Tuesday, September 8, 2015

አቃቤ ህግ በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን መዝገብ 6 ምስክሮችን አሰማ

• ‹‹አቃቤ ህግ አዛዥ ናዛዥ ሆኗል›› ጠበቃው
• ‹‹አርበኛው ግንባር የሚገኘው ሻዕቢያ ነው›› ምስክር
የፌደራል አቃቤ ህግ ዛሬ ጳግሜ 3/2007 ዓ.ም በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ ስር የሚገኙ 6ኛ ተከሳሽ ወርቅዬ ምስጋናው፣ 7ኛ ተከሳሽ አማረ መስፍን፣ 9ኛ ተከሳሽ ቢሆነኝ አለነ እና 12ኛ ተከሳሽ አትርሳው አስቻለው ላይ 6 ምስክሮችን አሰምቷል፡፡ አቃቤ ህግ በዛሬው ዕለት 13 ምስክሮችን ያቀረበ ቢሆንም ሁሉንም ሳያስመሰክር ቀርቷል፡፡ ሌሎች 7 ምስክሮች እንዳሉት ቢገልፅም ‹‹ገና ከጎንደር የሚመጡ ስለሆነና ምን እንደሚሉ ስለማናውቅ ማቅረብ አልቻልንም›› በሚል ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ አቃቤ ህግ 13ቱንም ምስክሮች ማን ላይ ምስክርነት እንደሚሰጡ ባለመመደቡ ጠበቃዎቹ ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡ አቃቤ ህግ 13ቱ ምስክሮች መካከል ማን ላይ መመስከር እንዳለባቸው የመደባቸው 6ቱ ብቻ በመሆናቸው ሌሎቹን ከሰዓት እንዲያስመሰክር በጠበቃዎቹ ቢጠየቅም ሳያስመሰክር ቀርቷል፡፡
በችሎቱ መርማሪዎቹ የተገኙ በመሆኑ ተከሳሾቹ በመቆም ተቃውሟቸውን ገልፀዋል፡፡ ከተከሳሾቹ መካከል 15ኛ ተከሳሽ አቶ አግባው ሰጠኝ ‹‹ማዕከላዊ ውስጥ ማንነታችን ሲያዋርዱና ሲገርፉን የነበሩት መርማሪዎች በዚህ ችሎት መገኘት የለባቸውም›› ሲል ተቃውሟል፡፡ የተከሳሾቹ ጠበቃዎችም መርማሪዎቹ በችሎት መገኘታቸው ደንበኞቻቸውንና ምስክሮች ላይ የስነ ልቦና ጫና እንደሚፈጥሩ በመግለፅ ከችሎቱ እንዲወጡ ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ቅሬታውን ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
በ12ኛ ተከሳሽ አቶ አትርሳው አስቻለው ላይ የመሰከረው 1ኛ ምስክር ተከሳሹ ለየትኛው ቡድን እንደመለመለው ሲጠየቅ ‹‹ለአርበኛው ግንባር፣ ለአርበኛው ግንባር ግንቦት ሰባት፣ ለግንቦት ሰባት፣ አርበኛው ግንባር ለግንቦት ሰባት›› ሲል የተለያዩ ስሞችን ተናግሯል፡፡ በተመሳሳይ 2ኛ ምስክር ተከሳሹ ለየትኛው ቡድን እንደመለመለው ሲጠየቅ ‹‹ለኤርትራ መንግስት›› ብሏል፡፡ ወደ ኤርትራ እንዲሄድ የተጠየቀበትን ምክንያትም ምን እንደነበር ሲጠየቅ ‹‹ኤርትራ ውስጥ የተሻሻለና ዴሞክራሲያዊ መንግስት አለ ተብለን ነው፡፡ ተመልሰን ይህን መንግስት እንድጥል ነው፡፡›› ሲል መስክሯል፡፡ ሁለቱም ምስክሮች ተመለመልንበት ያሉትን ቀን፣ ጊዜና፣ ተደዋወልንባቸው ያሏቸውን ስልኮችና ሌሎች ዝርዝር ጥያቄዎች ‹‹አናስታውሳቸውም›› ብለው አልፈዋቸዋል፡፡
በተመሳሳይ 12ኛ ተከሳሽ ጎንደር 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለ ምንም ተፅዕኖ ቃሉን ሲሰጥ አይቻለሁ ያለው ሶስተኛ ምስክር ተከሳሹን በአካል እንዲያሳይ ሲጠየቅ 7ኛ እና 10ኛ ተከሳሽን ‹‹ከሁለቱ አንዱ›› ብሎ በአማራጭነት አሳይቷል፡፡ መርማሪዎች ምስክርነት ላይ የነበሩትን ምስክሮችን ቃል በማየት በቀጣይነት ለሚመሰክሩት ከችሎቱ እየወጡ መረጃ እየሰጡና እየመከሩ ነው በሚል ተከሳሾቹና ጠበቃዎቻቸው ቅሬታ አቅርበዋል፡፡ ይሁንና ፍርድ ቤቱ ሲወጡ ሲገቡ የነበሩትን መርማሪዎች ላይ ምንም ሳይል አልፏል፡፡ መርማሪዎች ለምስክሮች መረጃ እያቀበሉና እየመከሩ ነው የሚል ስጋት ያደረባቸው ተከሳሾች 3ኛ ምስክር 12ኛ ተከሳሽን ሳያውቀው በመቅረቱ መርማሪዎች ለሚቀጥለው ምስክር በምልክት ይነግሩታል በሚል 12ኛ ተከሳሽ ቦታውን ቀይሮ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ 4ኛ ምስክር ወደ ችሎት ገብቶ 12ኛ ተከሳሽን እንዲያሳይ ሲጠየቅም 12ኛ ተከሳሽን ቦታ ቀይሮ የተቀመጠውን 10ኛ ተከሳሽን በ12ኛ ተከሳሽ ስም በመጥራት ‹‹እሱን ነው የማውቀው›› በሚል ጠቁሟል፡፡
5ኛ ምስክር 9ኛ ተከሳሽ አቶ ቢሆነኝ አለነ ለኮንስትራክሽን የስራ ልምድ እንዲፅፍለት ሲጠይቃቸው ኤርትራው ውስጥ የተሻለ እንድል እንዳለ በመግለፅ ወደ ኤርትራ ለመላክ እንደመለመለው መስክሯል፡፡ ኤርትራ ውስጥ አለ የተባለው መልካም አጋጣሚ ምን እንደሆነ የተጠየቀው ምስክር ‹‹ብዙ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ስላለ ትጠቀማለህ ተብዬ ነው፡፡›› ብሏል፡፡ በመስቀለኛ ጥያቄ አርበኛው ግንባርን ለመቀላቀል ከአቃቤ ህግ በቀረበለት ጥያቄም ያመነው ምስክሩ፤ አርበኛው ግንባር የት እንደሚገኝ ሲጠየቅ ‹‹ሻዕቢያ›› ብሏል፡፡ ቀጥሎም ‹‹ሻዕቢያና አርበኛው ግንባር አንድ ናቸው›› ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡
በ2005 ዓ.ም በማያውቀው ወንጀል ታስሮ እንደነበር የገለፀው 6ኛ ምስክር ይህንን በደሉን ለ6ኛ ተከሳሽ ወርቅዬ ምስጋናው እንዲሁም ለ7ኛ ተከሳሽ አማረ መስፍን አማክሯቸው ሁለቱ ተከሳሾች ኤርትራ ከሚገኝ ሰው ጋር በስልክ እንዳገኙት ገልፆአል፡፡ የተከሳሾቹ ጠበቃ ምስክሩ በእስር ላይ በደረሰባቸው ችግር ምክንያት በግዳጅ ለምስክርነት ቀርበው እንደሆነ ጥያቄ ቢያቀርቡም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ ፍርድ ቤቱ በአቃቤ ህግና በጠበቃዎች መካከል በነበረው ክርክር ለአቃቤ ህግ በተደጋጋሚ የበየኑ ሲሆን የተከሳሾቹ ጠበቃዎች ለአቃቤ ህግ የተለየ መብት ተሰጥቶታል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡
አቃቤ ህግ ካሰማቸው በተጨማሪ ከሰዓት ይመሰክራሉ ተብለው የነበሩትን ምስክሮች ማን በማን ላይ እንደሚመሰክር እንዲገልፅ 16ቱን ተከሳሾች ወክለው የቀረቡት 4 ጠበቆች ጥያቄ ቢያቀርቡም አቃቤ ህግ ‹‹አንዱ መቅረብ ይችላል፡፡ ከሌሎቹ ጋር ግን ገና አልተነጋገርንም!›› በሚል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ሆኖም አንዱም እንዲመሰክር ሲጠየቅም ከሌሎቹ ጋርም ተነጋግረው ነገ እንዲያቀርብ እንዲፈቀድለት በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ ፈቅዶለታል፡፡ ከተከሳሾቹ ጠበቃ መካከል አንዱም ‹‹አቃቤ ህግ የተለየ መብት ተሰጥቶታል፡፡ አዛዥ ናዛዥ ሆኗል፡፡ ከፈለገ ዛሬ ያቅርብ፡፡ ደንበኞቻችን በእስር ቤት እየተጉላሉ ነው›› ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡ ቀሪዎቹ ጠበቆችም አቃቤ ህግ አሉኝ የሚላቸው ምስክሮች አሰምቶ ደንበኞቻቸው የተፋጠነ ፍርድ እንዲያገኙ ጠይቀዋል፡፡ ሆኖም ፍርድ ቤቱ የጠበቃዎችን አቤቱታ ሳይቀበሉት ቀርተዋል፡፡ አቃቤ ህግ ነገ ጳግሜ 4/2007 ዓ.ም በቀሩት ተከሳሾች ላይ 14ት ምስክሮችን ያሰማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Monday, September 7, 2015

