Sunday, November 3, 2013

ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አመታት ከ400 ሺ በላይ ዜጎቿን በስደት አጣች

ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አመታት ከ400 ሺ በላይ ዜጎቿን በስደት አጣች

November 2, 2013
ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ በህዝብና በአገር ላይ የሚፈጽመዉን ግፍና በደል በመሸሽ ከኢትዮጵያን እየጣለ የሚሰደደዉ ሰዉ ቁጥር ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ መምጣቱን ከአገር ዉስጥና ከአለም አቀፍ ተቋሞች የሚመጡ መራዎች ጠቆሙ። በቅርቡ ከወያኔዉ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ባለፉት 2 ዓመታት ዉስጥ ብቻ ከ400 ሺ በላይ ዜጎች ኢትዮጵያን ለቅቀዉ መሰደዳቸዉ ታዉቋል። ይህንን እጅግ በጣም አሳሳቢ መረጃ ይፋ ያደረገዉ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጨምሮ እንዳስረዳዉ ይህ ቁጥር የወያኔን ጫናና መከራ ላለማየት በሀጋዊ መንግድ አገር እየለቀቁ የሚሄዱትን ሰዎች እንደማይጨምር ታዉቋል።

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ኢትዮጵያዉያን ከደርግ ዘመን ጀምሮ በጎንደር፤ በሐረር፤ በወለጋ፤ በባሌና በሲዳሞ በኩል አገር እየጣሉ እንደሚሰደዱ የታወቀ ሲሆን ወያኔ አትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ የአገሪቱ የፖለቲካና የኤኮኖሚ ሁኔታ ይሻሻላል በሚል ብዙዎች ኢትዮጵያን እየለቀቀ የሚሰደደዉ ሰዉ ቁጥር ይቀንሳል የሚል እምነት ነበራቸዉ። ሆኖም ወያኔ ብዙም ሳይቆይ የዘረኝነት ፖሊሲዉን ተግባራዊ ማድረግ በመጀመሩ የስደተኘዉ ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱ ታዉቋል። በደርግ ዘመን በብዛት ይሰደድ የነበረዉ የቀይ ሽብር ብትር ያርፍበት የነበረዉ ወጣቱና ምሁሩ ሲሆን ዛሬ በወያኔ ዘመን ግን ወንድና ሴት ሳይለይ ወጣቱ፤ተማሪዉ፤ ምሁሩ ፤ሰራተኛዉና ገበሬዉ አንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ የአለማችን አምስተኛዉ ታዳጊ ኤኮኖሚ ነዉ እያሉ ወያኔና አፈ ቀላጤዎቹ ቢናገሩም ዛሬም ኢትዮጵያ አፍሪካ ዉስጥ ከፍተኛ ህዝብ የሚሰደድባት አገር አንደሆነችና በተለይ በከፍተኛ ደረጃ የተማረዉን የሰዉ ኃይል በተመለከተ ኢትዮጵያ ምሁሮቻቸዉን በአዉሮፓና በአሜሪካ ከተቀሙ ታዳጊ አገሮች ግንባር ቀደሟ እንደሆነች አለም አቀፍ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በተለይ የወያኔ አገዛዝ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ስራ ፍለጋ ወደ ፋርስ በህረሰላጤ አገሮችና ወደ መካከለኛዉ ምስራቅኢ አገሮች የሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን ሴቶች ቁጥር በከፈተኛ ፍጥነት ማደጉ የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህንኑ ተከትሎ አያሌ የዜጎች ወደነዚህ አገሮች የሚያደርጉትን ፍልሰት የሚያፋጥኑ ድርጅቶች አዲስ አበባን ማጨናነቃቸዉ ይታወቀቃል። ወያኔ አገዛዝም ቢሆን በዚህ የሰዉ ልጆች ንግድ ተጠቃሚ ስለሆነ ስራ ፈላጊዎች ከመሰደድ ይልቅ አገር ዉስጥ ስራ እንዲያገኙ ያደረገዉ ምንም ነገር የለም። አርብ አገር የሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን ሴቶች የሚደርስባቸዉ ከፈተኛ ችግር፤ ሞትና እንግልት በአለም አቀፍ ሜድያዎች ጭምር በመዘገቡ ወያኔ በቅርቡ ለስራ በሚል ወደ ውጪ በሚጓዙት ላይ እገዳ መጣሉ ይታወቃል።
የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ስምሪት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ አበበ ሀይሌ እንዳሉት ፥ እገዳው ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ሊባኖስ ፣ ኳታር ፣ ሳውዲ አረብያ ፣ ኩየት ፣ የመን ፣ ሱዳንና ደቡብ አፍሪካ ይገኙበታል።በእገዳው መሰረት ካሁን ቀደም ቪዛ ያገኙትን ጨምሮ ቪዛ ለማግኘት እየተጣጣሩ ያሉትም ቢሆን ወደ ሀገራቱ መጓዝ አይችሉም።፤ እገዳው በቤት ሰራተኝነት ተቀጥሮ ለመስራት ከሚደረጉት ጉዞዎች ባሻገር አለም አቀፋዊ ተቀባይነት ባላቸው ሙያዎች ላይ የሚደረጉ ጉዞዎችን እንደማይመለክትም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በመንገድ የቀረው ቀርቶ ወደ መጨረሻ መዳረሻ ሀገር የገቡት ዜጎች እጣ ፈንታ አብዛኛውን ጊዜ ስቃይና እንግልት ቢሆንም ፥ ዛሬም በዚያ የሞት ጎዳና ላይ የሚተሙ ዜጎች ቁጥር ሊቀንስ አልቻለም።

