Wednesday, April 29, 2015

ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች እየለጠፉ መሆናቸው ተገለፀ

የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች በመለጠፍ ላይ መሆናቸውን ሰማያዊ ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አሳወቀ፡፡ ፓርቲው ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አዲስ አበባ ውስጥ በትምህርት ቤቶች፣ በቤተ ክርስቲያናት፣ በወታደራዊ ካምፖች እንዲሁም በሌሎች ፓርቲዎች ዕጩ ፖስተሮች ላይ ያለ ፓርቲው ዕውቅና የሰማያዊ ፓርቲ ፖስተር እየተለጠፈ እንደሚገኝና ይህም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሚፈጽሙት ተግባር እንደሆነ ገልጾአል፡፡
ይህንንም ተከትሎ ምርጫ ቦርድ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በተከለከሉ ቦታዎች ፖስተር እየተለጠፈ ነው›› የሚል ቅሬት በማቅረቡ ምን አልባት አባላት ተሳስተው ለጥፈው ይሆናል ብለው ፖስተሮቹን እንዳነሱ የገለጸው የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ ወጣት እያስፔድ ተስፋዬ ፖስተሮቹን ካስነሱ በኋላ በድጋሜ እነዚህ ቦታዎች ላይ ያለ ሰማያዊ እውቅና ፖስተሮቹ ተለጥፈዋል ብሏል፡፡ ፖስተሮቹን ለሁለተኛ ጊዜ ለማንሳት የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትም መታሰራቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ወጣት እያስፔድ አክሎም ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ እውቅና ውጭ ፖስተሮች እየተለጠፉ ያሉት ገና ሰማያዊ ፖስተር ባልለጠፈባቸው አካባቢዎች ነው፡፡ እኛ ስናነሳ ደግመው ይለጥፋሉ፡፡ ለማንሳት የሚሄዱ አባላትንም ያስራሉ፡፡ ይህን እኩይ ድርጊትም ገዥው ፓርቲ ነው የሚፍጽመው ብለን እናምናለን፡፡ ይህን እያደረገ ያለው ሰማያዊን ሆን ብሎ ለመክሰስ ነው፡፡ ይህንንም ለምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡ ፓርቲውም ‹‹ይህን ድርጊት ፓርቲያችን እንደፈፀመው ተደርጎ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት በኩል የተሰጠው ማሳሰቢያ ፓርቲያችን አይመለከተውም›› ሲል በደብዳቤው አሳውቋል፡፡

ኢህአዴግ ሰማያዊን ለማውገዝ በየ አካባቢው የአደባባይ ስብሰባ መጥራቱ ተሰማ

ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ ለነገ ሀሙስ አዲስ አበባ ውስጥ በየ ወረዳው በሚገኙ ሜዳዎች የአደባባይ ስብሰባዎችን መጥራቱን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ህዝባዊ ንቅናቄ›› የተባሉት የአደባባይ ስብሰባዎች ባለፈው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ፈጥረዋል በሚል በገዥው ፓርቲ እየተከሰሱ ያሉትን በተለይም ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ የተጠሩ ናቸው ተብሏል፡፡ በህዝባዊ ስብሰባዎቹ ከካድሬዎች ውጭ ተቃውሞ የሚያሰሙ ኢትዮጵያውያን እንዳይገኙ የኢህአዴግ አባላት ብቻ እንዲገኙ በደብዳቤ እንደተጠሩ ታውቋል፡፡
መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ እርምጃ ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ላይ ለጉዳዩ ትኩረት አልሰጠም በሚል ተቃውሞ ከገጠመው በኋላ ሰማያዊ ፓርቲ ከተቃውሞው በስተጀርባ እንዳለበት ከመክሰሱም ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች በጠራቸው ሰልፎች ሰማያዊን ሲያወግዝ ተስተውሏል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ ኢህአዴግና የመግንስት ተቋማት ስሙን ከማጥፋት ካልተቆጠቡ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስደውና ከዚህም ባሻገር ሌሎች ተከታታይ እርምጃዎችን እንደሚወስድ በመግለጽ ህዝብ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡

Tuesday, April 28, 2015

የዞን 9 ጦማርያን የማአከላዊ ስቃይና መብት ጥሰት

ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ( ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት) በተለይ
- ምን ላድረግልህ 
- ታደሰ ወይም ጥጋቡ ( የሽፋን ስም )
- ደስታ ወይም ሃሰን ( የሽፋን ስም)
- ዬሃንስ
- ፈይሳ
ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - ሚያዝያ 18(ከሰአት ከ8-10) ፣ ግንቦት 11 ( ከምሽቱ 2 ሰአት- ሌሊቱ 6 ሰአት) እና ሰኔ 26 ( ከምሽቱ 4 ሰአት -ሌሊቱ 7 ሰአት) እና በማእከላዊ ምርመራ በልዬ ሁኔታ በቆየሁባቸው 76 ቀናት
የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ላይ ቢሮ ቁጥር 5.፣ 32፣30 ፣ የስብሰባው አዳራሽ እና ከዋናው ህንጻ ተነቅሎ በሚገኝ ህንጻ ውስጥ በሚገኝ ጨለማ ክፍል
ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
- የተያዝኩበት ማግስት አቶ ምን ላድርግልህ የተባለ የምርመራ ክፍሉ አባል ብሄሬን ጠይቆኝ ኢትዬጲያዊ መሆኔን እና በተለያዬ ብሄሮች ስር ራሴን አንደማልገልጽ እና በጥቅል ኢትዬጲያዊ መባል አንደምመርጥ ነገርኩት ተነስቶ ድብደባ ጀመረ ፡፡ በጥፌና በእርግጫ በተደጋጋሚ መታኝ፡፡ ሌላው መርማሪ ንግግራችንን ያልሰማ ከውጪ መጥቶ ያለምንም ጥያቄ ድብዳባውን ተቀላቀለ ፡፡ ከዱላው በተጨማሪ በጣም አጸያፌ ስድቦችን ሰደቡኝ፡፡ ብሄርህን የካድክ በብሄርህ የምታፍር ይሉኝም ነበር፡፡
- ከሚያዝያ 19-ሰኔ 26 2006 ባሉት ቀናት ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ አያድንህም በማለት አጸያፌ ቃላት በመሰንዘር ሰውነቴ ሊቋቋመው የማይችለው የአካል እንቅስቃሴ እንዳደርግ ተገድጃለሁ ፡፡
- በተለይ ግንቦት 11 ላይ የዞን9 አላማ ጠይቀውኝ ስናገር እውነቱን አውጣ በሚል በተደጋጋሚ ድብደባ የደረሰብኝ ሲሆን ደስታ እና ሃሰን የተባሉ ሽፋን ስሞች የሚጠቀመው መርማሪ በተደጋጋሚ ባደረሰብኝ ጥፌ ድብዳባ ጆሮዬ ተጎድቶ በህመም ላይ እገኛለሁ፡፡
- ቤቴ የተገኘው ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ያሉትን ቃላት ነጣጥለው የሰጠሁት ቃል ውስጥ ያስገቡትን፣ ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ያለው ሙሉው ነው አንጂ ተነጣጥሎ ቃሌ ውስጥ ተካቶ አልፈርምም በማለቴ አቶ ፈይሳ፣ አቶ ዬሃንስ ( ስማቸው የሽፋን አንደሆነ የምጠረጥረው) ታደሰ( ጥጋቡ በሚልም ይጠራል) ከፍተኛ ድብደባ አድርሰውብኛል፡፡
- ድብደባውም ጨለማ ክፍል ውስጥ በማስገባት አፌ ውስጥ ካልሲ በመወተፍ እግሮቼን ከላይ፣ ውስጥ እግሬን እና ከውስጥ ባቴን ታፋዬን እንዲሁም ጀርባዬን በእንጨትና በኮምፒውተር ገመድ ገርፈውኛል ፡፡
- የምርመራ ክፍሉ ወለል ላይ በደረቴ አንዲሁም በጀርባዬ እያገላበጡ በማስተኛት መላ ሰውነቴን ረግጠው ተራምደውብኛል፡። አፌን ሳይቀር ረግጠውታል፡። ይህንን በሚያደርጉበት ሰአት ሞራል የሚነካ ስድብ ይሳደቡ ነበር፡፡ ሁሉም የአካል ሆነ የስነልቦና ጥቃት ሲደርስብኝ እጄ በካቴና ታስሮ ሲሆን በቀን 15 ደቂቃ በላይ የጸሃይ ብርሃን የማላይበት ቀዝቃዛ ክፍል ውስጥ ለ76 ቀናት ቆይቻለሁ፡፡
*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው


ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ( ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት) በተለይ ሳጅን ምን ላድርግልህ ፣ ም/ሳጅን አብተው 

ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - ሚያዝያ 22 ( ከምሽቱ 2 ሰአት ገደማ)፣ ሚያዝያ 23 ከጠዋቱ 4 ሰአት፣ ግንቦት 6( ከምሽቱ 3 ሰአት ገደማ)፣ ሚያዝያ 24 ከጠዋቱ 4 ሰአት እና ከሚያዝያ 22 እስከ ግንቦት 6/2006 ድረስ ባሉት ቀናት ከእሁድ በስተቀር 

የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ላይ ቢሮ ቁጥር 30፣ 32 በ1981 አም በተሰራው ህንጻ ላይ 2ተኛ ፎቅ በስተግራ ጥግ በኩል ያለ ቢሮ

ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
- በምርመራ ወቅት ዛቻ እና ማስፈራሪያ የደረሰብኝ ሲሆን በተጠራሁባቸው ቢሮ ውስጥ ሁሉ በጥፌ ተደብድቤያለሁ ፡፡ በጥፌ መመታት የተለመደ ነበር ፡። በተደጋጋሚ ክፍተኛ ስፓርት የሰራሁ ሲሆን በቀን 10 ደቂቃ ብቻ የፀሃይ ብርሃን እያየሁ በጠባብ ክፍል ውስጥ ያለምንም ተፈጥሮ ብርሃንና መጸዳጃ ለ 76 ቀናት ቆይቻለሁ፡፡

- ጫማዬን አውልቄ በባዶ እግሬ አንድቆም ከተደረኩ በኋላ እግሮቼ ጣቶች ላይ መርማሪዎቹ በጫማቸው በሃይል በመርገጥ እግሬ ላይ ከባድ ድብደባ አድርሰውብኛል፡፡ ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስም እጄ እንደታሰረ አናቴ ላይ አድርጌ እንድመረመር ተገድጄ ነበር፡፡