Eritrea warns of Ethiopia war 'sabre-rattling'

Nairobi (AFP) - Eritrea has accused arch-rival Ethiopia of "sabre-rattling" and of threatening to invade, with the neighbours still in a tense standoff following a 1998-2000 border war.  
Asmara's Ministry of Information said in a statement that war-like rhetoric from Ethiopia's main party in the ruling coalition -- the Tigrayan People's Liberation Front (TPLF) -- had increased. 
Eritrea, which broke away from Ethiopia in 1991 after a brutal 30-year independence struggle, remains on an effective war-footing with Addis Ababa after a return to war in 1998. 
"The TPLF's sabre-rattling has been a common staple throughout winter. And this has been ratcheted up in the past few weeks," said the information ministry statement, released Monday. 
"The TPLF regime is resorting to tactics of covert intimidation to dissuade various circles from associating with Eritrea. It has gone beyond these hints to openly assert that, 'it has secured a green-light from the United States to unleash war against Eritrea." 
There was no immediate reaction from Ethiopia, but Addis Ababa has previously dismissed such statements as propaganda. 
Eritrea is struggling to stem a flood of refugees from its borders to Europe, an exodus attributed to gross human rights violations in the hermit state. 
Eritreans make up the third largest number of refugees trying to reach Europe, after Syrians and Afghans. 
Asmara however says its controversial policy of decades-long national service -- a key reason some 5,000 people flee each month -- is due to threats from Ethiopia. 
But Asmara said its progress had sparked "frustration bordering on insanity in the camp of the TPLF and its key sponsors." 

