Friday, May 1, 2015

ኢህአዴግ መራጮችን እያደራጀ መሆኑ ታወቀ

ኢህአዴግ ከምርጫው በፊት ማን ሊመርጠው እንደሚችልና እንደማይችል ለማወቅ፣ እንዲሁም መራጮቹን ከአሁኑ ለመወሰን የ‹‹መራጮች ኔትወርክ›› የሚል ቡድን እያደራጀ መሆኑ ታወቀ፡፡ የመራጮች ኔትወርክ ብሎ የሚጠራውን ቡድን ለማቋቋም የየክፍለ ከተማው ደህንነቶች፣ ካቢኔዎች፣ የወረዳ ካቢኔዎች፣ የሴቶችና የወጣቶች ፎረሞች በሰፈርና በመስሪያ ቤት ፎርም እያዞሩ እያስሞሉ መሆኑን ታውቋል፡፡ በ‹‹መራጮች ኔትወርክ›› የተደራጁት ዜጎች ከአሁኑ ኢህአዴግን እንደሚመርጡ ቃል እንደሚገቡና ሌሎች ኢህአዴግን እንዲመርጡም የመመልመል ግዴታ እንዳለባቸውም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የእነዚህ የመራጮች ኔትዎርኮችን የሚመሩት የፓርቲ ካድሬዎች ሲሆኑ እነሱም በመራጮች ኔትወርክ ውስጥ የመራጮች ቡድን መሪና የቀጠና መሪ ይሆናሉ፡፡ እያንዳንዱ ትዕዛዝ የሚመጣው ከማዕከላዊ የኢህአዴግ ጽ/ቤት እንደሆነም ታውቋል፡፡

Jailed Ethiopian Blogger Asks John Kerry for Justice

zone9flag

he Netizen Report offers an international snapshot of challenges, victories, and emerging trends in Internet rights around the world. It originally appears each week on Global Voices Advocacy. Ellery Roberts Biddle, Lisa Ferguson, Weiping Li, Hae-in Lim, and Sarah Myers West contributed to this report.
GVA logo
It has been one year since Ethiopian authorities arrested nine bloggers and journalists in association with the Zone9 blogging collective, a group of recent university graduates who wrote about political challenges in their country and worked to help Ethiopians understand their constitutional rights. The government’s case against the bloggers, who were charged under the Anti-Terrorism Proclamation, focuses on their use of secure communications tools and online platforms in what the government called an attempt to “overthrow, modify or suspend the Federal or State Constitution by violence, threats or conspiracy.”
Ethiopia has a mandate (and large amounts of aid money) from the United States and other Western governments to maintain a security stronghold in the Horn of Africa, where the threat of violent extremist groups such as Al-Shabaab is a persistent concern. But apart from countering these threats, the Ethiopian government has also used this scenario as a justification for punishing its most vocal critics, among them journalists like Eskinder Nega, Reeyot Alemu, and the Zone9 bloggers.
Although they have been behind bars since last April, the Zone9 bloggers’ voices have not been quelled: With the help of friends, they have smuggled out multiple accounts of their experiences in prison. Last week, the Guardian published a letter from Zone9 blogger Natnael Feleke addressed to Secretary of State John Kerry, whom he met at a student forum prior to his arrest. Feleke, an economics student at Addis Ababa University, writes:
To be honest with you, how much time I will be spending in prison is not the most pressing issue on my mind right now. ... It is not that I don't appreciate the earnest assistance being forwarded to the development process in my country. It is just that I strongly believe effective monitoring of such assistance can only be employed where there is a government accountable to its people. It is ironic that the world's top recipient of development assistance is without effective monitoring and accountability. …
I understand the difficulty you face in striking a balance between maintaining security and stability and promoting democratization in your foreign policy. ... As US national interests are built on core values of liberty and democracy, I have hope and confidence that you will adopt a new stance that forges a clearer relationship between any form of assistance and the democratization process.
Natnael’s original letter can be read on Global Voices. Global Voices writers and advocates from Azerbaijan, Croatia, Cuba, Iran, Kenya, Mexico, and beyond created a video to mark the anniversary of the bloggers’ arrest:
Signals drop as Guatemalans call for president’s resignation
Tens of thousands of Guatemalans demonstrated in the nation’s capital last Saturdaydemanding the resignation of President Otto Perez Molina and Vice President Roxana Baldetti, in the wake of a massive corruption scandal that allegedly involved Baldetti’s secretary. Multiple protesters posted photos of strange devices set up around the capital, which several local sources say are high-resolution cameras used to monitor the protests. Mobile phone signals were blocked, preventing protesters from communicating over social media. It remains unclear whether the outage was a strategic move to diminish their efforts or merely a system overload.
Vietnam’s social networks are lively, despite strict Internet laws
According to a report
 by pro-democracy party Viet Tan, Vietnamese netizens areincreasingly turning to social networks to express their views on social and political issues, despite stringent restrictions on free expression in the country.
Source: The Netizen 