France’s Consul in Ethiopia issues security advice

France’s Consul in Ethiopia issues 

security advice



France warns its citizens from travelling to Addis Ababa and 

potential target areas which include residential areas, 

business offices, hotels, clubs, restaurants, places of 

worship, schools, public areas, shopping malls, and other 

tourist destinations both in the United States and abroad 

where its citizens gather in large numbers. 




The bomb explosion in the Bole neighbourhood in Addis 

Ababa on 13 October “only confirms the reality of the 

terrorist risk in Ethiopia”, according to the message sent to 

his compatriots on 16 October by Jerôme Periolat, the 

French consul in Addis Ababa.


The fact is revealed as TPLF cadres deliberately planted and 

detonated a self-made bomb on 13 October 2013. This is 

merely to blame the Ethiopian muslims and the growing 

opposition groups so as to falsely accuse them of terrorist 

act and throw the opposition members into prison.

Saturday, November 2, 2013

“አንድነት” በአባላቶቹ ላይ የሚደርሰው ጥቃት መባባሱን ገለፀ

“አንድነት” በአባላቶቹ ላይ የሚደርሰው ጥቃት መባባሱን ገለፀ

“አንድነት” በአባላቶቹ ላይ የሚደርሰው ጥቃት መባባሱን ገለፀ
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በአባላቱና በደጋፊዎቹ ላይ የሚደርስባቸው ጥቃትና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ መባባሳቸውን ገለፀ፡፡
ከትላንት በስቲያ ፓርቲው በፅ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት፤ ከ2003 አንስቶ በአባላቱና ደጋፊዎቹ ላይ የደረሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በዝርዝር አቅርቧል፡፡ ፓርቲው “የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት” በሚል ባወጣው ሰነድ፤ ከተዘረዘሩ ጥቃቶች መካከል:- በድብደባ አካል ማጉደል፣ በህገወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር ማዋል፣ ማሰቃየት፣ ማስፈራራትና መዛት እንዲሁም በማስገደድ መረጃ ከፓርቲያቸው እንዲያመጡ ማድረግ፣ የመኖሪያ ቦታን በህገወጥ መንገድ መበርበር፣ ይዞታና ንብረትን ያለ ካሳ ነጥቆ መውሰድ… የሚሉት ይገኙበታል፡፡
አቶ ደምሴ መንግሥቱና አቶ ገበየሁ ይርዳው የተባሉ የፓርቲው አመራሮች፤ በአባላትና ደጋፊዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደመጣ ጠቁመው፣ ጥቃት የደረሰባቸው አራት አዛውንት አባላቶቻቸው ጉዳታቸውን በአካል በማሳየት በህገመንግስቱ እውቅና የተሰጣቸውን:- በህይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነት እንዲሁም በህግ ፊት እኩል የመታየት ተብለው የተዘረዘሩት መብቶች መጣሳቸውን ገልፀዋል፡፡