ኤርትራ ኢትዮጵያን አስጠነቀቀች

ጷግሜን ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኤኤፍፒ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በመጥቀስ እንደዘገበው፣ የኢህአዴግ መንግስት በኤርትራ ላይ የሚያሰማው የጦርነት ዛቻና አገሪቱን እወራለሁ እያለ የሚያሰማው መግለጫ ጨምሯል። የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት /ህወሃት በተለየ ሁኔታ በኤርትራ ላይ ዛቻ እያሰማ ነው። በክረምቱ ወር ይሰማ የነበረው ፉከራ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ተጠናክሮ መቀጠሉን የማስታወቂያ ሚኒስቴሩ ገልጿል። የህወሃት አገዛዝ ኤርትራን እንዲወር ከአሜሪካ ፈቃድ አግኝቻለሁ እያለ በመናገር ላይ መሆኑን የገለጸው የኤርትራ መንግስት፣ በተለይም ከኤርትራ ጋር ግንኙነት አላቸው ብሎ የሚጠረጥራቸውን ሃይሎች ለማሸማቀቅ እየጣረ መሆኑን ገልጿል። ካለፉት ጥቂት ወራት ጀምሮ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ሃይሎች በትግራይና በአማራ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። የተቃዋሚ ሃይሎች ሃይላቸውን እያጠናከሩ መምጣታቸው፣ ገዢውን ፓርቲ ስጋት ላይ ጥሎታል። በሌላ በኩል የኢህአዴግ ጉባኤ የግንባሩን ችግር አባባሰው እንጅ አልፈታውም ተባለ ሰሞኑን በመቀሌ የተካሄደው የኢህአዴግ 10ኛ ጉባኤ የድርጅቱን ችግር አባባሰው እንጅ አልፈታውም ሲሉ አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የፓርቲው አባል ተናገሩ። የአመራር አባሉ እንዳሉት፣ ድርጅቱ " በዚህ ሁኔታ መቀጠል አንችልም በሚሉትና በጥንታዊው መንገድ እንጓዝ በሚሉት መካከል በግልጽ ለሁለት ተከፍሏል። ክፍፍሉ በጉባኤው ወቅት በደንብ ቢንጸባረቅም፣ ከጉባኤው በሁዋላም በግልጽ ፈጦ እየወጣ ነው። ነባሩ አመራር "የኢህአዴግ አካሄድ እየተበረዘ ነው" በሚል የቀድሞ ተሰሚነቱን ለማረጋገጥ እየሞከረ ሲሆን፣ አዲሱ አባል ደግሞ የእስከዛሬው አካሄድ ግንባሩን በስልጣን ላይ ለረጅም ጊዜ አያስቀጥለውም በማለት የተወሰኑ ፖለቲካዊ ለውጦች እንዲኖሩ እየጠየቀ ነው። ከአመት በፊት ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር የተደረገው ውይይት አዲሱ የኢህአዴግ አመራር " በዚህ ሁኔታ መጓዝ የለብንም" የሚል አቋም እንዲይዝ አድርጎታል የሚሉት አባሉ፣ በድርጀቱ ውስጥ ለሚታየው ተስፋ መቁረጥ ዋነኛው መነሻም ይህ ነው ይላሉ። አዲሱ ትውልድ ከስርአቱ ጋር አለመገናኘቱ በይበልጥ የታወቀው ታዳጊ ተማሪዎች ያነሱዋቸው የነበሩት ጥያቄዎች ናቸው የሚሉት አባሉ፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የውስጥ የድርጅት ፍትጊያው እንደቀጠለ ነበር ሲል ያስታውሳሉ። የመቀሌው ጉባኤ የችግር መስሚያ እንጅ ለችግሮች መፍትሄ የሰጠ አለመሆኑን የገለጹት አባሉ፣ በመጨረሻ ላይ የተሰጠው ውሳኔም ግንባሩ ነባር አመራሮችንም አዲሱን አመራርም ላለማስከፋት፣ ችግሩን አድበስብሶ ማለፍ ነበር ብለዋል። ግንባሩ መሰረታዊ የሆነ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል መሪ እንደሌለውም ይገልጻሉ። በአባይ ወልዱ የሚመራው ህወሃት ድርጅቱ ሳይበረዝ እንዲቀጥል ይፈልጋል። ይህንኑ አቋም ከሞላ ጎደል የመለስ ዜናዊ ወገን ተደርገው የሚታወቁት እነ አቶ በረከትም ይደግፉታል።

Source: ethsat

ለአጠቃላይ ለ36ተኛ ጊዜ ለብይን ደሞ ለ4ተኛ ጊዜ ተቀጥሮ የነበረው የዞን9 ጦማርያን ጉዳይ በድጋሚ ለመስከረም 27 ተቀጠረ።

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለዛሬ በተደጋጋሚ የተላለፈው የብይን ጥበቃ በድጋሚ ዳኞች አልተሟሉም በሚል ሰበብ ለ37ተኛ ጊዜ ተቀጥሯል።
በዳኞች አለመሟላት የተነሳ ችሎቱን ማስቻል አልችልም ብለው በቢሮ ተከሳሾችን እና ጠበቆችን የጠሩት ዳኛ ዘሪሁን ብይኑ ቢሰራም ለማሳወቅ ሁሉም ዳኞች መገኘት ስላለባቸው ለመስከረም 27 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተናል ብለዋል ።
ተለዋጭ ቀጠሮ ተከሳሾችን ቤተሰቦችን እና ውሳኔውን ሲጠብቁ የነበሩ ብዙ አጋሮችን በከፍተኛ ደረጃ ያስከፋ ነበር ።
ከአንድ ወር በኃላ በመደበኛው የፍርድ ቤት መከፈቻ የተቀጠረው ችሎት ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ ይሰናበቱ ወይስ ይከላከሉ የሚለውን ውሳኔ ያነባል ተብሎ ይጠበቃል።
የዞን9 ማስታወሻ
በአሳፋሪው የፍትህ ስርአትና በስራ አስፈፃሚው በሚዘወሩት ዳኞች እንደተከሳሽም ሆነ እንደአገር ማፈራችንን እያሳወቅን ይህ በውጤታማ እና ሰላማዊ ወጣቶች ህይወት ላይ መቀለድ፣ በታሪክም ሆነ በወደፊትዋ ፍትሃዊ ኢትዮጲያ ፊት የዳኞችን አንገት የሚያስደፋ ተከሳሾችን ደሞ የሚያኮራ ተግባር ሆኖ እንደሚታወስ በእርግጠኝነት እንናገራለን።
የዞን9 ጦማርያን በአምባገነን አገዛዝ የሚዘወሩ የጭቆና እጆች የማያንበረክኳቸው ኩሩ እና ነፃ ወጣቶች ናቸው።
ዞን9