The United States’ irresponsible praise of Ethiopia’s regime

ETHIOPIA’S ELECTIONS, scheduled for May 24, are shaping up to be anything but democratic. A country that has often been held up as a poster child for development has been stifling civic freedoms and systematically cracking down on independent journalism for several years.
It was consequently startling to hear the State Department’s undersecretary of state for political affairs, Wendy Sherman, declareduring a visit to Addis Ababa on April 16 that “Ethiopia is a democracy that is moving forward in an election that we expect to be free, fair and credible.” The ensuing backlash from Ethiopians and human rights advocates was deserved.
Ms. Sherman’s lavish praise was particularly unjustified given Ethiopia’s record on press freedom: It has imprisoned 19 journalists, more than any other country in Africa. According to a new report by the Committee to Protect Journalists, the country ranks fourth on its list of the top 10 most censored countries in the world. At least 16 journalists have been forced into exile, and a number of independent publications have shut down due to official pressure.
Last weekend marked one year since six bloggers were arrested and jailed without trial. The “Zone 9” bloggers, who used their online platforms to write about human rights and social justice and to agitate for a democracy in Ethi­o­pia, were charged with terrorism under the Anti-Terrorism Proclamation, which has been used to clamp down on numerous journalists critical of the regime. Today, the bloggers remain imprisoned, awaiting what will likely be a trial by farce.
As for the elections, opposition parties say the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front , led by Hailemariam Desalegn, has undermined their efforts to register candidates for the May vote. Since last year, members of opposition parties and their supporters have been arrested and harassed. In March, the sole opposition leader in Parliament said he would not run for reelection due to state interference with his party’s affairs. The EPRDF, which has been in power since 1991, was reported to have won the last elections in 2010 with 99.6 percent of the vote.
The State Department released a statement last week urging Ethiopia to release journalists who have been imprisoned for doing their jobs. But as the considerably more high-profile statement by Ms. Sherman indicated, the Obama administration has been reluctant to criticize what it regards as a key security ally in the Horn of Africa. A State Department spokeswoman confirmed this week that Ms. Sherman’s comments “fully reflect the U.S. government’s positions on these issues.”
With its ancient culture, strategic location and population of 94 million, Ethi­o­pia is indeed key to the future of eastern Africa. But that does not justify make-believe statements or a go-softly approach that is not working. The United States should stop funneling millions of aid dollars to a regime that has continued to choke off the media, hamper the participation of opposition parties and silence its critics. If the election is not judged by independent observers to live up to Ms. Sherman’s billing, the administration should swallow her words — and change its approach.
Source: washingtonpost

አምቡላንሶች ለምርጫ ቅስቀሳ በመዋላቸው የእናቶች ህይወት እያለፈ ነው

በሀድያ ዞን አምቡላንሶች ለምርጫ ቅስቀሳ እየዋሉ በመሆኑ ህመምተኞች በተለይም ነፍሰ ጡር እናቶች ህክምና ሳያገኙ ለሞት እንደሚዳረጉ ነዋሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም አንዲት ምጥ የተያዙ እናት በአቅራቢያቸው በሚገኝ የጎምበራ የጤና ጣቢያ በሄዱበት ወቅት ‹‹ከአቅማችን በላይ ነው!›› ተብለው ወደ ሆሳና ሪፈራል ሆስፒታል ሄደው እንዲታከሙ ሪፈር ቢጻፍላቸውም በትራንስፖርት ችግር ነፍሳቸው አልፋለች፡፡ 