በጂጂጋ ፍተሻው ተጠናክሯል

በጂጂጋ ፍተሻው ተጠናክሯል


ከቀኑ 10 ሰዓት በኋላ ባጃጆች አይሰሩም 
ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላ ሰዓት እላፊ ታውጇል 
በኢትዮጵያ ሶማሊያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ እስከ ህዳር 30 ድረስ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መዘጋታቸውን ምንጮች ገለፁ፡፡ በከተማው የሚገኙ 2300 ያህል ባጃጆችም ከቀኑ አስር ሰዓት በኋላ ስራ እንዳይሰሩ መታገዳቸውን ምንጮች የገለፁ ሲሆን ከምሽቱ አራት ሰዓት በኋላም ሰዓት እላፊ ስለታወጀ በከተማው ነዋሪዎች ከአራት ሰዓት በኋላ እንደማይንቀሳቀሱ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ 
“በምሰራበት የመንግስት መስሪያ ቤት ዋና የስራ ሂደት ባለቤት ነኝ” ያሉ አንድ ግለሰብ፤ የመንግስት ሰራተኛ ስራውን ትቶ በከተማው ካሉ ልዩ ሀይሎች ጋር በመሆን ሰዎችን ወደመፈተሽ ስራ መግባቱን ተናግረዋል። አንድ ሰው ከከተማው አንድ ቦታ ተነስቶ የሚፈልግበት እስኪደርስ ቢያንስ አምስትና ስድስት ጊዜ ሊፈተሽ ይችላል ያሉት እኒሁ የመንግስት ሠራተኛ፤ ለከተማው ፀጥታ ሲባል ፍተሻው ተገቢ ቢሆንም ለ40 ቀን የመንግስት ስራ ቆሞ ሰራተኛውን ፈታሽ ማድረግ ግን አግባብ እንዳልሆነና እንደሚቃወሙት ገልፀዋል። 
በቅርቡ የሚከበረውን የብሔር ብሔረሰቦች በዓል በጅጅጋ ለማክበር የሚደረገውን ዝግጅት ተከትሎ አካባቢውን ለመጠበቅ በሚል ፍተሻው ቢጠናከርም የመንግስት ሰራተኞች ለ40 ቀን ስራ ትተው ለፍተሻ መሰማራታቸው አግባብ እንዳልሆነ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ 
“የብሄር ብሄረሰቦች በዓል በልዩነታችን ውስጥ አንድነታችንን የምናይበት እና የምንከባበርበት እንጂ ዜጎች ስራ አቁመው ወዳልተፈለገ ስራ የሚሰማሩበትና የሚሰቃዩበት መሆን የለበትም” ሲሉ አማረዋል፤ ግለሰቡ፡፡ “አንድ ባጃጅ ለሹፌሩን እና ለባለቤቱ ቤተሰቦች ገቢ የሚያስገኝ በመሆኑ ከ10 ሰዓት በኋላ እንዳይሰሩ መከልከሉን እንቃወማለን” ያሉት ስማቸውን ያልገለፁ ሌላው የመንግስት ሰራተኛ፤ ጉዳዩን የፌዴራል መንግስት አውቆት እልባት እንዲያገኝና የክልሉ መንግስት ስህተቱን እንዲያርም አሳስበዋል፡፡ 
“እኔ የመንግስት ሰራተኛ ባለመሆኔ የመንግስት መስሪያ ቤት ስለመዘጋቱ የማውቀው የለም” ያሉት አንዲት የከተማዋ ነዋሪ፤ ባጃጆች ከአስር ሰዓት በኋላ ስራ እንደማይሰሩና ሰዓት እላፊ መታወጁን ግን እንደሚያውቁ ተናግረዋል፡፡ “በአጋጣሚ መታወቂያ ሳትይዢ ከቤት ከወጣሽ ታፍሰሽ ወደ እስር ቤት ትወሰጃለሽ” ያሉት ሌላው ነዋሪ፤ ያለፖሊስ ማዘዣ ቤቶች ሲፈተሹና ሲበረበሩ ያድራሉ፤ ለዚሁ ስራ ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የነበሩ ልዩ ሀይሎች ተሰማርተዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ 
“ለ40 ቀናት የመንግስት መስሪያ ቤቶች መዘጋት እንዳለባቸው ሰብስበው የነገሩን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ናቸው” ያሉት አንድ የመንግስት ሰራተኛ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ማክበር የመንግስት ብቻ አለመሆኑን ከተስማማን በኋላ ሁላችሁም ወገባችሁን አስራችሁ ፍተሻ ቀጥሉ በሚል ስም ተመዝግቦና ቁጥጥር እየተደረገ የመንግስት ሰራተኛው በቡድን ተከፍሎ ፍተሻውን ተያይዞታል ብለዋል፡፡ 
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዲአዚዝ መሀመድ በበኩላቸው፤ መረጃው የተሳሳተ መሆኑን ገልፀው “እንዴት የመንግስት መስሪያ ቤት 40 ቀን ሙሉ ይዘጋል” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
የብሔር ብሔረሰቦችን በዓል አከባበር በተመለከተ፣ የመንግስት ሠራተኞች በትርፍ ሰዓታቸው ለሕዝቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት አገልግሎት ይሰጣሉ ካሉ በኋላ፤ “ፍተሻ አለ፣ ባጃጅ አይሰራም፣ ሰዓት እላፊ ታውጇል የሚባለው ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ አስተባብለዋል፡፡