Sunday, September 6, 2015

Inside the Trial of Zone9 Bloggers: 16 Months and Counting

Police lead Natnael Feleke (center right) and fellow blogger Atnaf Berahane (center left) to court. Photo courtesy of Trial Tracker Blog.
Police lead Natnael Feleke (center right) and fellow blogger Atnaf Berahane (center left) to court. Photo courtesy of Trial Tracker Blog.
Since they were first arrested and jailed on April 25, 2014, Ethiopia's Zone9 bloggers have seen many twists and turns in their case. All told, they have appeared before the court over 30 times in 16 months, and been adjourned each time. But with the release of five of the detainees in July, the case has reached a critical juncture.
Five Ethiopian writers (four in prison and one in absentia) remained on trial for terror-related crimes that the Ethiopian government claims were committed beginning in May 2012. Endalk Chala, a founding member of the Zone9 blogging collective and Global Voices contributor, walks us through the latest developments in the Zone9 bloggers’ trial before the next court session on Monday, September 7.
How did it begin?

When the bloggers were first arrested on April 25, 2014, they were not allowed to be visited by family members or to have a legal counsel for about three weeks. The never-ending trial of the bloggers started to unfold only four weeks after their arrest. However, during those four weeks friends and families of the bloggers reported seeing the bloggers’ Gmail accounts as logged in. The active green dots of their Gmail accounts alarmed the loved ones of the bloggers, and many suspected that the bloggers had been tortured to disclose the passwords of their Gmail accounts during the prolonged pre-trial investigation phase that took a little over three months overall.
Source: globalvoicesonline

ከብሄር ፖለቲካ እንውጣ!