- የምሽት ምርመራዎች ወቅት በአብዛኛው ጊዜ እጄን ወደላይ አድርጌ እንድመረመር እገደድ ነበር ፡። ምርመራው ቀኑን ሙሉ የሚቆይ ሲሆን ምሽት እስከ ሌሊቱ ስድስተ ሰአት ድረስ ስፓርት በመስራት እና ፌቴን በማዞር እንድመረመር እገደድ ነበር፡፡

- ሰብአዊነቴን የሚነኩ ስድቦች ልክስክስ ፣ ውሻ መሳሰሉትን ስድብ በምርመራ ወቅት እሰደብ የነበረ ሲሆን አካለ ጎዶሎ ሆነህ ነው ከዚህ ቤት የምትወጣው ፣ ለግለሰብ መብት አንጨነቅም አንተን አንደፈለግን እነድናደርግ አሰራራችን ይፈቅድልናል የሚሉ ተደጋጋሚ ማስፈራሪያዎች ነበሩብኝ ፡፡

*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው



ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት እና የፌደራል ደህንነት መስሪያ ቤት አባላት መርማሪ ታደሰ ወይም ጥጋቡ ( ስሙ በትክክል የማላውቀው) በተለይ መርማሪ ምን ላድርግልህ መርማሪ ጽጌ መርማሪ አብዱልመጂድ
ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - በተያዝኩባቸው ቀናት በሙሉ በተለይ ሚያዝያ 17፣ ሚያዝያ 22 ሚያዝያ 25 እና ግንቦት 9
የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ቢሮ ላይ
ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
- በታሰርኩነት ወቅት ህጋዊ የእስር እና የብርበራ ትእዛዝ አልነበረም፡፡ ህጋዊ ያልሆነ ፍተሻ ከ12 ሰአት በኋላ አታድርጉ ብልም የሚሰማኝ አላገኘሁም ፡። ፍተሻው በከፍተኛ ማስፈራሪያ የታጀበ ነበር፡፡ ፓሊስ ጣብያ እሄዳለሁ ብለህ እንዳታስብ ራስህን ለምትሄድበት ቦታ አዘጋጅ እያሉ ከፍተኛ ስነልቦና ጫና አድርሰውብኛል
- በመጀመሪያው ቀን ፍርድ ቤት ስንቀርብ ትምህርቴን አጠናቅቄ ላስረክበው ያዘጋጀሁትን የመመረቂያ ጽሁፍ ፓሊስ መያዙን እና ኮፒ አድርጌ እንዳስረክብ ይፈቀድልኝ ብዬ ስጠይቅ ፍርድ ቤቱም መብቱ ነው ብሎ ትእዛዝ ቢሰጥም ፓሊስ ትእዛዙን ተግባራዊ አንዲያደርግ ብጠይቅ የማዕላዊ ወንጀል ምርመራ ሃላፊ ኢንስፔክተር “ፍርድ ቤት እኛን አያዘንም“ ” የት ያለህ መሰለህ” ዳኛዋ ታስረክብልህ” አንዲሁም “አንዲህ አይነት ጥያቄ ካነሳህ እርምጃ ይወሰድብሃል” የሚሉ ንግግሮችን ተናገረውኝ አንጓጠውኛል በዚህም ምክንያት መመረቂያ ጽሁፌን ማስረከቤ ተሰናክሏል፡፡
- በምርመራ ወቅት በዙ አጻያፌ ስድቦችን እየተሰደብኩ የምመረመር ሲሆን ከነሱም መካከል “የነጭ ተላላኪ የነጭ አምላኪ አገር ሻጭ ከሃዲ “ የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡
- የዞን 9 አላማ ተናገር ካልሆነ ያሉንን የምርመራ መንገዶች ተጠቅመን እንድታወጣ እናደርጋለን የሚለው ማስፈራሪያ በተደጋጋሚ በምርመራ ወቅት የደረሰብኝ ነው
- የሰጠሁት ቃል ላይ እኔ ያላልኩትን ጨምረው በፍርሃት ጥፋተኛ ነኝ ብዬ አንድፈርም ከመገደዴም በላይ የበላይ አካል ተቀባይ አንዲሆን በሚል እየቀያየሩ በተደጋጋሚ አስፈርመውኛል፡፡
*ይህ ጽሁፍ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው


ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ( ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት) በተለይ
- ምን ላድረግልህ 
- ታደሰ ወይም ጥጋቡ ( የሽፋን ስም )
- ደስታ ወይም ሃሰን ( የሽፋን ስም)
- ዬሃንስ
- ፈይሳ
ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - ሚያዝያ 18(ከሰአት ከ8-10) ፣ ግንቦት 11 ( ከምሽቱ 2 ሰአት- ሌሊቱ 6 ሰአት) እና ሰኔ 26 ( ከምሽቱ 4 ሰአት -ሌሊቱ 7 ሰአት) እና በማእከላዊ ምርመራ በልዬ ሁኔታ በቆየሁባቸው 76 ቀናት
የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ላይ ቢሮ ቁጥር 5.፣ 32፣30 ፣ የስብሰባው አዳራሽ እና ከዋናው ህንጻ ተነቅሎ በሚገኝ ህንጻ ውስጥ በሚገኝ ጨለማ ክፍል
ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
- የተያዝኩበት ማግስት አቶ ምን ላድርግልህ የተባለ የምርመራ ክፍሉ አባል ብሄሬን ጠይቆኝ ኢትዬጲያዊ መሆኔን እና በተለያዬ ብሄሮች ስር ራሴን አንደማልገልጽ እና በጥቅል ኢትዬጲያዊ መባል አንደምመርጥ ነገርኩት ተነስቶ ድብደባ ጀመረ ፡፡ በጥፌና በእርግጫ በተደጋጋሚ መታኝ፡፡ ሌላው መርማሪ ንግግራችንን ያልሰማ ከውጪ መጥቶ ያለምንም ጥያቄ ድብዳባውን ተቀላቀለ ፡፡ ከዱላው በተጨማሪ በጣም አጸያፌ ስድቦችን ሰደቡኝ፡፡ ብሄርህን የካድክ በብሄርህ የምታፍር ይሉኝም ነበር፡፡
- ከሚያዝያ 19-ሰኔ 26 2006 ባሉት ቀናት ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ አያድንህም በማለት አጸያፌ ቃላት በመሰንዘር ሰውነቴ ሊቋቋመው የማይችለው የአካል እንቅስቃሴ እንዳደርግ ተገድጃለሁ ፡፡
- በተለይ ግንቦት 11 ላይ የዞን9 አላማ ጠይቀውኝ ስናገር እውነቱን አውጣ በሚል በተደጋጋሚ ድብደባ የደረሰብኝ ሲሆን ደስታ እና ሃሰን የተባሉ ሽፋን ስሞች የሚጠቀመው መርማሪ በተደጋጋሚ ባደረሰብኝ ጥፌ ድብዳባ ጆሮዬ ተጎድቶ በህመም ላይ እገኛለሁ፡፡
- ቤቴ የተገኘው ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ያሉትን ቃላት ነጣጥለው የሰጠሁት ቃል ውስጥ ያስገቡትን፣ ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ያለው ሙሉው ነው አንጂ ተነጣጥሎ ቃሌ ውስጥ ተካቶ አልፈርምም በማለቴ አቶ ፈይሳ፣ አቶ ዬሃንስ ( ስማቸው የሽፋን አንደሆነ የምጠረጥረው) ታደሰ( ጥጋቡ በሚልም ይጠራል) ከፍተኛ ድብደባ አድርሰውብኛል፡፡
- ድብደባውም ጨለማ ክፍል ውስጥ በማስገባት አፌ ውስጥ ካልሲ በመወተፍ እግሮቼን ከላይ፣ ውስጥ እግሬን እና ከውስጥ ባቴን ታፋዬን እንዲሁም ጀርባዬን በእንጨትና በኮምፒውተር ገመድ ገርፈውኛል ፡፡
- የምርመራ ክፍሉ ወለል ላይ በደረቴ አንዲሁም በጀርባዬ እያገላበጡ በማስተኛት መላ ሰውነቴን ረግጠው ተራምደውብኛል፡። አፌን ሳይቀር ረግጠውታል፡። ይህንን በሚያደርጉበት ሰአት ሞራል የሚነካ ስድብ ይሳደቡ ነበር፡፡ ሁሉም የአካል ሆነ የስነልቦና ጥቃት ሲደርስብኝ እጄ በካቴና ታስሮ ሲሆን በቀን 15 ደቂቃ በላይ የጸሃይ ብርሃን የማላይበት ቀዝቃዛ ክፍል ውስጥ ለ76 ቀናት ቆይቻለሁ፡፡
*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው


ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ( ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት) መርማሪ የህይስ መርማሪ ጽጌ መርማሪ ታደሰ ( ስሙን እርግጠኛ ያልሆንኩት) 

ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት ማእከላዊ ምርመራ በቆየሁበት ጊዜ ሁሉ 
የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - ማእከላዊ ወንጀል ምርመራ

ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
-በውል በማላስታውሳቸው ቀናት እስከእኩለ ሌሊት ድረስ የቆየ ምርመራ ተደርጎብኛል
-ለ75 ቀናት በተለምዶው ሳይቤሪያ የሚባለው ቦታ በቀን 15 ደቂቃ ብቻ የጸሃይ ብርሃን ለማየት ተፈቅዶልኝ ከዚያ ውጪ ያለውን ጊዜ 24 ሰአት አንድ በር ተዘግቶብኝ ቆይቻለሁ፡፡
-አራት በአራት በሆነ በዚህ ክፍል ውስጥ ቁጥራቸው አስር ከሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ጋር ጤናዬን ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ ሁኔታ ውስጥ ነበርኩ
-በእስር በቆየሁባቸው ቀናት በቀዝቃዛው ሳይቤርያ ውስጥ በማሳለፌ በከፍተኛ ቅዝቃዜው የተነሳ ለጤና ጉዳት እና ለበሽታ ተዳርጌያለሁ
-ከፍተኛ እና ከአቅሜ በላይ የሆነ የአካል እንቅስቃሴ ያደረኩ ሲሆን በምርመራ ወቅት በተደጋጋሚ እመታ ነበር
-በዚህም የተነሳ ከፍተኛ የስነልቦና ጉዳት ደረሰብኝ ሲሆን በስተመጨረሻም ያላልኩትን አለ ተብዬ ፣ የማላምንበት እና ያልፈጸምኩትን ጥፋተኛ ነኝ ብለህ ፈርም በመባሌ ለመፈረም ተገድጃለሁ

*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው 



ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት እና የፌደራል ደህንነት መስሪያ ቤት አባላት መርማሪ ደስታ በዋናነት
ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - በተያዝኩባቸው ቀናት በሙሉ (በተለይ ሚያዝያ 18 በኋላ ባሉት የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት በሰፊው) 

የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ቢሮ ላይ
ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት

- በጠበቃ እና በቤተሰብ የመጎብኘት መብቴ ተጥሷል፡፡ ከተጎበኘሁም 10ደቂቃ ለማይሞላ ጊዜ በፓሊስ ተከብቤ ነበር፡፡

- በተደጋጋሚ በምርመራ ወቅት አመጽ ለማነሳሳት እነደጸፍሽ እመኚ እየተባልኩ በጥፊ እና በካልቶ ተደብድቤያለሁ፡፡

- በምርመራ ወቅት ልብሴን አስወልቀው አንድቀመጥ በማድረግ አይኔ ተሸፍኖ በምሽት ምርመራ ተደርጎብኛል፡፡

- ሙሉ ልብሴን እንዳወልቅ ተገድጄ ራቄቴን በወንድ መርማሪዎች ፊት ስፓርት አንድሰራ እገደድ ነበር ፡፡ “ሴትነትሽ አንዲህ ከሚዋረድ አመጽ እንዳነሳሳሽ እመኚ ተብያሁ”

- በሌሊት ግርፋት የሚፈጸምበት ክፍል ውስጥ ገብቼ ጫማሽን አውልቂ ተብዬ ጫማዬን አውልቄ ከቆምኩ በኋላ ውስጥ እግርሽን ከምትገረፊ አመጽ ማነሳሳትሽን አምነሽ ፈርሚ ተብያለሁ፡፡

- ሰጠሁት የተባለው ቃል ሰዎች በሚቀጥለው ክፍል እየተደበደቡ የጩኀት ድምጻቸው እየተሰማ ፈርሚ ተብዬ የተባልኩት ቦታ ላይ ሳላነብ በፍርሃት ፈርሜያለሁ።

- በተለያዬ ምርመራ ወቅቶች "ለነጭ አገሪትዋን የሸጥሽ ሸርሙጣ ውሻ ባንዳ..." አንዲሁም ለመጸፍ የሚከብዱ አፀያፈ ስድቦች በየቀኑ እሰደብ ነበር ፡፡

*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው

ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት እና የፌደራል ደህንነት መስሪያ ቤት አባላት መርማሪ ደስታ በዋናነት

ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - በተያዝኩባቸው ቀናት በሙሉ በተለይ ሚያዝያ 18 ,20, 21, 22, 23
የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ቢሮ ላይ
ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት

-መርማሪዬ ደስታ በተደጋጋሚ በጥፊ ይመታኝ ነበረ ሲሆነ ከዚህ ቤት የፈለግነውን ልናደርግሽ እንችላለን በአካል አትወጪም እያለ አስፈራርቶኛል

-የዞን 9 አባል አይደለሁም በማለቴ ፌቴን አዙሬ ከባድ የአካል አንቅስቃሴ የሰራሁ ሲሆን በተጨማሪም አላማቸውን ተናገሪ ሲለኝ የተለየ አላማ እንዳላቸው አላውቅም በማለቴ ሳታውቂ አንዴት አብረሻቸው ትውያለሽ ሸርሙጣ ብሎ በተደጋጋሚ ሰድቦኛል፡። ሌሎቹ መርማሪዎች አብረው ተቀምጠው በስድቦቹ ይስቁ ነበር

-ሌላኛው ተከሳሽ አጥናፍ መደብደቡን ፍርድ ቤት በመናገሩ አንቺ ትሞክሪውና ዋጋሽን ታገኛለሽ እኛ ፍርድ ቤት አያዘንም የግለሰብ መብትም አያሳስበንም ብሎኛል

-ጥጋቡ የሚባለው መርማሪ ምርመራ መሃል ደንገት በሩን ከፍቶ ገብቶ በጥፊ መቶኝ ይወጣ ነበር ( ስለምናወራው ጉዳይም ሆነ ስለምርመራው ሳይሰማ) እምቢ ካለችህ ልብሷን አስወለወቀህ ግረፋት ብሎ እኔን የተለመደውን ስድብ ሰድቦኝ ሄዷል

-በምርመራ ወቅት የዞን አባል ነኝ ብለሽ እመኚ ተብዬ ልብሴን አውልቄ ሙሉ እርቃኔን አንድመረመር ተገድጃለሁ ፡። በጥፊ እመታ የነበረ ሲሆን በዚህ ቀን ምርመራው ምሽት ላይ ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰአት ቆይቷል

-በተለምዶው ከምመረመርበት ቢሮ ውጩ አንደኛ ፎቅ አዳራሽ ውስጥ ለምርመራ ተወስጄ ልብሴን እንዳወልቅ እና የተለያዬ ለመናገር የሚከብዱ ስፓርታዊ አንቅስቃሴዎችን እንድሰራ ተገድጃለሁ፡፡ እንዲህ ከምትዋረጂ አመጽ ልናስነሳ ነበር ብለሽ ለምን አታምኚም እያለ ይመታኝ ነበር ፡፡ በጥፊው ተደጋጋሚነት የተነሳ ታምሜ ክሊኒክ ተመላልሻለሁ::