ለጎምበራ ጤና ጣቢያ የተመደበችው አምቡላንስ በጎምበራ ወረዳ ኦሌ ቀበሌ ለገዥው ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በመውጣቷ ቤተሰብ ነፍሰጡሯን ከጎምበራ ጤና ጣቢያ ወደ ሀድያ ሪፈራል ሆስፒታል በቃሬዛ ለመውሰድ መገደዳቸው ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ወደ ሀድያ ሆስፒታል በቶሎ መድረስ ባለመቻላቸው የነፍሰ ጡሯ ህይወት መንገድ ላይ ሊያልፍ ችሏል፡፡
 
ነዋሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጹት አምቡላንሶች ለምርጫ ቅስቀሳ በመዋላቸው ምክንያት በርካታ ህመምተኞች በተለይም እናቶችና ህፃናት በቶሎ ወደ ሆስፒታል መድረስ ባለመቻላቸው ተመሳሳይ ችግር እየገጠማቸው ነው፡፡

በኮምፒተር የኤሌትሪክ ገመድ የሚገርፍ አገዛዝ – ግርማ ካሳ

የኢትዮጵያ መንግስት ለሕግ የሚቆረቆር መንግስት እንደሆነ ብዙ ጊዜ ሲናገር ይደመጣል። የተባበሩት መንግስታት አባል ድርጅት እንደመሆኗም፣ ኢትዮጵያ፣ የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶችን ድንጋጌን የማክበር ግዴታ አለባት። እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ1976 የተደረገው፣ ቃልኪዳን ለሰብአዊና ፖለቲካ መብቶች ፣ The International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR) ዉል/ስምምንት ፈራሚ አገር ናት።

የ ICCPR ዉል አንቀጽ ሰባት እንዲሁም የተባበሩት መንግስት የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ አምስት፣ በግልጽ እንዳስቀመጡት ፣ ማን ሰው በአካሉ ላይ ድብደባ፣ ጉዳት፣ ቶርቸርና ክብሩ የሚነኩ ተግባራት ሊፈጸሙበት እንደማይገባ ይደነግጋሉ። «No one shall be subjected to torture or to cruel, inhuman or degrading treatment or punishment» ይላሉ አንቀጾቹ።

በአገራችን ኢትዮጵያ ወዳሉት ሕጎች ስንመጣ ደግሞ፣ የሕጎች ሁሉ የበላይ ሕግ መንግስቱ እንጂ ከጥቂት የሕወሃት የደህንነት አባላት የሚመጣ መመሪያ እንዳለሆነ በግልጽ ተቀምጧል። የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 21 « በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰባአዊ ክብራቸውን በሚተበቁ ሁኔታዎች የመያዝ መብት አላቸው» ይላል።

ሆኖም በተለያዩ ጊዜያት ተቃዋሞ የሚያሰሙ ወገኖች ሕግ መንግስቱ ወረቀት ብቻ እንደሚሉት፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ለአገሪቷ ሕግ ደንታ እንደሌለው፣ የአለም አቀፍ ሕግጋቶችን የሚጥስ ፣ አደገኛው አሸባሪና የሕግ አፍራሽ እንደሆነ በግልጽ እያሳየ ነው።
ለሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ለሚባል ድርጅት ፣በማእከላዊ እሥር ቤት ስለደረሰባቸው ሁኔታ ዞን ዘጠኞች የተናገሩትን ላነበበ፣ በርግጥም ምን ያህል አገራችን በሕግ የማትተዳደር እንደሆነ መደምደም አያቅተውም።