ethiopian
የተባበረችውን ኢትዮጵያን እንገንባ!
በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ ኣገራችንን የሚበትኑ ኣጥፊ ዘሮች ያሏቸውን ሶስት ጉዳዮች ኣነሱ። ኣንደኛው ጠባብነት፣ ሁለተኛው ትምክህተኛነት፣ ሶስተኛው በሃይማኖት ሽፋን የሚራመድ ኣክራሪነት ናቸው ኣሉ። በመሰረቱ እነዚህን ጉዳዮች ኣቶ ሃይለማርያም ለመጀመሪያ ጊዜ ያነሷቸው ጉዳዮች ኣይደሉም። በ”ኢህዓዴግ” ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚነሱ ሁሌም ሲባሉ የነበሩ ናቸው። ኣቶ ሃይለማርያም ኣዲስ ነገር ኣልተናገሩም።
ለማናቸውም ግን እነዚህ ኣደገኛ ዘሮች ከየት መጡ? ኣገሪቱንስ ወዴት እየወሰዱ ነው? በርግጥ ከብሄር ፖለቲካው ኣዝማሪዎች ኣልፎ ወደ ታች ወርዶ የኔብጤው ተራው ህዝብ ኣካባቢ እነዚህ ዘሮች ጎልተው እየታዩ ነው ወይ? የሚለው ጉዳይና ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ያለመቻሏ ጉዳይ፣ የሰብዓዊ መብት ኣያያዝ ጉዳይ ሃላፊነት ለሚሰማው ኢትዮጵያዊ፣ ለዓለማቀፍ ተቋማትና ለኢትዮጵያ ወዳጅ ሃገራት ዲፕሎማቶች በጣም ኣሳሳቢ ጉዳይ ሆኖባቸው ኣያለሁ።
ወደ ጠቅላይ ሚንስትሩ ንግግሩ እንመለስና በመጀመሪያ እሳቸው ራሳቸው ያመኗቸው እነዚህ ሶስት ጉዳዮች በሰፊው የሚታዮት በኣንድ ሃገር ውስጥ ፖለቲካው በጠባቡ ሲቀረጽ፣ ወይም በየቤትህ እደር ኣይነት የፖለቲካ ጨዋታ ሲጀመር ወይም የፖለቲካው ጥብቆ ሲጠብ ነው። ሳይንሳዊ በሆነ ኣገላለጽ የማንነት ፖለቲካ (Identity Politics) የሚባለው ሲሆን በተለይ ብዙህ በሆነ ማህበረሰብ ውስጥ ይህ የፖለቲካ ስርዓት ሲዘረጋ የሚያመጣቸው ወይም ከዚያ የሚፈለፈሉ ችግሮች ብዙ ናቸው። የብሄር ፖለቲካ የማህበራዊ ካፒታል ምስጥ ነው። ለዚህም ነው ምሁሩ፣ ተማሪው፣ የተማረው፣ ያልተማረው ሁሉ ላለፉት ሃያ ዓመታት በላይ የብሄር ፖለቲካን ሲነቅፍ የነበረው:: የማንነት ፖለቲካ እነዚህን ኣደገኛ ነገሮች እንደሚያመጣ ብዙ ሳይንሳዊ ምርምር የሚጠይቅም ኣልነበረም። የብሄር ፖለቲካ ስነ- ልቦናው ራሱ ጠባብነት ነው። ከጎሳው ያላለፈ የፖለቲካ ስብእና ይዞ እንዲያድግ የሚያደርግ የፖለቲካ ኣስተሳሰብ የተጫነው በመሆኑ የጠባብነት መነሻው ይሄው የብሄር ፖለቲካ ነው።
ትምክህተኝነት የሚባለውም ከዚሁ ከጠባብ ኣስተሳሰብ የሚመነጭ የኣንድ ዛፍ ቅርንጫፍ ነው። ሰው ጠባብ ሲሆን ነው የሚመካው። በወንዙ በጎሳው ሲመካ ጠባብ ሆኖ ነውና። ጠባቦች ሁል ጊዜም ትምክህተኝነት ኣያጣቸውም። ሁለቱም ባህርያት የተያያዙ ከኣንድ መራራ የብሄር ፖለቲካ ምንጭ የሚቀዱ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩ ሲናገሩ ተማሪው ላይ ተጽእኖው ይታያል እንጂ እነዚህን ዘሮች የሚዘራው ኣስተማሪው ነው ኣሉ። ማን ነው የጠባብነትን ፖለቲካ የሚያስተምረው? ህወሃት “ኢህኣዴግ” ኣይደለምን? ህወሃት “ኢህዓዴግ” ከመምጣቱ በፊት ትግሬው፣ ዓማራው፣ ኦሮሞው ወዘተ ኣብሮ ቁጭ ብሎ ሲጫወት መች የብሄር ነገር ትዝ ብሎት ያውቅ ነበር? ቢታወሰውም እየተቀላለደ ከመኖር ውጭ መራራ ስር ኣልነበረውም። ለእነዚህ ኣደገኛ ዘሮች መፈጠርና ማደግ ጥሩ መፈልፈያ የሆነው ራሱ የፖለቲካው ቤት መሆኑን መረዳት ብዙ ምርምር ኣልጠየቀም።
ቡድኖች ለምንድነው የብሄር ወይም የሃይማኖት ማንነታቸውን ይዘው ወደ ፖለቲካ የሚሳቡት? ካልን የፖለቲካን ሃይል መሳሪያ በማድረግ የቡድንን የወል ጥቅምና የበላይነት ለማረጋገጥ ነው። የፖለቲካው ስልጣን የመሳሪያ ሃይል ያለውንና የኢኮኖሚውን ክፍል ስለሚያዝ ያንን ቡድኖች መቆጣጠር ከቻሉ ለቡድናቸው ኣቋራጭ እድገት ዓይነተኛ መሳሪያ ሆኖ ስለሚያዩት ነው። በዚህ የፖለቲካ ድባብ ውስጥ ኣክራሪነት፣ ልዮነትን ማድመቅ የመከሰታቸው እውነት ለምን ጥያቄ ውስጥ ይከተናል? ሃይማኖታዊ ኣክራሪነትም የሚከሰተው ኣጠቃላይ የፖለቲካው ቅርጽ በማንነት ላይ ሲረብብ ሃይማኖታዊ ማንነታቸውን ይዘው ወደ ስልጣን እንዲሳቡ የሚያደርግ ስነ ልቡናዊ ድባብ ሲፈጠር ነው። በመሰረቱ ሃይማኖትን ማጥበቅ ማለት ኣይደለም ኣክራሪነት ማለት። ሃይማኖታዊ ኣክራሪነት የሚፈጠረው በሃይማኖቱ መሰረት ላይ የቆመ ፖለቲካ ለመመስረት መጣርና በጋራ ህልውና (coexistence) ኣለማመን ነው። በግለሰብ ደረጃም ሆነ በቡድን እንዲህ ዓይነት ባህርያት ሲገለጹ ኣክራሪነት መጣ እንላለን። ይህ ኣክራሪነት በኢትዮጵያ ከታየ ኣካባቢያዊ ኣስተዋጾዎች እንዳሉ ሆነው ራሱ የፖለቲካው ተፈጥሮና የመንግስት ኣያያዝ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ማድረጋቸው ኣይካድም። በኣጠቃላይ ምንጩ የማንነት ፖለቲካ ሆኖ ሳለ ለምን የመንግስት ሰዎች እነዚህን ችግሮች እየጠቀሱ ኣጥፊዎች ናቸው እንደሚሉ ዶክተር ዳኛቸው በቅርቡ በ VOA እንዳስረዱት ለማንም ኣይገባም። “ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል” ነው ያሉት?
ጠቅላይ ሚንስትሩ ራሳቸው እኮ ቢያንስ እንደ ብሄር ራሳቸውን የሚገልጹበት ታእታይ የፖለቲካ ስብእና ባይኖራቸውም በመልክዓምድር በተወሰነ የፖለቲካ ታእታይ ስብእና የታጠሩና ለፈጠራቸው ህወሃት ኣድርባይ ናቸው። የህወሃት ኣባላትም እንዲሁ የፖለቲካ ውስጣዊ ወይም ታእታይ ሰውነታቸው በብሄር ላይ የቆመ ጠባብ ነው። በርግጥ “ኢህዓዴግ” የሚባለውን ለብሰናል ለማለት ከሆነ ህዝቡ ኣይዋጥለትም። ከዚህ በፊት እንደገለጽኩት “ኢህዓዴግ” የሚባል ድርጅትም በዓለም ላይ የለም። ለምን የለም? ከተባለ ከማንነት ፖለቲካ ተፈጥሮ ጋር ያለውን ፍልስፍናዊውን ጉዳይ ልተወውና ኣንድ ጥቂት ተግባራዊ ነገር በማንሳት ላሳይ።