Friday, November 1, 2013

Ethiopian opposition claims rampant abuse


Ethiopian opposition claims rampant abuse



Opposition party says more than 150 of its members have suffered abuse at hands of Ethiopian security officials.

Negasso Gidada, the UDJ party chief, centre, has urged the government to stop abusing his party members [EPA]
An opposition party has accused the Ethiopian government of beating, abducting and illegally detaining more than 150 of its members during July and September this year.
In a 39-page report launched on Thursday, the Unity for Democracy and Justice (UDJ) detailed what it said were "gruesome rights violations" committed against its supporters and members.
"One hundred and fifty members and supporters of the party have been subjected to severe beatings, illegal detentions and abductions by the police and security officials," Negasso Gidada, the party chairman, told reporters.
"We are asking the government to stop these human rights violations and take those responsible to justice," said Negasso, who served as the country's president from 1995 to 2001, before joining the opposition.
A government spokesman declined to comment saying it had yet to receive the report.
Earlier this month, Human Rights Watch said many former detainees - including politicians, journalists and alleged supporters of opposition groups - were slapped, kicked and beaten with sticks and gun butts during investigations at Addis Ababa's Federal Police Crime Investigation Sector, known as Maekalawi.
Ethiopia intensified its clampdown on peaceful dissent after the disputed 2005 election, the New York-based watchdog said.
Stifling dissent
At the time, the polls ended in violence, killing abouot 200 people.

Opposition candidates won 174 seats, but many did not take them up, saying the vote was rigged.
In an interview with Reuters this month, Prime Minister Hailemariam Desalegn said the government was not to blame for the opposition's poor showing.
He has also accused some opposition party members of collaborating with rebel groups the government had previously labelled as terrorist organisations.
But UDJ's leaders deny any links with the outlawed rebel groups, and warn the government that "stifling" dissent may encourage violence in the country.
"We are not requesting anything from the government side, we are requesting a level playing ground," Girma Seifu, a senior UDJ official and the sole opposition politician in Ethiopia's 547-seat parliament.
The Horn of Africa country has won international plaudits for delivering double-digit growth for much of the past decade, but rights groups often accuse the government of using state institutions to stifle dissent and silence political opposition.
http://www.aljazeera.com

ፊን ፊሸር ሰላዩ ቫይረስ

ፊን ፊሸር ሰላዩ ቫይረስ

ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም በዓለም 25 ሀገሮች ዉስጥ መሠራጨቱንና መንግስታቱም የገዛ ዜጎቻቸዉን ለመሠለል እንደሚጠቀሙበት አንድ ጥናት አመለከተ። ኢትዮጵያ ዉስጥም በሠፊዉ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ጥናቱ ይፋ አድርጓል።
የኢንተርኔት ቫይረሱ ኮምፕዩተር ዉስጥ ከገባ ግለሰቦች በኮምፕዩተራቸዉ ላይ የሚያደርጉትን የፅሁፍ የድምፅና የምስል የመልዕክት ልዉዉጦች ወደዋና መረጃ ማሰባሰቢያዉ ማዕከል ይልካል። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች RSF ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚደረገዉን ቁጥጥር አስመልክቶ የተጠቀሰዉ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን ጥናቱን ጠቅሶ ለዶቼ ቬለ መግለፁን ዘግበናል። ዶቼቬለ ስለጉዳዩ የጠየቃቸው የኢትዮ ቴሌኮም የኮምንኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሂም አህመድ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠቀሰው ፕሮግራም እንደማይገለገል በስልክ ተናግረዋል። አቶ አብዱራሂም ስለጥናቱ ውጤት እንደማያውቁ ገልፀው ሆኖም ፊን ፊሸር የተባለው የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ላይ ውሏል መባሉን ከዕውነት የራቀ ሲሉ አጣጥለውታል።
ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት RSF በያዝነዉ ሳምንትባወጣዉ የኢንተርኔት ቁጥጥርን የሚመለከት ዘገባ አምስት ሀገሮችን የኢንተርኔት ጠላት ሲል ፈርጇል። የሶርያ፤ ቻይና፤ ኢራን፤ ባህሬን እንዲሁም የቬትናም መንግስታት የኢንተርኔት መረጃዎችን ለመቆጣጠር ከሚሰነዝሩት የድረገፅ ጥቃት በተጨማሪ ዜጎችን ለመሰለል የግለሰቦችን የኢሜል መረጃ የሚያጠምዱ ፕሮግራሞችን በመጠቀም ግንባር ቀደም ተብለዋል። ከበርካታ ሀገሮች እነዚህ አምስቱ የተመረጡትም ለኢንተርኔት ቁጥጥሩ የሚጠቀሙበት ቴክኒዎሊጂ መራቀቅና በዚህ ስለላ መሠረትም ጋዜጠኞችና ዜጎቻቸዉን በማሰራቸዉ እንደሆነ የRSF የዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ተመራማሪ ግሬግዋ ፑዤ ገልፀዋል። በተለይም ቻይና የኤሌክትሮኒክ መከላከያዋ ከዓለም ምናልባትም የረቀቀ ተብሎ ሲገመት ይህንኑ ቁጥጥሯን ለማጠናከር የግል ኢንተርኔት ኩባንያዎች ዜጎቿን ለመሰለል የሚረዱ ስልቶችን እንዲያቀርቡላት ማድረጓም ተገልጿል። ኢራን በበኩሏ የራሷን «ሃላል ኢንተርኔት» በሚል አቋቁማ የኢንተርኔት መረጃ ቁጥጥሯን አጠናክራለች። RSF የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂን ሳይኖራቸዉ አምባገነን መንግስታት ዜጎቻቸዉን ለመሰለል እንደማይችሉ በማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ ተባባሪ የኢንተርኔት ጠላቶች ሲል የመሰለያ ፕሮግራሞችን የሚሰሩና ለሀገራቱ የሚያቀርቡ ድርጅቶችንም ስም አጋልጧል። ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት ዜጎቻቸዉን በኢንተርኔት መረጃ ልዉዉጥ ሳይቀር እንዲቆጣጠሩና እንዲሰልሉ ስልቱን እያስተካከሉ የሚያቀርቡትን አምስት የግል ኩባንያዎችም የዘመኑ «ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች» ሲል RSF ወቅሷል።
ኢትዮጵያ ዉስጥ በርከት ያሉ ድረ ገፆች መነበብ እንደማይችሉ ተደጋግሞ የተገለፀ ጉዳይ ነዉ፤ መንግስት በበኩሉ ወቀሳዉን ቢያስተባብልም። የጥናቱ ተባባሪ ፀሐፊ ግሬግዋ ፑዤ ከአምስቱ ሀገሮች ተርታ በዘገባዉ ኢትዮጵያ ያልተጠቀሰችዉ የኢንተርኔት አገልግሎቱ እንደአምስቱ ሀገሮች የተስፋፋ ባለመሆኑ እንደሆነ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። ያ ማለት ግን ድርጅታቸዉ ክትትል አላደረገም ማለት አይደለም፤
«ባለፈዉ ዓመት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን እንደተደረገ እየተካተልን ቆይተናል። ማለትም TOR የተሰኘዉ ስልት ተዘግቷል፤ የሰዎች ኢሜይል ልዉዉጥ እየሰበረ የሚበረብረዉ DPI የተሰኘዉ ፕሮግራምም ስራ ላይ መዋሉን እናዉቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ከቶሮንቶ አንድ ዘገባ አዉጥቷል፤ ያም ኢትዮጵያ ዉስጥም አንድ የግለሰቦችን የኮምፕዩተር መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም መጠቀም መጀመሩን ይገልፃል። ተቋሙ ዛሬ ይፋ ባደረገዉ ዘገባ ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚካሄደዉን ቁጥጥር የሚያረጋግጥ መረጃ አካቷል።»
ግሬግዋ ፑዤ የጠቀሱት ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ይፋ ያደረገዉ ዘገባ የግለሰቦችን መረጃ የሚያጠምደዉ የኢንተርኔት ፕሮግራም ፊን ፊሸርስ እንደሚባል ይገልፃል። እንደዘገባዉም ኢትዮጵያ በተለይም ከተቃዉሞ ፖለቲካ ቡድኖች ጋ ግንኙነት ያላቸዉ ግለሰቦችን ለመከታተል ትጠቀምበታለች።
ኩባንያዉ ይህን የግለሰቦችን የኢንተርኔት መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ያዘጋጀዉ የግንቦት ሰባት አባላትን ፎቶዎች በመጠቀም እንደሆነም ዘገባዉ በመዘርዘር ምስሎቹን ያሳያል። ግሬግዋ ፑዤ፤
«ባለፈዉ የበጋ ወቅት ሲቲዚን ላብ ፊን ፊሸር የተሰኘዉ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ዉስጥ ሥራ ላይ መዋሉን ደረሰበት። የግንቦት ሰባትን «ስሙን በትክክል ብየዉ እንደሁ አላዉቅም» ምስል የያዘዉ ይህ ህገወጥ ፕሮግራም በርካታ የተቃዉሞ ፓርቲ አባላት በኢሜል አድራሻቸዉ እንዲደርሳቸዉ ተደረገ። እናም ይህ ምስል ትክክለኛ መልዕክት የያዘ ሳይሆን ያ መረጃ የሚያጠምደዉ ፕሮግራም ነዉ። ይህን ፕሮግራም አንዴ ኮምፕዩተርሽ ዉስጥ ከገባ ወደማዘዣዉ ኮምፕዩተር መረጃዎችን በሙሉ እየቀዳ ይልካል። ይህ ነገር ኮፕዩተርሽ ዉስጥ ካለ እያንዳንዷ የምትፅፊያት ነገር ፕሮግራሙን ወደላከዉ አካል ይሸጋገራል።» እሳቸዉ እንደሚሉትም ሲቲዚን ላብ ባደረገዉ ክትትል የግለሰቦችን መረጃ እየቀዳ የሚልከዉ ህገወጥ ፕሮግራም ትዕዛዝ አስተላላፊ የኮምፕዩተር መረጃ ማከማቻ የሚገኘዉ እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን ደርሶበታል። ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንተርኔት ላይ የሚከናወነዉን ጥብቅ ቁጥጥር እና ስለላ አስመልክቶችም ሲቲዚን ላብ ይፋ ያደረገዉን አዲስ መረጃ በማካተት ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ዘገባ ይፋ እንደሚያደርግም ከወዲሁ ጠቁመዋል።