«ከወንበሬ አንድነሳ አዘዙኝ፡። ከዚያም በቆምኩበት ግራ ብብቴን እና እጄን በአንድ እጁ አንዳልወድቅ ወጥሮ ይዞ በእግሩ ጭኔን በሃይል ደበደበኝ። ከድብደባው በማስከተል ደግሞ እግሬ መሃል እግሩን በማስገባት ወደግራ እና ወደቀኝ በመምታት ተዘርጥጬ እንድቆይ በማድረግ እጄን ወደላይ አድርጌ እግሬ ግራና ቀኝ ተዘርጥጦ ( በተለምዶ ስፕሊት በሚባለው) በግራ እና ከቀኝ በመደብደብ እጄን ወደላይ አድርጌ እነድመረመር ተደርጌያለሁ። ከዚህ ምርመራ በኋላ ለሁለት ቀን እያነከሰኩ ነበር» ሲል ነበር በፋቃዱ ሃይሎ ሰቆቃዉን የገለጸው።

አቤል ዋበላ በተራው የደረሰበትን ግፍ ሲያስረዳ «ድብደባውም ጨለማ ክፍል ውስጥ በማስገባት አፌ ውስጥ ካልሲ በመወተፍ እግሮቼን ከላይ፣ ውስጥ እግሬን እና ከውስጥ ባቴን ታፋዬን እንዲሁም ጀርባዬን በእንጨትና በኮምፒውተር ገመድ ገርፈውኛል። የምርመራ ክፍሉ ወለል ላይ በደረቴ አንዲሁም በጀርባዬ እያገላበጡ በማስተኛት መላ ሰውነቴን ረግጠው ተራምደውብኛል፡። አፌን ሳይቀር ረግጠውታል» ነበር ያለው።

ናትናኤል ፈለቀ በበኩሉ «ጫማዬን አውልቄ በባዶ እግሬ አንድቆም ከተደረኩ በኋላ እግሮቼ ጣቶች ላይ መርማሪዎቹ በጫማቸው በሃይል በመርገጥ እግሬ ላይ ከባድ ድብደባ አድርሰውብኛል» ሲል አጥፋን ብርሃኔ ደግሞ «ከግድግዳ ጋር እያጋጨ ደብድቦኛል» ሲል በማእከላዊ የነበረዉን ሰቅጣጭ ቶርቾር አጋልጠዋል።

በማእከላዊ የሚታየው ቶርቸር፣ ከዋናዉ የደህንነት ሃላፊዎች አዎንታ ያገኘ የተለመደ አሰራ እንደሆነ የታወቀ ነው። በሕወሃት/ኢሕአዴግ ዉስጥ ያለው ባህል፣ ፓለቲካን አሰራር የፍቅር፣ የሰብአዊነት፣ የመቻቻል፣ የሰለጠነ፣ የፍቅር ሳይሆን የጫካ፣ የአዉሬ፣ የጭካኔ፣ የኢሰባአዊነት አረሜኔያዊ ፖለቲካን አሰራር ነው።

ይህ ባህል፣ ይህ ፖለቲካ፣ እስካልተቀየረ ድረስ ዛረ በነ በፍቃዱ ላይ የሆነው ነገ በሌሎችም ላይ መድረሱ አይቀርም። ዛሬ ዞን ዘጠኞችን ያንኳኳ፣ ነገ የኛን በር ማንኳኳቱ አይቀርም። በመሆኑም ይሄንን ለአዲሱ ትዉልድ የማይመጥን፣ ያረጀ፣ ኋላ ቀር፣ ዘረኛ፣ ፍጹም አረመኔያዊ የሆነ ስርዓት ለመቀየር እያንዳንዳችን ከመቼዉም ጊዜ በላይ መነሳት አለብን። ከዚህ በላይ ዉርደት፣ ከዚህ በላይ ሞት የለም። ወገን፣ በነጻነትና በክብር እንድንኖር በእግዚባሄር አምሳል የተፈጠርን ሰዎች እንጂ እንስሶች አይደለም። በቃ የምንለበት ጊዜ ነው። እነርሱ ለጊዜው ሜዲያዉን ይዘው ፣ ዲስኩር በማስማት ያስፈራሩ ይሆናል። እነርሱ በጥቅም በገዟቸው ጉጄል ፌዴራሎችን አጋዚዎች ይመኩ ይሆናል። «አንመካም በጉልበታችን፣ እግዚአብሄር ነው የኛ ኃይላችን» እንዳሉት የአዲስ አበባ ሰልፈኞች እኛ የምንመካው በእግዚአብሄር ነው። በፈጣሪ እርዳታ፣ በፍቅርና በአንድነት ተያይዘን ከቆምን፣ ጥቂቶች በምንም ሂሳብ ሚሊዮኖችን ሊያሸንፉ አይችሉም።
-Source: satenaw

የአራት ኪሎ ወጣቶች ለሁለተኛ ጊዜ ታፈሱ

• ‹‹ከአሁን በኋላ በሽብር እንከሳችኋለን!›› ፖሊስ
አራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ወጣቶች ትናንት ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ መታፈሳቸውን ወጣቶቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ከአንድ ወር በፊት ፖሊስ ወጣቶቹን ቪዲዮና ኳስ የሚታይባቸው ቤቶች ውስጥ እያሉ ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት አላችሁ›› በሚል ካሰረ በኋላ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ እንደለቀቃቸው ገልጸዋል፡፡
በትናንትናው ዕለትም ፖሊስ በርከት ያሉ ወጣቶችን አስሮ የነበር ሲሆን ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ እንድትበጠብጡለት ምን ያህል ብር ይከፍላችኋል? ማን ነው ያደራጃችሁ? ደንጋይ ለመወርወር ምን ያህል ብር ይከፈላችኋል?›› በሚል ምርመራ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል፡፡ በስተመጨረሻም ምሽት ላይ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ ከእስር ተለቀዋል፡፡ ወጣቶቹን ‹‹ከአሁን በኋላ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት እንዳላችሁ ካወቅን በሽብር ነው የምንከሳችሁ፡፡›› የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ቤት ተበረበረ

• የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ለ‹ምርመራ› ተወስዷል
ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስ ሊቢያ በሚገኙ ንጹሃን ኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸመውን አሰቃቂ የሽብር ድርጊት ለማውገዝ ጠርቶት በነበረው ሰልፍ ሳይጀመርና ከሰልፉ በኋላ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ቤት ተበረበረ፡፡ ካሳንቺስ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ትናንት ሚያዝያ 22 ቀን 2007 ዓ.ም በቄራ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ቀርበው የ6 ቀን ቀጠሮ ከተሰጠባቸው በኋላ ምሽት ላይ ቤታቸው መበርበሩንና ንብረቶቻቸው መወሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡ 
በብርበራው ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ፣ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በሰላማዊ ሰልፍና በሌሎች አጋጣሚዎች የሚለብሱት የሰማያዊ ፓርቲ አርማ ያለበት ቲሸርት፣ የምርጫና ሌሎች ቅስቀሳ ወረቀቶችም ለ‹ምርመራ› ተወስደዋል፡፡
ቤታቸው ለሰዓታት የተበረበረባቸው ወይንሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ጸጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ማስተዋል ፍቃዱ ሲሆኑ ወይንሸት ሞላ የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ ወረቀቶች፣ የሰማያዊ ፓርቲ አርማ ያለበት ቲሸርት፣ ሲዲዎች፣ አርማ የሌለው የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ (በተናጠል አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የሆነ)፣መጽሐፎች እና ሌሎችም ህጋዊ ሰነዶች እንደተወሰዱባት ገልጻለች፡፡ ዳንኤል ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ፣ የሰማያዊ ፓርቲ አርማ ያለበት ቲሸርት፣ በአንድ ላይ ያስጠረዛቸው የፋክትና የአዲስ ጉዳይ እትሞች፣ ሲዲዎችና ካሴቶች ተወስደውበታል፡፡ በተመሳሳይ ኤርሚያስ ጸጋዬ ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሰነዶች፣ ሲዲዎች፣ ማስታወሻ ደብተሮችና ሌሎችም ህጋዊ ሰነዶች ተወስደውብኛል ብሏል፡፡