የዛሬ 40 ኣመት ገደማ ሁሉም እንደሚያውቀው ህወሃት ይቋቋማል።በዚህ ወቅት ህወሃት ሲፈጠር የነበረውን ህልም ተግባራዊ ለማድረግ ውሎ ኣድሮ ያስባል። ወደዚያ የሚያደርሰው ኣድራሽ፣ ኣድራሽ ብቻ ሳይሆን እስከ ፈለገው ጊዜ እንዲቆይ፣ ጊዜ እንዲያገኝ የሚያደርገው፣ የሚያግዘው የፕሮጀክት ግብዓት ፈለገ። ጥሩ ኣድራሽና ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚሆነው የተለያዩ ብሄሮችን ስም የያዙ የፖለቲካ ድርጅቶችን መፈልፈል ሆኖ ኣገኘው። በመሆኑም እንደ ኦህዴድ፣ ብዓዴን የመሳሰሉትን ሁሉ ፈለፈለ። እነዚህ ድርጅቶች የህዝብ ብሶት የወለዳቸው፣ ህዝብ የጠየቃቸው ኣይደሉም። ህወሃት ራሱ ለፕሮጀክቱ ግብዓት ይሆኑለት ዘንድ በኣምሳሉ የቀረጻቸው ናቸው። በሌላ ኣገላለጽ እነዚህ ድርጅቶች ራሳቸው ህወሃት ናቸው። ምንምን እንኳን የተለያየ ብሄር ኣባላትን ይዘው ቢመሰረቱም ተገትረው ብናይም በህወሃት ብሶት፣ በህወሃት ራእይ፣ በህወሃት እጅ የተፈጠሩ በህወሃት የህወሃት ናቸው። ኣንዳንዶቹ ድርጅቶች በተለይም ኦህዴድ እንደሚወራው ኣንዳንድ መሪዎቹ የህወሃት ኣባላት ስማቸውን እየቀየሩ ኣመራር ላይ የነበሩበት ሁኔታም ነበር።
ኣቶ በረከት ስምዖን በህወሃት 40 ዓመት ላይ ንግግር ሲያደርጉ እንዲህ ኣሉ
እኛ ብአዴኖችም ሁሌም ቢሆን ራሳችንን ከህወሓት ነጥለን ያየንበት ጊዜ የለም። ሁላችንም “ወየንቲ ኢና” (ወያኔዎች ነንነው የምንለው።” (በረከት ስምዖን)
የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ቴድሮስ ኣድሃኖም ደግሞ ይህንን ያስረግጡልናል።
አንዳንድ ወገኖች …. ስድብ መስሏቸው “ወያኔ” አሉኝ ከጥቂት አመታት በፊት ለተመሳሳይ ጉዳይ በረከት ስምዖን ያለውን አስታወሱኝሁላችንም ወያኔ ነን” አዎ አሁንም ሁላችንም ወያኔን ነን…..እኔ ወያኔ ኢህአዴግ ነኝ! Je Suis Woyane!…. በዚህም ኩራት ይሰማኛል፡፡እኔ ወያኔ ነኝሁላችንም ወያኔ ነንይህን ችግር የሚፈታውም በወያኔነት ነው…እንበርታ፡፡” (ቴድሮስ ኣድሃኖም)
በኣንጻሩ ከህወሃት ኣባላት መንደር ሁላችንም ኦህዴድ ነን ወይም ደህዴግ ወይም ብዓዴን ለማለት ጨርሶ ታስቦ የማያውቅ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም እነዚህ ድርጅቶች እንደ ፖለቲካ ድርጅት በህወሃት ህሊና የሉምና። እንዴውም ኣቶ መለስ እንኳን ከዚህ ቡድን ተወለድኩ ብለው ጠባብና ትምክህተኛነታቸውን በኣደባባይ ሲናገሩ ተደምጠው ነበር። ይሄ ነው ጠባብነት፣ ትምክህትና ኣክራሪነት የሚባለው።
በኣጠቃላይ የሆነ ኣጀንዳ ይዞ የተነሳው ህወሃት ሲሆን በየመንገዱ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚሆኑትን የፖለቲካ ድርጅቶችን የፈለፈለ ሲሆን እነዚህን ግብዓቶች ይዞ ሁዋላ ላይ “ኢህዓዴግ” የሚል ስያሜ ይዞ ብቅ ይላል። “ኢህዓዴግ” የራሱ የህወሃት ፕሮጀክት ማስፈጽሚያ ሲሆን እንደ ፖለቲካ ድርጅት ግን ኣለ ማለት ኣይቻልም። ለዚህም ነው ራሱ በኣድራሽነት የተሰራውና የሚኖረውም። ግንባር በተፈጥሮው ኣድራሽ ሲሆን ይህ በግንባርነት የተዋቀረ ቤት የዚሁ የህወሃት ሌላው የኣዲስ ኣበባ ቤት ነው።
በርግጥ ወደ ተራው ኣባል ኣካባቢ ስናይ የዋህነት ሊኖር ይችላል። ተሰብስበው ግምገማ ሲባል፣ እቅድ ኣውጡ ኣውርዱ ሲባል “ኢህዓዴግ” በህይወት ያለ ይመስላቸው ይሆናል። የለም። ተላላ መሆን ኣያስፈልግም። ህወሃት እነዚህን ድርጅቶች ሲያቆም ኣዲስ ኣበባን ለመቆጣጠር ብቻ ሳይሆን ከዚያ በሁዋላ ደህንነቱንና ወታደሩን እንዲሁም ኢኮኖሚውን እስኪቆጣጠር ግብዓት ስለሚሆኑት ነው። በርግጥም በኣሁኑ ሰዓት በነዚህ ድርጅቶች እገዛ ህወሃት እነዚህን ህልሞቹን ኣሳክቷል። ኣቅጣጫ ነው ያጣው። በመሆኑም የነዚህ ድርጅቶች ኣባላት መታለሉን ማቆም ኣለባቸው። መንቃትና ለለውጥ መነሳት ያስፈልጋል። በቂምና በበቀል ላይ ሳይሆን ሁሉን ነጻ የሚያወጣ የወደፊቱን በማሰብ ላይ የተመሰረተ ቢሆን ነው የሚሻለው።
በኣጠቃላይ የሚንስትሮቻችን የመሪዎቻችን ታእታይ የፖለቲካ መሰረት የወንዝ ፖለቲካ በመሆኑ ከዚህ የብሄር ፖለቲካ ዘር የሚወለደው ያው ጠባብነትና ኣክራሪነት ከመሆን ኣያልፍም።ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም ከፍ ሲል እንዳየነው እኔ “Je Suis ወያኔ ነኝ” ብለዋል። ይሄ እውነተኛ የፖለቲካ መሰረታቸው ሊሆን ይችላል። የሚገርመው ግን እኚህ ሰው ኣንድ ጊዜ ኒዮርክ በተደረገ ስብሰባ ላይ “ ኒውዮርክ ሜልቲንግ ፖት ናት” ብለው በስሜት ተናገሩ። መልቲንግ ፖት የህወሃት ኣስተሳሰብ ጸር ነው። ባህላዊ ውህደት ማለት ነው ሜልቲንግ ፓት ማለት። እኚህ ሰው ምን ኣልባት ተለውጠው ከሆነ ይህን ያሉት እንዳንል የኒውዮርኩን ንግግር ካደረጉ በሁዋላ ነው እኔ “ Je Suis ወያኔ ነኝ” የሚሉን። እሳቸው ይህን ይበሉ ፣ እኔ ደግሞ Je Suis ኢትዮጵያዊ! እናንተስ?
እንግዲህ ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያም ይህን ዘር ኣጥፊ ነው ብለው ካመኑ በዚህ የወንዜ ፖለቲካ ቤት ውስጥ መዋል ማደር የለባቸውም። ሌሎች ምስጢሩ ያልገባቸው የዋህ የህወሃት፣ የብኣዴን፣የደህዴግ ወዘተ ኣባላት ከዚህ የፖለቲካ ኣስተሳሰብ ወጥተው ጠባብነትን የህወሃትን የበላይነት መዋጋት ኣለባቸው። የጠባብነትና የትምክህት ዋና የሆነውን የብሄር ፓለቲካ ቤት ግድግዳውንና ጣራውን ለመንደል የውስጥ ኣርበኞች መሆን ኣለባቸው። ለለውጥ መነሳት ኣለባቸው።የተባበረችውን ኢትዮጵያን ለመገንባት ትውልዱ ሁሉ ኣምርሮ መነሳት ኣለበት።የተባበረችውን ኢትዮጵያን የምንገነባው ደግሞ ከብሄር ፖለቲካ ስንወጣ፣ ስምምነት ውስጥ ስንገባ ነው። ይህ ስምምነት የህዝብ ውክልና በሌላቸው በዚህ ኣርባ ኣመት ባፈራናቸው እዚህም እዚያም በተኮለኮሉ ፓርቲዎች መካከል ኣይደለም። ወደ ባህላዊ ቡድኖች ታች ድረስ ወርዶ ህዝቡ ተወያይቶ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሉን ኣዋጥቶ ኣገሩን እንዲገነባ የሚያደረግ ሰፊ ስምምነት ነው።ለዚህ ደግሞ ኣገሪቱ የሆነ የጽሞናና የሽግግር ጊዜ የሚያስፈልጋት ሲሆን በዚህ ከፍተኛ ኣሳብ ላይ ሁሉም መጠቅለል ይኖርበታል። ይህ ካልሆነ ህወሃት የዘራው ዘር ከፍተኛ ኣደጋ ውስጥ ሊጥለን ይችላል።