-በጋዜጠኝነት ሞያየ የተሳተፍኩበትን ስልጠናዎች ስናገር አንቺ ለምን ተመረጥሽ የኢቲቪ ጋዜጠኞች ለምን አይሄዱም አንቺ ለፈረንጅ ስለምትሰልዬ ነው ብሎኛል፡፡ በተጨማሪም ዞን9 ላይ የሚወጡት ጽሁፎች አንድ ገጠር ያለ ሰው ቢያነበው ለአመጽ የሚያነሳሳው ልማቱን የሚያጣጥል ነው ብሎ በተደጋጋሚ በጥፊና በካልቾ ተመትቻለሁ፡፡

-በተጨማሪም በተፈቺ እስረኛ ወደውጪ መልእክት ልከሻል በሚል ሰበብ ሌሊት ተጠርጬ በዱላ ሲዛትብኝ አርፍዷል

-በእስሩ ወቅት ከማህሌት ፋንታሁን ጋር ለብቻችን ከሰው አንዳንገናኝ ተደርገን ቆይተናል፡፡

*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው

Source: zone9

Sunday, April 26, 2015

Continued detention of Ethiopian journalists unacceptable – UN human rights experts


GENEVA (24 April 2015) – The Special Rapporteur on freedom of opinion and expression, David Kaye, and the Special Rapporteur on freedom of peaceful assembly and of association, Maina Kiai, today said the detention of the six so-called “Zone Nine” bloggers and three other journalists in Ethiopia over the past year has been “absolutely unacceptable”.
The bloggers, who used an online platform to report on social and political issues in Ethiopia, were arrested on April 25 and 26 last year and have remained in detention ever since. The Federal First Instance Court of Ethiopia reportedly charged them under the 2009 Anti-Terrorism Proclamation for “working with foreign human rights organizations and inciting violence through social media to create instability in the country.” Their trial has been adjourned several times.
“The continued detention of these journalists is absolutely unacceptable and particularly worrying as the country prepares to hold parliamentary elections on May 24. The open public debate that should mark any democratic process is obviously undermined if journalists are silenced through harassment or detention,” Kaye said.
“Muzzling the media and limiting public debate is never a good response to the threats of violence and terrorism,” continued Kaye. “Prosecuting journalists who are legitimately exercising their right to freedom of expression creates a system of self-censorship in which journalists must choose between limiting their speech, living in exile, or facing years in prison.”
“To comply with its obligations, Ethiopia must respect the rights to assemble peacefully and associate freely, online as well as offline, including those of people expressing dissenting views,” added Kiai.
The Special Rapporteurs noted that the Ethiopian authorities had already publicly recognized the need to ensure freedom of the press.
“During the last Universal Periodic Review of Ethiopia’s record in the UN Human Rights Council, the Government accepted a number of recommendations relating to the promotion of freedom of expression and encouraging political debate ahead of elections. Fulfilling these commitments is essential for the promotion of democracy and the rule of law.”
ENDS
David Kaye (USA) was appointed as Special Rapporteur on the promotion and protection of the right to freedom of opinion and expression in August 2014 by the United Nations Human Rights Council. Learn more, log on to: http://www.ohchr.org/EN/Issues/FreedomOpinion/Pages/OpinionIndex.aspx
Maina Kiai: (Kenya) was appointed by the United Nations Human Rights Council as the first Special Rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly and of association on May 2011. Learn more, log on to: http://www.ohchr.org/EN/Issues/AssemblyAssociation/Pages/SRFreedomAssemblyAssociationIndex.aspx
The UN Special Rapporteurs are part of what is known as the Special Procedures of the Human Rights Council. Special Procedures, the largest body of independent experts in the UN Human Rights, is the general name of the independent fact-finding and monitoring mechanisms of the Human Rights Council that address either specific country situations or thematic issues in all parts of the world. Special Procedures’ experts work on a voluntary basis; they are not UN staff and do not receive a salary for their work. They are independent from any government or organization and serve in their individual capacity.
- See more at: http://www.ohchr.org/EN/NewsEvents/Pages/DisplayNews.aspx?NewsID=15890&LangID=E

ደህንነቶች የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ ነው

መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያውያን ላይ የፈፀመውን የጭካኔ እርምጃ ለመቃውም በጠራው ሰልፍ ላይ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲው እንዲለቁ ደህንነቶች ጫና እያደረጉ መሆኑ ታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ደህንነቶች ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ እንደሆነና ከፓርቲው ከለቀቁ እንደሚፈቷቸው መግለጻቸው ታውቋል፡፡

በተለይ ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትን ወይንሸት ሞላንና ዳንኤል ተስፋዬን ሌሊት ሌሊት ከታስሩበት በማስወጣት ለረዥም ሰዓት ከታሰሩበት ጉዳይ ጋር የማይገናኝ ከፍተኛ ምርመራ እንደሚያደርጉባቸውና ከፓርቲው ካልለቀቁ በስተቀር እንደማይፈቱ እንደሚያስፈራሩዋቸው ተገልጾአል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው አብዛኛው ምርመራ ፍርድ ቤት ላይ ፖሊስ ካቀረበባቸው ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ክስ ጋር የማይገናኝና በፓርቲው ውስጣዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በሰልፉ ወቅት ታፍሰው ከታሰሩት መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አባል ያልሆኑትን ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነኝ፡፡ ፓርቲው ብጥብጥ እንዳስነሳ ልኮኝ ነው ወደ ሰልፉ የመጣሁት›› ብለው እንዲፈርሙ እያስገደዱ መሆኑን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ በርካታ የገዥው ፓርቲ አባላትም በአፈሳው ወቅት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ከቀበሌ የምስክር ደብዳቤ አምጥተው መለቀቃቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ደህንነቶች የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ ነው

መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያውያን ላይ የፈፀመውን የጭካኔ እርምጃ ለመቃውም በጠራው ሰልፍ ላይ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲው እንዲለቁ ደህንነቶች ጫና እያደረጉ መሆኑ ታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ደህንነቶች ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ እንደሆነና ከፓርቲው ከለቀቁ እንደሚፈቷቸው መግለጻቸው ታውቋል፡፡

በተለይ ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትን ወይንሸት ሞላንና ዳንኤል ተስፋዬን ሌሊት ሌሊት ከታስሩበት በማስወጣት ለረዥም ሰዓት ከታሰሩበት ጉዳይ ጋር የማይገናኝ ከፍተኛ ምርመራ እንደሚያደርጉባቸውና ከፓርቲው ካልለቀቁ በስተቀር እንደማይፈቱ እንደሚያስፈራሩዋቸው ተገልጾአል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው አብዛኛው ምርመራ ፍርድ ቤት ላይ ፖሊስ ካቀረበባቸው ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ክስ ጋር የማይገናኝና በፓርቲው ውስጣዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በሰልፉ ወቅት ታፍሰው ከታሰሩት መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አባል ያልሆኑትን ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነኝ፡፡ ፓርቲው ብጥብጥ እንዳስነሳ ልኮኝ ነው ወደ ሰልፉ የመጣሁት›› ብለው እንዲፈርሙ እያስገደዱ መሆኑን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ በርካታ የገዥው ፓርቲ አባላትም በአፈሳው ወቅት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ከቀበሌ የምስክር ደብዳቤ አምጥተው መለቀቃቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የሰው ልጅ አውሬነትና የሰው ልጅ ቅዱስነት በሊቢያ!

