Tuesday, November 8, 2016

የዲያስፖራዉ ተፅዕኖ በኢትዮጵያ ተቃውሞ

የአስቸኳይ ጊዜ ከታወጀ ወዲህ መንግስት የሞባይል ኢንተርኔትና በርካታ የማህበራዊ ድረ-ገጾችን ዘግቷል፡፡ በርካቶች እርምጃውን ከጊዜው ጋር የማይሄድ ጨቋኝ መንግስት የሚከተለው የኃይል አካሄድ ነው ሲሉ ይተቹታል፡፡ መንግስት በበኩሉ እርምጃዎቹ ሀገሪቱን ለተጨማሪ አለመረጋጋቶች የሚዳርጉ አደገኛ አስተያየቶችን ለማስቆም አስፈላጊ እንደነበር ይሟገታል፡፡

በሳምንቱ መጨረሻ ፒያሳ ትደምቃለች፡፡ ሱቆች እና መዝናኛዎችን በያዘው የአራዳ ገበያ ላይ ወጣቶች ተሰብስበው እየተዝናኑ ነው፡፡ ፊታቸው በፈገግታ ፈክቶ እስክስታ ይወርዳሉ፡፡ ምሽቱን በውዝዋዜ ያሳልፋሉ፡፡ የአዲስ አበባ እንዲህ አይነቱ ህይወት ሀገሪቱ ያለችበትን እውነት በቀላሉ የሚያስረሳ ነው፡፡ 
ስርዓትን ለማስከበር በሚል መንግስት ያወጀው እና ለስድስት ወር የሚቆየው የአስቸኳይ ጊዜ ድንጋጌ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ሳምንታት ቢያልፉም መዲናይቱ አይሞቃት አይበርዳት ሆናለች፡፡ አዲስ አበባ ባለፈው ዓመት ጥቅምት ወር በኦሮሚያ ከተቀሰቀሰው እና በኋላ ላይም ወደ አማራ ክልል ከተዛመተው ተቃውሞ በአንጻራዊነት ራሷን ከልላ ቆይታለች፡፡
ከመስከረም ሃያ ዘጠኙ አዋጅ በኋላ ግን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ቁንጥጫው የተሰማቸው ይመስላል፡፡ የኢንተርኔት እና የማህበራዊ ድረ-ገጾች መዘጋታቸው የቀን ተቀን እና የስራ ህይወታቸው ላይ ተጽእኖ አሳርፏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ስለ ማህበራዊ ድረ ገጾች ያላቸውን አመለካከት በይፋ ያወጡት አዋጁ ከመታወጁ አስቀድሞ ነው፡፡ 
Berlin Demonstration von Oromo-Aktivisten (DW/H. Kiesel)
በመስከረም በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ማህበራዊ ድረ-ገጾች እንዴት ተቃውሞዎችን እያቀጣጠሉ እንደሚገኙ ገልጸው ነበር፡፡ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አባባል የተዛቡ መረጃዎች በማህበራዊ ድረ-ገጾች እየተዛመቱ በተለይ ወጣቶችን እያሳሳቱ ነው፡፡ “ማህበራዊ ድረ-ገጾች የህዝብን ጥያቄ ለራሳቸው መጠቀሚያ ማድረግ የሚፈልጉ ጽንፈኞችን እና ዝና ወዳዶችን የልብ ልብ ሰጥቷቸዋል” ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡ 
የኢትዮጵያ ተቃውሞዎችን አስመልክቶ  በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ አብዛኞቹ አስተያየቶች የሚጻፉት ከኢትዮ-አሜሪካ ዳያስፖራዎች ነው፡፡ እነዚህ ዳያስፖራዎች በኢንተርኔቱ ዓለም ከፍተኛ ተደማጭነት ያካበቱ እና በሀገር ቤት ባለው የፖለቲካ ሂደት ላይም ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ናቸው፡፡ እንደ አቶ ልደቱ አያሌው ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት የዳያስፖራው ተጽእኖ ያሳስባቸዋል፡፡ 