ኣዲሲቱ የተባበረችው ኢትዮጵያ ከብሄር ፖለቲካ ወጥታ በተሻለ ውቅር ልትሰራ ይገባል። የማንነት ኪሳራ እንዳይመጣብን በኣንድ በኩል የተደራጀ የባህል መንግስት መስርተን ባህላችንን እየተንከባከብንና እየተደሰትን በሌላ በኩል ፖለቲካዊ ቤት መስራት እንችላለን። እንደ ኢትዮጵያ ብዙ መልካም ታሪክና ባህላዊ እሴቶች ያሉዋትን ኣገር ለማስተዳደር የዚህ ዓይነት ሲስተም መዘርጋቱ ሰላምን፣ ልማትና ዴሞክራሲን ያፋጥንልናል። ከዚህም በላይ ለዜጎች ርካታን ይሰጣል።
ከልጅነት ጊዜየ ጀምሮ በእድሜ የበሰሉ ሰዎች የሚሰጡት ትምህርት ይማርከኝ ነበር። ኣረጋውያን ሲያወሩ ጠጋ ብሎ ማዳመጥ ርካታን ይሰጠኛል። ከእለታት ኣንድ ቀን እንዲሁ ኣንድ የእድሜ ባለጸጋ ኣገኘሁና በተፈታ ስሜት ወግ ጀመርን። እኚህ ሰው ከሚናገሩት የሚበዛው ያለፈው ዘመን ምን ያህል የተሻለ እንደነበር ነው። ምን ኣልባት በኢኮኖሚ ጥንት የተሻሉ ነበሩ ማለት ነው፣ ኣሁን ኑሯቸው ኣሽቆልቁሏል ማለት ነው፣ ብየ እንዳላስብ ኣይደለም። ልጆቻቸው የተሻለ ገቢ ኣላቸው። እሳቸውም ድሃ የሚባሉ እንዳይደሉ ኣውቃለሁ። ምንድነው ወደ ኋላ የሚጎትታቸው? ምን ኣጥተው ነው? የሚል ጥያቄ ይዞኝ ነበር። በሳቸው የልጅነት ጊዜ በእግር ነበር ይጓዙ የነበሩት፣ ኣሁን በመኪና ይሄዳሉ፣ የተሻለ ልብስ ፣ የተሻለ ጫማ፣ የተሻለ ምግብ፣ የተሻለ ነገር…. እንዳላቸው መረዳት ችያለሁ። እኚህ ሰውም ይህንን ሁሉ ይደሰቱበታል። ይሁን እንጂ ያጡት ነገር ደግሞ ወደ ሁዋላ ሲጎትታቸው ኣየሁና ሁዋላ ላይ ለራሴ የተረዳሁት ነገር እኚህ ሰው ያጡት ባህል ነው ማለት ነው ብየ ደመደምኩ። በለውጥ ስም የሚወዱዋቸውን ባህሎቻቸውን ኣጥተዋል። ኣንቱ የተባሉ ሽማግሌዎችን ከሰፈራቸው ኣያዩም፣ ክብረ በዓላትን ሲያዩ ይገረማሉ፣ የጠፉ ባህላዊ ተቋማት ይናፍቋቸዋል፣ ወዘተ።
እኚህ ሰው ዘመናዊውን ዴሞክራቲክ የሆነ መንግስት ማየት ይፈልጋሉ። በርግጥ ደግሞ ባህላዊ ተቋሞቻቸው ቢያንስ ከነ ሙሉ ሃይላቸውም ባይሆን በቅርስነት በህይወት ማየት እንደሚፈልጉ ተማርኩ። እኚህ ሰው ኢትዮጵያን ቢወዱም ኣገራቸው የድሮ ሞገሷን የተገፈፈች ኣድርገው እንደሚያስቡ ገመትኩ። ርግጥ ነው ቁሳዊም ሆነ መንፈሳዊ ባህልን ማጣት እንደ ሃገርም እንደ ዜጋም ይከነክናል ይጎዳልም።ሌሎች የኢኮኖሚ ህይወታቸው እያደር እየደቀቀ የመጣ ሰዎችም እንዲሁ የድሮውን ጊዜ ሲናፍቁ ብዙ ጊዜ እሰማለሁ። ጥያቄያቸው ኢኮኖሚያዊ ብቻ ሳይሆን ባህላቸውንም እንደናፈቁ መረዳት ይቻላል።
ለዚህ ነው ኣዲሲቱ ኢትዮጵያ የተደባለቀውን ፖለቲካዊ ማንነትና ባህላዊ ማንነት በመለየትና በተለያየ ቤት እንዲያድሩ በማድረግ የተሻለ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋታል የሚያስብለን ። የተባበረችውን ኢትዮጵያን የምንመሰርተውም እንዲህ በጠነከረ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መሰረት ላይ መሆን ኣለበት። ለዴሞክራሲ፣ ለለውጥ የምናደርገው ትግል ሁሉ Je Suis ኢትዮጵያ መርሃችን ኣድርገን የተባበረችውን ኢትዮጵያን እንገንባ። ኢትዮጵያውያን የተባበረችውን ኢትዮጵያን ገንብተን ትኩረታችንን ሁሉ በምግብ ዋስትና ላይ ልናደርግ ይገባናል። ተመልከቱ እስቲ። ኢትዮጵያ ባለፉት ኣስር ኣመታት ያለማቋረጥ በጥንድ ቁጥር እያደገች ነው ተባለ። ጠቅላይ ሚንስትሩ በቅርብ ጊዜ ኢትዮጵያ በምግብ በብሄራዊ ደረጃ ራሷን ቻለች ኣሉ።
እነሆ በማግስቱ ዛሬ በጥቂት ወራት ውስጥ ለ4.5 ሚሊዮን ህዝብ ኣስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋል ተባለ። የተባበሩት ህዝቦች ድርጅት የሰባዊ መብት ኣጋር ድርጅትና መንግስት ይህን ገልጸዋል። በእኔ እምነት ይህም ይፋ የሆነው በተባበሩት ህዝቦች ድርጅት ቅስቀሳ እንጂ መንግስት ይህ ነገር ወደ ኣደባባይ ሳይወጣ የሆነው ቢሆን የሚመርጥ ነው የሚመስለኝ። የሚገርመው ዛሬ በብሄራዊ ደረጃ ራሳችንን በምግብ ቻልን ያሉን ጠቅላይ ሚንስትር ለተራቡ ሰዎች ቀለብ ለመግዛት ከሚያስፈልገው ተጨማሪ $230 ሚሊዮን ውስጥ $33 ሚሊዮን የሚሆነውን ብቻ ነው መንግስት መሸፈን የሚችለው። ቀሪውን 200 ሚሊዮን ገደማ ዶላር ባስቸኳይ የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ርዳታ እንዲያደርግ ልመና ጀምረናል። ይህ ማለት ደግሞ በምግብ በብሄራዊ ደረጃ ራሳችንን ኣልቻልንም ነበር ማለት ነው። ለብዙ ዓመታት በጥንድ ቁጥር ኣድጊያለሁ ዓለም ያጨብጭብልኝ ስትል የነበረች ኣገር ዛሬ ለጥቂት ወራት እንኳን ዜጎቿን መታደግ ኣልቻለችም። ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብስ ምነው ዛሬ ጠዋት በምግብ ራሳችንን ቻልን ብልችሁ የለም እንዴ? ቢለን ……ያሳፍራል። ኢትዮጵያውያን ፖለቲከኞች በውነት ኣጃንዳቸው ሁሉ ይህ ነው ሊሆን የሚገባው። ይህቺን ኣገር በምግብ ራስዋን የማስቻል ስራ ነው መቅደም ያለበት። ሰው በሚራብበት ኣገር የብሄር ፖለቲካ ቅብጥርሴ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። ለውጥና ሪፎርሜሽን ይመግበናል፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮቻችንን ይፈታልና ለለውጥ ታጥቀን እንነሳ።
እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!
geletawzeleke@gmail.com
Source: goolgule

