍርድ ቤቱም አቃቤ ህግ የማስረጃ ዝርዝር መግለጫውን እንዲያካትት በማዘዝ ጠበቆቻቸው የሚያቀርቡትን የዋስትና ጥያቄ ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለህዳር 2 ቀን 2007ዓ.ም ከቀኑ 5 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