“በጣም አዋኪዎች ናቸው፡፡ አዎንታዊ ሚና እየተጫወቱ አይደለም፡፡ ችግሩ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ይጨቁናል፡፡ ህዝቡ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ላይ በጣም ተስፋ በመቆረጡ ከአትላንቲክ ባሻገር ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን መስማት ጀምሯል፡፡ እነሱ የራሳቸው የሬድዮ፣ ቴሌቪዥን እና መገናኛ ብዙሃን ስላላቸው ህዝቡ ጋር በቀላሉ ይደርሳሉ፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ግን ይህ አይነት የመገናኛ ዘዴ የላቸውም፡፡ መንግስት እዚህ ያሉትን ህጋዊ እና ሰላማዊ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ባዳከመ ቁጥር በውጭ ያሉ ጽንፈኛ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ይበልጥ ያጠናክራል” ይላሉ አቶ ልደቱ፡፡ 
የማህበራዊ ድረ-ገጾች ተፅእኖ እንዲህ ሊጎላ የቻለው መንግስት ነጻ የሀገር ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን እንዲያድጉ ባለመፍቀዱ እንደሆነ የሚጠቁሙ አሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ቢያደርግ ኖሮ ለዳያስፖራ አቀንቃኞች የተጋነኑ ትርክቶች አጸፋዊ ምላሽ ይኖር ነበር ሲሉ ይከራከራሉ፡፡ በመሬት ላይ ያለው እውነታ እንደሚያመለክተው ግን የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ለማገናዘብ አልቻለም፡፡ ይልቁኑ የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃኑን ወይ ብቻቸውን መተው አሊያም ሙሉ ለሙሉ መጠርቀም መርጧል፡፡ 
Berlin Demonstration von Oromo-Aktivisten (DW/H. Kiesel)
ከተቃውሞው ጋር በተያያዘ በሰፈነው ውጥረት መሀል ቁጣ፣ መራር ትችት፣ ስሞታ እና አሳዛኝ ሁነት ኢትዮጵያውያን ዘላቂ መፍትሄ እንዳይፈልጉ ምክንያቶች ሆነዋል፡፡ አቶ አበበ ኃይሉ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ጠበቃ ናቸው፡፡ የኃይለስላሴ መንግስትን የገረሰሰው የ1966ቱ አብዮት ሲፈነዳ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበሩ፡፡ የመፍትሄ ፍለጋውን ጉዳይ ከኢትዮጵያውያን አስተሳሰብ እና ይትባህል ጋር ያዛምዱታል፡፡  
“አብሮ መብላቱን እንጂ አብሮ መስራቱን እናውቅበትም፡፡ ስለ ኢትጵያውያን አስተሳሰብ አንድ ነገር መገነዘብ አለብህ፡፡ ከ16ኛው ከፍለዘመን እስከ 18ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ  በመገለል ነው የኖርነው፡፡ ስለዚህ የራሳችንን ስነ ልቦና እና አስተሳሰብ አዳብረናል፡፡ የኢትዮጵያ አስተሳሰብ ክብ ነው፡፡ አብያተ ክርሰቲያናቱ ከብ ናቸው፣ መስጊዶቹ ክብ ናቸው፣ የምንበላው እንጀራም ክብ ነው፡፡ ሁሉ ነገር ክብ ነው፡፡ በክብ አስተሳሰብ በተመሳሳይ ነገር ላይ ዝም ብለህ ትከራከራለህ እንጂ ውሳኔ ላይ አትደርስም” ሲሉ አቶ አበበ፡፡
 ጄምስ ጄፍሪ/ተስፋለም ወልደየስ
ሒሩት መለሰ
DW

ስለዚች ሀገር ማን ይጨነቅ

አንዱን ብሔር ጠልተን ሌላ መውደድ ማላገጥ ነው!!!
አንድ ሰው አማራን ጠልቶ ኦሮሞ ሊወድ አይችልም፤ጉራጌን ጠልቶ አፋርን ሊወድ አይችልም ትግራይ ጠልቶ ትግራይን ወይም ሌላ ህዝብ ሊወድ ኣይችልም።
አንተ ማን ነህ? ኢትዮጵያዊ !
ምን አገባ? ያገባኛል! ኢትዮጵያዊ ዜጋ ነኝ ድምፄ በየትኛውም መንገድ አሰማለው ለኢትዮጵያ ይጠቅማል ያልኩትን ሀሳብና መንገድ እከተላለው ኢትዮጵያ አይጠቅምም፣ይጎዳል ባልኩት መንገድ አልሳተፍም፣ለሆዴም አልገዛም።ለአገር መቆርቆር ፖለቲከኛ ካስባለ ***አዎ ፖለቲከኛ ነኝ***።የአገር ጥቅም ከሚያስጠብቁ ዜጎች ጋር አብሮ መስራት ከዚህ በላይ የሚያስደስት ነገር ምን አለና።

ስለዚች ሀገር ማን ይጨነቅ
አንድ ሀገር ! አንድ ህዝብ ! አንድ ባንዴራ !
ዘላለማዊ ፍቅር፤ አንድነት፤ ክብር፤ ለኢትዮጵያ ሀገራችን ይሁን !!!
ስለዚች ሀገር ማን ይጨነቅ???

ለምንድን ነው እርስ በእርስ እየተሻኮትን ለወያኔ እድሜ የምንጨምርለት?

የኢትዮጵያ ህዝቡ አንድ በሆነበት ሰዓት በፖለቲካው ድርጅቶች ርዕዮተዓለም መከፋፈል ምክንያት ህዝቡን ከጨቋኝ ስርዓት መታደግ ያልተቻለበት ግዜ ላይ መሆናችንን አስተውለናል ካላስተዋልን እናስተውል እንጂ! ዛሬ በዚህ ወሳኝ ትግል ምዕራፍ በሆንበት ወቅት ላይ ሆነን አንድነታችን ካልታየ ነገ ደግሞ እንደፈራነው ስንታገል የነበርነው ድርጅት እራስ በራሳችን መሻኮት ልንጀምር ነው ማለት ነው ኧረ ጠንቀቅ እንበል!!
ኢትዮጵያ ውስጥ የሐይማኖት፣ የፖለቲካ፣የጎሳ ችግርች ሲፈጠር እንደ እሳት አደጋ አላርም እየነፉና እየከነፉ መሮጥና ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ብቻ ግን መሆን የለበትም፡፡መፍቴውን ማበጀት ያስፈልጋል።መፍቴው ደግሞ ልዩነታችንን ወደ ኋላ ትተን ህዝባችንን መታደግ ነው መሆን ያለበት! ያለበለዚያ ‹‹በአህያ ቆዳ የተሰራ ቤት፣ ይፈራርሳል ‹‹ጅብ የጮኸ ዕለት...›› እንዳይሆን አንድነታችንም የዘይትና የውሃ አይነት እንዳይሆን ማንም ቢሄድ፣ ማንም ቢመጣ የማይነቃነቅና መሰረተ ፅኑ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ሆኖ እንዲዘልቅ ወደ ታች ወርደን እናጥብቀው፡፡
ለፖለቲካ ድርጅቶች እውነት ለኢትዮጵያ ህዝብ ቆመናል ካልን አንድ የሚያረገን፣ የምናብርበት ግዜ አሁን ነው። ከዚህ የከፋ የጭቆናና የአፈና ዘመን አታሳዩን! ለህዝባችን በአንድ ላይ እንቁም !ዛሬ ህውሃት በወንዝ ላይ የወደቀ ዛፍ በሆነበት ግዜ እኛ የወንዙን ውሀ መልቀቅ ሲገባን የሀሳብ ልዩነት ገደለን። የነፃነት ጉዞ መጨረሻው ያማረና ጣፋጭ ነች። ድል ነፃነት ለናፈቀው ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

Friday, November 4, 2016

Calls for Theresa May to help British man jailed in Ethiopia

The family of Andy Tsege are demanding greater efforts to secure his release after being informed his life may be in danger.

Andy Tsege. Picture: Reprieve
There are calls for the Prime Minister to intervene in the case of a British man who is in prison in Ethiopia after the Foreign Office admitted there were concerns for his safety.
Andy Tsege was illegally seized while at an international airport in Yemen and taken to Ethiopia, where he had already been tried and found guilty of treason in his absence.
He was born Ethiopia but as an outspoken critic of the government he was granted asylum and British citizenship 30 years ago.
He has now been detained for more than two years, but despite the controversial manner of his conviction and imprisonment, the British government has never demanded his release.
Mr Tsege's partner Yemi Hailemariam says she has been 'termed a terrorist'
Mr Tsege's partner Yemi Hailemariam and his family say they are increasingly worried
The British embassy in Addis Ababa has provided some consular assistance, but Mr Tsege's family say not enough has been done to help him.
Last weekend the Foreign Office contacted his partner Yemi Hailemariam to say they had received information his life may be in danger.
Four days later, British officials have still not secured access to him to check on his well-being.
The human rights group Reprieve have written to Foreign Secretary Boris Johnson to express its concern.
"This situation is extremely troubling - it is not overstating matters to say that there is no evidence that Andy is still alive," it wrote.
Campaigners have called for the release of the Briton held in Ethiopia
Campaigners are demanding Mr Tsege's release
Its director Maya Foa said it was proof the approach taken by British officials was not working, and that the situation needed to be escalated with the involvement of Theresa May.
The Foreign Office told Sky News: "(We) are working hard to make sure his welfare is protected.
"After being notified of an incident in the prison in Ethiopia, our Ambassador immediately contacted the relevant authorities to request action to ensure his health and safety."
But Mr Tsege has not been seen by British officials since August, and his family say they are increasingly worried about his condition.

UK refused access to British father ‘in fear for his life’ on Ethiopia’s death row


The British Foreign Office (FCO) has failed for a week to confirm the safety and wellbeing of a British father held on death row in Ethiopia, despite having received reports last weekend that his life was in danger.
Last Saturday (28th), the family of Andargachew ‘Andy’ Tsege, from London, were told by British officials in Ethiopia that Mr Tsege had indicated that he was ‘in fear for his life’, following disturbances at the prison where he is held. Mr Tsege has been imprisoned unlawfully in Ethiopia since 2014, when he was kidnapped at an international airport and rendered to the country. He is held under an illegal sentence of death, which was imposed in absentia in 2009 in relation to his vocal criticisms of Ethiopia’s ruling party.
Concerns for Mr Tsege’s wellbeing have been growing this week, after the Foreign Office indicated to Mr Tsege’s family that it has been unable to establish consular access to him to check on his wellbeing. Yesterday, Minister Tobias Ellwood said in a written statement to MPs that the FCO had not seen Mr Tsege since August this year – an admission which appeared to contradict a recent claim by the Foreign Secretary, Boris Johnson, that “regular consular access” was “now in place.”
The latest concerns for Mr Tsege come amid criticism of the Government’s approach to his case. The FCO has focused recently on requesting legal access for Mr Tsege – a request which the Ethiopian Prime Minister promised to honour in June this year, but has since reneged upon. International human rights organisation Reprieve – which is assisting Mr Tsege – has argued that requesting legal access is ineffectual, because the Ethiopian Government has already stated that there is no legal route by which Mr Tsege will be allowed to challenge his death sentence. Reprieve has asked the UK Government to request Mr Tsege’s return home to his family in Britain, but the FCO has refused to do so.
Torture is common in Ethiopian prisons, and experts such as the UN Special Rapporteur on Torture have previously expressed concerns about Mr Tsege’s wellbeing. Parliament’s Foreign Affairs Committee is currently monitoring Mr Tsege’s case as part of an ongoing inquiry into the FCO’s human rights work overseas.
Commenting, Maya Foa, a director at Reprieve, said:
“It’s shocking that Andy could be in mortal danger, and yet British officials – who haven’t seen him since August – seem unable or unwilling to check that he is alive and well. Andy’s partner and children in London are sick with worry for him, and their concerns are worsening with every hour that passes. Andy has already suffered a catalogue of abuses – from an unlawful in absentia death sentence, to kidnap, rendition, torture, and over two years’ illegal detention. Andy is now in fear for his life – what more will it take for the British government to stop cowtowing to the Ethiopians, stand up for the rights of this innocent British father of three, and secure his return home to his family in London?”
Reprieve.org.uk

Open Letter to the Government of Ethiopia- HRW

Armed security officials watch as protesters stage a protest against government during the Irreechaa cultural festival in Bishoftu, Ethiopia on October 02, 2016.
Armed security officials watch as protesters stage a protest against government during the Irreechaa cultural festival in Bishoftu, Ethiopia on October 02, 2016.