አዲሱ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በይፋ ስራውን ጀመረ

አዲሱ የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት ዛሬ ጱግሜ 1/2007 ዓ.ም በይፋ ስራውን ጀምሯል፡፡ በዛሬው የአዲሱ ምክር ቤት ስብሰባ ነሃሴ 16ና 17/2007 ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ አስመራጭ የነበረው ኮሚቴ የብሔራዊ ምክር ቤትን፣ የኢዲትና ምርመራ ኮሚሽን አባላትን ውጤት ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በጠቅላላ ጉባኤው ምርጫ ከ1ኛ-50ኛ የተመረጡ አባላት እንደ ውጤታቸው 37ቱ ቋሚ እንዲሁም 13 ተለዋጭ አባላት ይፋ ሆነዋል፡፡ በተጨማሪም 5 የኦዲትና ምርመራ አባላትንም ይፋ አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ አዲስ የተመረጠው የኦዲትና ምርመራ የአዲሱን ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ አስመርጧል፡፡ ለሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢነት አቶ ይድነቃቸው ከበደ፣ አቶ አበበ አካሉና አቶ እስክንድር ጥላሁን የተወዳደሩ ሲሆን አቶ ይድነቃቸው ከበደ የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሆኖ ተመርጧል፡፡ በእስር ላይ የሚገኘው አቶ የሸዋስ አሰፋ ምክትል ሰብሳቢ ሆኖ ተመርጧል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ መስከረም 9/2008 ዓ.ም በሚያደርገው ሁለተኛ ስብሰባው የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት አዲሱን ካቢኔያቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር