Monday, July 6, 2015

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ካሳ ተከፍሏቸው ከእስር እንዲፈቱ ተጠየቀ

ኢሳት ዜና (ሰኔ 28 2007 አ/ም)
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የአንድ አመት የእስር ቤት ቆይታ ሲከታተል የቆየው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የካሳ ክፍያ በመፈጸም አቶ አንዳርጋቸውን በአስችኳይ እንዲፈታ ማሳሰቡን አለማቀፍ ሚዲያዎች ዘገቡ።
ባለስምንት ገጽ ውሳኔውን በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን በኩል ለኢትዮጵያ ያቀረበው ድርጅቱ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በእስር ቤት ቆየታቸው ጭካኔ የተሞላበት ኢ-ሰባዊ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው መግለጹን ዘ-ፋይናንሺያል ኤክስፕረስ የተሰኘ
ጋዜጣ ዘግቧል። በድርጅቱ የስቃይ ሰለባ ግለሰቦችን ጉዳይ የሚከታተል ገለልተኛ አካል የአቶ አንዳርጋቸውን የእስር ቤት ሁኔታ ሲከታተል ከቆየ በኋላ ጥሪውን ማቅረቡን ጋዜጣው አመልክቷል።
አቶ አንዳርጋቸው ከእስር ተፈተው ወደ መኖሪያ ሀገራቸው ብሪታኒያ ከመመለሳቸውም በፊት የኢትዮጵያ መንግስት በቂ የካሳ ክፍያን መፈጸም እንዳለበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በውሳኔው ገልጿል ።
በቅርቡ የብሪታኒያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በአⶆ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ሲፈጸሙ የቆዩ ኢ-ሰባዊ ድርጊቶችን ይፋ ማድረግ ተከትሎ በርካታ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ስጋታቸውን በአዲስ መልክ በመግለጽ ላይ ናቸው ።
የብሪታንያ መንግስት ያሳየው ዲፕሎማሲያዊ መለሳለስ ለአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር አለመፈታት ምክኒያት ሆኗል ሲሉ ድርጅቶቹ ተቃውሞአቸውን እንደገለጹ ዘ-ፋይናንሺያል ኤክስፕረስ ጋዜጣ ዘግቧል።
የብሪታኒያ መንግስት ጠንካራ አቋም ማሳየት መጀመሩን የዘገበው የእንግሊዝ ዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ በበኩሉ የሀገሪቱ የፖርላማ አባላትን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ሀገሪቱ የተባበሩት መንግስት ድርጅት አይነትን አቋም እንድትወስድ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን ዘግቧል::
የብሪታኒያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፊሊፕ ሀሞንድ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጉዳይ ትብብርን የማያሳይ ከሆነ የሀገሪቱ ግንኙነት ሊሻክር እንደሚችል ማሳሰባቸው ይታወሳል:: የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ላስተላለፈው ውሳኔ እስካሁን ከኢትዩጵያ መንግስት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም::

Sunday, July 5, 2015

በእስር ስትጉላላ የከረመችው የሰማያዊ ወጣት ምስጋና አቀረበች

ወይንሸት ሞላ የሰማያዊ ፓርቲ ካፈራቸው ትንታግ ታጋዮች አንዷ ናት። ለወራት ወያኔ በሃሰት ከሶ ሲያንገላታት ከርሟል፣ እነሆ ከእስር ተፈታ “ትግሉ ይቀጥላል!” ትለናለች።
Woyinshet Molla, Semayawi party member
ወይንሸት ሞላ
ምስጋናዬ ይድረሳችሁ!
ኢህአዴግ አይ ኤስ የተባለውን አራጅ ቡድን እናውግዝ ብሎ ራሱ ሰልፍ ከጠራ በኋላ ሰልፉ ሳይጀመርና እኔም መስቀል አደባባይ ሳልደርስ መስቀል አደባባይ ተገኝቼ እንደበጠበጥኩ በሀሰት ተከስሼ በታሰርኩባቸው ጊዜያት በተለያዩ መንገዶች ድጋፋችሁን ለሰጣችሁኝ ወገኖች ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡
ባልተገኘንበት አስረው፣ በሀሰት አስመስክረውብን፣ ወህኒ ቤት ሲያወርዱን ሞራላችን የሚሰበር፣ ወደኋላ የምንል ቢመስላቸውም እኛን ግን ይበልጡን እንድንጠነክር አድርጎናል፡፡
ወትሮውንም ወደ ትግሉ ስንገባ መስዋዕትነት እንደምንከፍል አውቀን ነው፡፡
በእስር ላይ እያለሁ ብዙ አሳዛኝ ነገሮች ተከስተዋል ነገር ግን ውድ ወንድማችን ታጋይ ሳሙኤል አወቀን ቀጥቅጠው መግደላቸው ከሁሉም በላይ ያሳዘነኛል። በኢትዮጵያ ታሪክ በተመሳሳይ ሁኔታ ግድያ የተፈጸመባቸው ታጋዮችን ለማግኘት ተቸግሬያለው። ሳሙኤል አወቀ የተገደለው በህሊናውና እና በማሰቡ ብቻ ነበር። ፍፁም ሰላማዊ ለሃገሩ እና ለወገኑ የሚጨነቅና ለባህልና ሃይማኖት ትልቅ ክብር ያለው ኢትዮጵያን የሚወድ ጀግና ነበር። ስለዚህ ተኪ የሌለው ታጋይና የትግል ጓደኛዬ በመሰዋቱ በጣም ተጎድቻለው።
እኔም በእስር ላይ ያሳለፍኩት ስቃይ እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነበር ግን ይህንን ልተወው ምክንያቱም ከዚህ በላይ ህይወቴንም ጭምር አሳልፌ ለመስጠት የወሰንኩበት የነፃነት ትግል ውስጥ ስለገባሁ የእስር ቤት ስቃይ የማይጠበቅ መከራ አይደለም።
የሳሙኤል አወቀ ድምጽ ከመቃብሩ ይጮሀል፤ ትግሉ ይቀጥል ትግሉን አፋፍሙት ይለናል፤ አደራ ይለምነናል። ዛሬ አንድ ወጣት በኑሮ ስኬታማ ለመሆን ብዙ አመራጮች ስለሚኖሩት ራስን ለነፃነት ትግል መስዋዕት ለማድረግ ፈታኝ የሆነበት ጊዜ ነው። ግን ደግሞ ኢትዮጵያዊ ነኝ ማለት የሚያስገርፍ እና ለእስር የሚዳርግበት፣ ዜግነታችን ውርደት የሆነበት ጊዜ ላይ በመሆናችን በኢትዮጵያ ሰላም፣ ዴሞክራሲ እና ብሄራዊ እርቅን ያማከለ አንድነት የግድ አስፈላጊ ነው።
ወትሮውንም ወደ ትግሉ ስንገባ መስዋዕትነት እንደምንከፍል አውቀን ነው፡፡ ፈጣሪ ከፈቀደው ሞትም ቢሆን ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነትና ነፃነት የሚጠየቀውን ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ መሆኔን እንድትረዱኝ እፈልጋለው።
ትግሉ ይቀጥላል!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ወይንሸት ሞላ

ወያኔ አርበኞች ግንቦት 7 የከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ለመደበቅ እየሞከረ ነው

ባለፉት ሦስት ቀናት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ትግራይ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የወያኔን ሃይል ገጥመው የወያኔ መኮንኖችን ጨምሮ በርካታ የወያኔ ሰራዊት አባላትን እንደገደሉ በቃል-አቀባያቸው አማካኝነት ለኢሳት ቴሌቪዥን ገልጸዋል። ለጥቀውም እስከ ትላንት ድረስ ውጊያው ቀጥሎ እንደሚገኝ በድጋሜ ዜናውን አብስረዋል።arbegnoch-ginbot7-fighters
በወያኔ ዘረኛና ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው የኢትዮጵያ ህዝብም ጆሮውን አቅንቶ ሁኔታውን በመከታተል ላይ ነው። ቀድሞውንም የወያኔ ሥርዓት ያለ ሃይል ትግል አይንበረከክም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካም ሆነ የሥርዓት ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በተቃውሞው ጎራ የተሰለፉት ተባብረው በወያኔ ላይ ክንዳቸውን ሲያሳርፉ ብቻ ነው ብለው የሚያምኑት ኢትዮጵያውያን አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት በከፍተኛ ደስታ ነው የተቀበሉት።
አንዳንዶች አርበኛውን በገንዘብ ለመደገፍ እና ለማጠናከር ከወዲሁ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
ይህ በዚህ እንዳለ በወያኔ ጎራ በኩል ይህን ጉዳይ በተመለከተ ምንም የተሰማ ነገር የለም። ጥያቄው… ለወትሮው ትንሽ ትልቁን “የግንቦት 7” አባል ነው ብሎ በመፈረጅ ንጹሃንን እስርቤት የሚወረውረው ወያኔ በይፋ ስለተከፈተበት ጦርነት ለምን ዝምታን መረጠ? ነው።
ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ ሥርዓት ህዝብ እጅግ እንደጠላውና ሆ ብሎ ሊነሳበት እንዳቆበቆበ ይረዳል። ስለዚህም ጉዳዩ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆኖ የህዝብ መነጋገሪያ እንዲሆን አይፈልግም። ያ ሆነ ማለት የተዳፈነው ፍም እሳት ፊቱ ላይ ተረጨ ማለት ነው።
ለዚህም ይመስላል በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለማብረድ ድምጹን አጥፍቶ መውተርተርን የመረጠው።
ሌላው ተጨማሪ ማስረጃ ደግሞ ወያኔ በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለመመከት ወደ አካባቢው እያሰማራ ያለው የጦር ክፍል ከአንድ ጎሳ የውጡና ቀደም ሲል በጡረታ ተሰናብተው ወያኔ ከወልቃይት ህዝብ ላይ ነጥቆ በሰጣቸው ለም መሬቶች ላይ የግብርና ስራ እያካሄዱ የሚገኙ የቀድሞ የህወሃት አባላት መሆናቸው ነው።
Source: ecadforum