አዲሱ ካቢኔ የምሁራንና የባለሞያዎች መንግሥት ነዉን?

የኢትዮጵያ መንግስት አዲስ ካቢኔ ማወቀሩን ተከትሎ አስተያየቶች ከየአቅጣጫው እየጎረፉ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አዲስ የሚያዋቅሩት ካቢኔ የፓርቲ አባላት ያልሆኑ የምሁራን እና የባለሙያዎች (ቴክኖክራቶች) ስብስብ እንደሚይዝ ጥቆማ ሰጥተው ነበር፡፡ የሚኒስትሮቹን ሹመት ከቃላቸው አንጻር የሚመዝኑ ጥያቄዎችን ማንሳት ጀምረዋል፡፡













በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም የካቢኔ መዋቅር ካሉ 30 ሚኒስትሮች መካከል ሲሶው ያህል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ምርምር ማዕከላት የመጡ ናቸው፡፡ በህዝብ ዘንድ እምብዛም ከማይታወቁት ከእነዚህ ተሿሚዎች ውስጥ የተወሰኑት ከሚመሩት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ጋር የተያያዘ የትምህርት እና የስራ ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ከዚህ ቀደም በተቋሞቻቸው ያካበቱት የስራ ልምድ እንደ መመዘኛ መስፈርት ተወስዶላቸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ለተወካዮች ምክር ቤት ትናንት ሲናገሩ “እውቀት እና ክህሎት” ያላቸውን እነዚህን ተሿሚዎች ለማግኘት ብዙ አፈላልገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈልጌ አገኘኋቸው ያሏቸው ሚኒስትሮችም ቢሆኑ ግን ከትችት አላመለጡም፡፡ ከተቃዋሚዎች እስከ የማህበራዊ ድረ-ገጽ ተሳታፊዎች የሚኒስትሮቹን “አዲስነት እና ብቃት” ጥያቄ ውስጥ ከትተዋል፡፡
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ከሚኒስትሮቹ ውስጥ ሁለቱን በምሳሌነት ያነሳሉ፡፡ ምሁራን ናቸው ቢባሉም በተቋሞቻቸው ውስጥ እያሉ ይፈጽሙት የነበረው ተማሪዎችን ለጉዳት የሚያጋልጥ ነበር ሲሉ ይከሳሉ፡፡
“እነዚህ ምሁራን የሚባሉት ለኢህአዴግ ሲሰሩ የነበረ ሲያገልግሉ የነበሩ ናቸው፡፡ የምሰማቸው ስሞች አዲስ አይደሉም፡፡ ኢህአዴግን በማገልገል የታወቁ ነበሩ፡፡ አንዳንዶቹ የምናውቃቸው ወለጋ ዩኒቨርስቲ፣ ሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የነበሩ ሰዎች የኦሮሞ ወጣቶች ያሳስሩን ነበር ሲሉ ሲከሷቸው የነበሩ ናቸው” ይላሉ ዶ/ር መረራ፡፡
Äthiopien Ministerpräsident Hailemariam Desalegn (DW/Y. Gebireegziabher)
   ሌሎች ተቺዎች ደግሞ በዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች ላይ ጽሁፎችን ማሳተም እንዴት የሚኒስትር መምረጫ መስፈርት ውስጥ እንደገባ ይጠይቃሉ፡፡ ካቢኔው “የዩኒቨርስቲ ሴኔት መሰለ” ያሉም አሉ፡፡እንዳንዶች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ሌሎች መስሪያ ቤቶች ውስጥ ኃላፊ ሆኖ መስራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ከመምራት የተለየ እንደሆነ ተከራክረዋል፡፡
በትናትናው የካቢኔ ምስረታ ሹመት ያገኙት አዲሱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ግን ሚኒስትሮቹ “አቅም አላቸው” የሚል ምልከታ አላቸው፡፡ “የተሻለ የሚናገረው ውጤት” እንደሆነ እና ጊዜውን ጠብቆ ያንን መመልከት እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ፡፡