Ethiopian opposition says members beaten, illegally detained

Ethiopian opposition says members beaten, illegally detained


By Aaron Maasho
ADDIS ABABA (Reuters) - An Ethiopian opposition group accused police and security officials of beating, illegally detaining and abducting more than 150 of its members between July and September this year.
The Horn of Africa country has won international plaudits for delivering double-digit growth for much of the past decade, but rights groups often accuse the government of using state institutions to stifle dissent and silence political opposition.
Addis Ababa, long seen by the West as a bulwark against militant Islam in the Horn of Africa, denies charges that it is quashing dissent.
In a 39-page report launched on Thursday, the Unity for Democracy and Justice (UDJ) detailed what it said were "gruesome rights violations" committed against its supporters and members.
"One hundred and fifty members and supporters of the party have been subject to severe beatings, illegal detentions and abductions by police and security officials," party chairman Negasso Gidada told reporters.
"We are asking the government to stop these human rights violations and take those responsible to justice," said Negasso, who served as the country's president from 1995 to 2001, before joining the opposition.
A government spokesman declined to comment saying it had to receive the report.
Earlier this month, Human Rights Watch said many former detainees - including politicians, journalists and alleged supporters of insurgencies - were slapped, kicked and beaten with sticks and gun butts during investigations at Addis Ababa's Federal Police Crime Investigation Sector, known as Maekalawi.
Ethiopia intensified its clampdown on peaceful dissent after the disputed 2005 election, the New York-based watchdog said.
Back then, the disputed polls ended in violence and the killing of 200 people. Opposition candidates won 174 seats but many did not take them up, saying the vote was rigged.
In an interview with Reuters this month, Prime Minister Hailemariam Desalegn said the government was not to blame for the opposition's poor showing.
He has also accused some opposition party members of collaborating with rebel groups the government had previously labelled as terrorist organisations.
But UDJ's leaders deny any links with the outlawed rebel groups, and warn the government that "stifling" dissent may encourage violence in the country.
"We are not requesting anything from the government side, we are requesting a level playing ground," Girma Seifu, a senior UDJ official and the sole opposition politician in Ethiopia's 547-seat parliament.
(Editing by James Macharia and Alison Williams)