የሰው ልጅ አውሬነትና  የሰው ልጅ ቅዱስነት በሊቢያ!
  • ለክርስቲያን ወገኖቹ ሲል የተሰዋው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም
  • አራት ኤርትራውያን “ሙስሊም ነን” ብለው ከISIS አመለጡ
  • በሊቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መንግስት አላነጋገረንም አሉ    
    ባለፈው እሁድ ነበር በአረመኔው የአሸባሪ ቡድን (ISIS) 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች መቀላታቸውን የሰማነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሦስቱ ጥገኝነት ተከልክለው ከእስራኤል የመጡ ኤርትራውያን ነበሩ ተብሏል፡፡ አንደኛው ደግሞ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ነው፡፡ ጀማል ራህማን ይባላል፡፡ ሶማሌላንድፕሬስ ድረገጽ እንደዘገበው፤አሸባሪው ቡድን ጀማል ሙስሊም በመሆኑ ለጊዜው አልፈለገውም ነበር፡፡ ሆኖም ቡድኑ የጀማልን ጓደኛ ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን መርጦ ሲወስድ አላስቻለውም፡፡ በፈቃደኝነት ተቀላቅሏቸው ሄደ፡፡ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ግድያ እንዳይፈጽም የቻለውን ያህል ቢያደርግም አልተሳካለትም፡፡ በመጨረሻም ሃይማኖታቸውን እንዲቀይሩ ተጠይቀው “አይሞከርም!”ካሉት ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ጎን በISIS አሸባሪ ቡድን ተቀልቷል፡፡ ሶማሌላንድፕሬስ የሐረር ተወላጁን ጀማል ራህማንን የገለጸው፤ “ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ሰማዕት!” በማለት ነው፡፡ (ከዚህ በላይ ቅድስና ከየት ይመጣል!?) በአንድ ቦታ ነው የሰው ልጅ አውሬነት እና የሰው ልጅ ቅድስና የተገለጠው። በአንድ በኩል አረመኔው ISIS፤ በሌላ በኩል ለክርስቲያን ወገኖቹ ሲል የተሰዋው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም!
አሁንም ግን በሊቢያ የኢትዮጵውያን ስደተኞች መከራ አላበቃም፡፡ አሁንም አሸባሪው ቡድን በርካታ ኢትዮጵያውያንን መያዙ ተሰምቷል፡፡ በትሪፖሊ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ አገራቸው መመለስ ቢፈልጉም ማን እንደሚወስዳቸውና የት እንደሚመዘገቡ እንደማያውቁ ጠቁመው እስካሁን ከመንግስት ወገን ያነጋገራቸው እንደሌለ ሰሞኑን ለቪኦኤ ገልጸዋል፡፡ በግብጽ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙሃሙድ ድሪል ስልክ ላይ ደጋግመው ቢደውሉም እንደማይነሳ በምሬት ተናግረዋል- ስደተኞቹ፡፡ አንድ በጣም ተስፋ የቆረጠ ኢትዮጵያዊ፤“የኢትዮጵያ መንግስት የሚረዳን አይመስለኝም” ብሏል - ለቪኦኤ፡፡ ዜጎች እንዲህ በባዕድ አገር፤ “ከአሁን አሁን እያዝ ይሆን?” እያሉ ከሞት ጋር በተፋጠጡበት የጭንቀት ሰዓት መንግስት “አለሁላችሁ” ሊላቸው ይገባል፡፡ (ዜጎችን ከሞት ከመታደግ የላቀ ልማት የለም!)
በነገራችሁ ላይ በሊቢያ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ብቻ አይደሉም፡፡ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት ስደተኞች በጀልባ ወደ አውሮፓ ለመሻገር እየተጠባበቁ ሲሆን በአሸባሪው ቡድን ተይዘው  አሰቃቂ የሞት እርምጃ እንዳይወሰድባቸው በመፍራት በርካታ ስደተኞች በአንድ ጀልባ ላይ እየተሳፈሩ የባህር ሲሳይ በመሆን ላይ ናቸው፡፡ ባለፈው ቅዳሜ በሜዲትራኒያን ባህር በሰጠመችው ጀልባ ከ800 በላይ ስደተኞች ለሞት የተዳረጉ ሲሆን ከሟቾቹ መካከል ኤርትራውያን፣ ሶማሊያውያንና ኢትዮጵያውያን-ይገኙበታል ተብሏል፡፡ በቁጥር የሚበዙት ግን  ኤርትራውያን እንደሆኑ ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡ (ለእነሱም ዜጎቼ የት ገቡ የሚል መሪ ይስጣቸው!)
ወንድማማቾቹ ከ ISIS አመለጡ
የ19 ዓመቱ ሃቤን እና የ14 ዓመት ታዳጊ ወንድሙ ሳሙኤል፤ከኤርትራ ተሰደው ሊቢያ የገቡት የአውሮፓ አገራትን አልመው ነበር፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ግን በአይምሬው አሸባሪ ISIS እጅ ውስጥ ገቡ፡፡ ታጣቂዎቹ ሃይማኖታቸውን ሲጠይቋቸው፣ሙስሊም መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ ክርስቲያን ነን ቢሉ የሚጠብቃቸውን ያውቃሉዋ፡፡
“ክርስትያኖች ነን፤ ነገር ግን እምነታችንን መካድ ነበረብን፡፡ ያለበለዚያ ታጣቂዎቹ ይገድሉናል፡፡ ወይ በጥይት ይመቱናል አሊያም  ይቀሉናል” በማለት ሃቤን ለሜይልኦንላይን ድረገፅ አስረድቷል፡፡ ሃቤን እንደሚለው፤ጓደኞቹ ክርስቲያን በመሆናቸው በISIS ግድያ ተፈጽሞባቸዋል፡፡
“ጓደኞች ነበሩኝ - ኤርትራዊና ግብፃዊ - ክርስትያን መሆናቸውን በመናገራቸው ተገድለዋል”
እነ ሃቤን የጓደኞቻቸው መገደል ጥልቅ ሃዘን ውስጥ እንደሚከታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ነገር ግን እነሱም እንደማይቀርላቸው ያውቃሉ፡፡
“ክላሺንኮቭ የታጠቁ ሰዎች ይመጡና እምነትህን ይጠይቁሃል፡፡ ክርስትያን ከሆንክ ወስደው ይገድሉሃል፡፡ አንገትህን ይቀሉሃል ወይም በጥይት ጭንቅላትህን ይመቱሃል፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ክርስትያኖችን እንደዚያ አድርገዋል” ብሏል - ሃቤን ለሜይልኦንላይን፡፡
ሃቤን እና ወንድሙ ህይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው ከኤርትራ ሊቢያ ድረስ የተጓዙት የነገን ብሩህ የአውሮፓ ህይወት አልመው ነው፡፡ ሁለቱ ታዳጊዎች አንገታቸው ላይ ያሰሩትን የእንጨት መስቀል ከልብሶች ስር ደብቀው ክርስቲያን መሆናቸው እንዳይታወቅ በማድረግ ከሞት ተርፈዋል፡፡ ሌሎች ኤርትራውያን ክርስትያኖች ደግሞ ሃይማኖታቸውን ለመለወጥ መገደዳቸውን ለሜይልኦንላይን ተናግረዋል፡፡
የ18 ዓመቱ አማን ሲናገር፤ “አንገቴ ላይ የእንጨት መስቀል አስሬ ነበር፤ ለህይወቴ ስል ግን መጣል ነበረብኝ፡፡ ታጣቂዎቹ ክርስትያኖችን ፍለጋ ነበር የመጡት፡፡ አህዛብን እንገድላለን ሲሉ ከአንገቴ ላይ በጥሼ ጣልኩት” ብሏል፡፡
“አረብኛ እናገራለሁ፤ ስለዚህ ክርስትያን እንዳልሆንኩና የእነሱ እምነት ተከታይ እንደሆንኩ አስመስዬ ቀረብኩ፤ እነሱም አመኑኝ” ሲል ከቡድኑ አሰቃቂ ግድያ ያመለጠበትን ሁኔታ አስረድቷል፡፡
ሃቤን እና ታናሽ ወንድሙ ሳሙኤል እንዲሁም አማን እና ተስፋለም፤የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ሲሆኑ ከ15 ቀናት በፊት አስቸጋሪውን የሜዲትራንያን ባህር በጀልባ በማቋረጥ አውሮፓ ለመግባት ችለዋል፡፡ ባለፈው እሁድ በአሸባሪው ቡድን ISIS አንገታቸውን የተቀሉት ኢትዮጵያውያንም ባህር ተሻግረው አውሮፓ ለመግባት ሲጠባበቁ ነበር ተብሏል፡፡
 ለሟቾች ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እንመኛለን!!
Source: addisadmassnews