Wednesday, July 10, 2013

የነጻ” አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሚዲያ

      የነጻአብዮታዊ  ዴሞክራሲ ሚዲያ
የእነዚህ ሕጎች መጽደቅ በዴሞክራሲ ማበብ ተስፋ ላይ ውኃ የቸለሱ ሲኾን አቶ መለስ ወደ ሚፈልጉት የአንድ ፓርቲ ፍጹም አምባገነንነት ሥርዐት ለመግባት ሕጋዊ የሚመስል ጭብጦ እና አለንጋ መጠቀምን እንደ አቅጣጫ አስቀምጧል። የኢሕአዴግን ሐሳብ የማይጋሩ ነጻ ሚዲያዎች የኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን በመቆጣጠር፣ በማዳከም፣ እና በማስፈራራት ለዘላቂው እንዳያብቡ በእንጭጩ የመከላከል ተግባር ላይ ተጠምዷል። አቶ በረከት የሚመሩት የኮሚዩኒኬሽን /ቤትም ዋና ሥራ ይህ ነው። 2000 . በኋላ ብቅ ያሉትን የተለያዩ ጋዜጦች አዲስ ነገር፣ አውራምባ ታይምስ ከመሳሰሉ ጋዜጦች የሁለት ገጽታ ያለው ግንኙነት ለመፍጠር ሞክሯል።


አንዳንድ ጋዜጦች በተደጋጋሚ ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በደረሰባቸው ማስፈራሪያ ልካቸውን አውቀው የተሸማቀቁ ሲኾን የአዲስ ነገር ጋዜጠኞች ደግሞ ለስደት ተዳርገዋል። ከመንግሥት ሚዲያ ባሻገርልማታዊ እና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የሚዲያ ዕድል አጥቶ እንዳይደርቅ ለመከላከል”  አዳዲስ ደጋፊ የፕሬስ ውጤቶች ወደ ገበያው እንዲገቡ፣ በኢኮኖሚ አቅማቸው ደካማ የኾኑ ነባር ሚዲያዎችንማቀፍአዲሱ የኢሕአዴግ የፕሬስ ኮንትራት ውል ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት በገበያው ባይቀናቸውም የኢሕአዴግን ሐሳብ የሚያቀነቅኑ አዳዲስ ፕሬሶች ወደ ገበያው ጎራ ብለዋል። አንዳንዶችም ነባር ጋዜጦች በፊት ከሚታወቁበት አሠራር በመለወጥልማታዊወደ የአዘጋገብ ዝንባሌ ውስጥ እየገቡ ነው። አንዳንዶችም የኢሕአዴግን አሠራር ባይደግፉትም ቢያንስ ተቃዋሚ ሆነው ራሳቸው ላይ አደጋ መጋበዝ አይፈልጉም። እጅግ ጥቂቶች አሁንም ኤዲቶሪያል ነጻነታቸውን ላለማስደፈር እየታገሉ ነው።
ነጻው ፕሬስ ተዳክሟል።እንዲውም ጠፍቷል ማለት ይቻላል፡ ይህች የኢሕአዴግ ኢትዮጵያ ናት። የነጻውን ፕሬስ መዳከም የተመለከቱ ታዛቢዎች ጀንበሯ በነጻ ፕሬስ ላይ አዘቅዝቃለችን? ሲሉ ጥያቄ ያነሳሉ። አንዳንዶች ደግሞጌታ ኾይ ምልክቶቹ እነዚህ ብቻ ናቸውን?” ይላሉ።

ከአንድናት ኢትዮጵያ ብሎግ

ኢትዮጵያ ክብር ለዘላለም ትኑር!

No comments:

Post a Comment