“እኔ በአዎንታዊ ጎኑ ነው የማየው፡፡ ደግሞ ውጤት ነው የተሻለ የሚናገረው፡፡ ብዙ ጊዜ እንግዲህ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ የተሻለ ተናጋሪዎች እና ብዙ የሚናገሩ ሰዎች የተሻለ ፖለቲከኞች የሆኑ አድርጎ መገመት አለ፡፡ አሁን ግን ይህ መሰረታዊ ለውጥ ይመስለኛል፡፡ የተሻለ ስራ የሚሰሩ፣ ሰርተው የሚያሰሩ፣ በስራ የሚያምኑ፣ በሀገር በዜጋ ተጠቃሚነት የሚያምኑ ሰዎች ስራ ውስጥ በሚገቡበት ጊዜ የሚበዙት ጥያቄዎች እንደዚህ ይቀጥላሉ ብዬ አላምንም፡፡ ዜጎችን አሳትፈው ሀገሪቷን ወደ ተሻለ መምራት ይችላሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡   
 “አዲሱ ካቢኔ በእርግጥ የቴክኖክራቶች ስብስብ ነው?” የሚለው ጥያቄ ማከራከሩን ቀጥሏል፡፡ የተሿሚዎችን የትምህርት እና የስራ ልምድ ቃኝተው በምሁርነታቸው እና ባለሙያነታቸው የተስማሙ እንዳሉ ሁሉ “የእነርሱ በካቢኔው መካተት ብቻ የጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለማርያምን አስተዳደር የቴክ ኖክራት መንግስት አያስብለውም” የሚሉ አሉ፡፡
ለመሆኑ የቴክኖክራት መንግሰት ማለት ምን ማለት ነው? በኒውዮርክ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ፕሮፌሰር ለሆኑት ጆሽዋ ተከር የቴክኖክራት መንግስት ማለት የሙሉ ጊዜ ፖለቲከኞች ያልሆኑ ሚኒስትሮችን በአባልነት ያቀፈ ነው፡፡እነዚህ ሚኒስትሮች የፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን እንደማይጠበቅባቸው ነገር ግን በተሰማሩበት ዘርፍ ባለሙያ መሆን ግድ እንደሚላቸው ይተነትናሉ፡፡
“በብያኔው መሰረት  የቴክኖክራት መንግስት ማለት የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች፣ ምክትላቸው እና በመንግስት ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ያላቸው ሰዎች መንግስት ከመሰረተው የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ከአጋሮቹ ሳይሆኑ ሲቀር ነው፡፡ ቴክኖክራት መንግስት የምንልበት ምክንያት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለመምራት የሚያስፈልግ ክህሎት ያላቸው ነገር ግን ራሳቸው ፖለቲከኛ ያልሆኑትን ስለሚያካትት ነው፡፡ የቴክኖክራት መንግስት የሚለውን ቃል ከፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም ተወካዮች ጋር ንኪኪ የሌለላቸውን ሰዎች ለመግለጽ ነው፡፡ ሰዎቹ ባለሙያ መሆን ይኖርባቸዋል” ብለዋል ፕሮፌሰሩ፡፡    
ዶ/ር ነገሪ የአዲሱ ካቢኔ አባላት ቴክኖክራቶች መሆናቸውን በልበ ሙሉነት ይመሰክራሉ፡፡   
“እነዚህ ምሁራን በእውነትም ቴክኖክራት ናቸው፡፡ ለምሳሌ አንዳንዶቹን [ብናይ] እንደ ተባበሩት መንግስታት ባሉ ዓለም አቀፍ ትልልቅ ተቋማት አልፈው በአህጉር ደረጃም ከዚያም በሀገር ውስጥም ትልልቅ ድርጅቶችን የመሩ ነገር ግን በፖለቲካ ቅርበት የማያምኑ እና የሀገር ፍቅር ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ኃላፊነቱ ከተሰጣቸው በኋላ ዝም ብለው የተሰጣቸውን የሚቀበሉ ይሆናሉ ብዬ አላምንም”  ሲሉ እምነታቸውን  ይገልጻሉ   
የኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትሩ ይህን ቢሉም በብዙዎች ዘንድ ግን ሹመቱ ያልተመለሱ ብዙ ጥያቄዎችን እንደደቀነ ነው፡፡

ተስፋለም ወልደስ
አዜብ ታደሰ
DW