‹‹የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ነው!››



(ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሳሙኤል አወቀ መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከተናገሩት)
ስለ ሳሙኤል ግድያ ብዙ ነገር ተብሏል፡፡ ብዙዎች ቁጭታቸውን ገልፀዋል፡፡ ለእኔ ከሳሙኤል አወቀ ግድያ ምን እንማራለን? የሚለው ነው ትልቁ ቁም ነገር፡፡ ሳሙኤል በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ንግግር ተናግረው የተገደሉ ሰዎች ጋር የሚመደብ ሰው ነው፡፡ የሳሙኤል ትውልድ አካል በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡ እንደገሚገሉት እያወቀ፣ ነገር ግን ያ ሞቱ ከንቱ እንዳይሆን አስፈላጊውን መረጃ አስቀምጦልናል፡፡ አቡነ ጴጥሮስ መንፈሳዊ አባት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስተምረው ህዝቡ ለጣሊያን እንዳይገዛ ሰብከው ተገድለዋል፡፡ ለዚህም ሀውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ይህ መታሰቢያ ለኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ልዕልና እና የአልበገሬነት ምልክት ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፡፡
የአቡነ ጴጥሮስን ታሪክ ተማሪዎችም ይማሩበታል፡፡ የሳሙኤልን ንግግርም ወደፊት እድሜ ከሰጠን እኛ እናየዋለን፡፡ እኛ ባንደርስበት እንኳ መጪው ትውልድ ሳሙኤል ለሀገሩ ሲል ዋጋ እንደከፈለ መታወሱ የማይቀር ነው፡፡ ምክንያቱም ይህን አይነት ታሪክ የሰሩ ሰዎች በህዝቡ ውስጥ ትንሽና የተመረጡ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም ሳሙኤል ከመካከላችን የተገኘ ልዩና ዕንቁ የኢትዮጵያ ልጅ ነው፡፡ ሳሙኤል እኔ በምመራው ፓርቲ፣ በእኔ ትውልድ ውስጥ እንዲህ አይነት ታሪክ መስራቱ ትልቅ የመንፈስ ጥንካሬ ሰጥቶኛል፡፡ ህይወት ምን እንደሆነም አስተምሮኛል፡፡
በህይወት መቆየትን እንደ ትልቅ ነገር ቆጥረውት ከትግል እንድንወጣ የሚመክሩን በርካቶች ናቸው፡፡ እነሱ የሚሉን ህዝብ ሲጨቆን ዝም በሉ ነው፡፡ ሳሙኤል ደግሞ እንዲህ አይነቱን ነገር መስራት እንደሌለብን በደሙና በአንድ በማትተካ ህይወቱ አሳይቶናል፡፡ እንደዚህ የሚሉንን ሰዎች ለመናቅ ሳሙኤልን ማሰብ ብቻ በቂ ነው፡፡ ገንዘብ ሲቸግረኝ ሳሙኤል ህይወቱን ማጣቱን ማስታወስ ይገባኛል፡፡ ለህይወት ትኩረት ስሰጥ፣ መኖር ስመኝ፣ መንፈሴ ሲላላ በእኔ ትውልድ ዘላለማዊ ሆኖ ያለፈውን ሳሙኤልን ማስታወስ አለብኝ፡፡ የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ይሰጣል፡፡ በእኔ እምነት ሳሙኤልን የገደሉት በግል ስለሚጠሉት አይመስለኝም፡፡ ሳሙኤል የብሩህ አእምሮ ባለቤት ነው፡፡ የመረጃና የአቋም ሰው ነው፡፡ በጣም ጠንካራ ልጅ ነው፡፡ ይህን አስተሳሰቡንና እምነቱን ነው የጠሉት፡፡ ይህ ሲጠፋ ለሌሎቹም መቀጣጫ መሆኑ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሳሙኤል ደም እኛ ተሰባስበናል፡፡ መፍራትና ወደኋላ ማለት እንደሌለብንም አስተምሮናል፡፡ ከዚህ ባለፈ በዚህ ትግል ውስጥ ለነገ የሚባል ነገር እንደማይሰራ የሳሙኤል ግድያ አሳይቶናል፡፡
የሰው ልጅ በባህሪው ሞኝ ነው፡፡ ዛሬን ብቻ አይደለም ዘላለምንም የምንኖር ነው የሚመስለን፡፡ ለሳሙኤል ግድያ ግን ህይወት ምን ማለት እንደሆነች አሳይቶናል፡፡ ዛሬውኑ ልትጠፋ የምትችል ከንቱ እንደሆነች አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም የሳሙኤል ሞት ትርጉም ያለውን ነገር ዛሬ አድርጌ እንዳልፍ እንጅ ለነገ እንዳልል ትልቅ ትምህርት ሆኖኛል፡፡ ዕቅድ አንድ ነገር ነው፡፡ ሆኖም ሞት አብሮን ያለ መሆኑን ተረድተን ለሀገራችን የሚጠቅመውንና ዛሬ ማድረግ ያለብንን ነገር ዛሬውኑ መስራት እንዳለብን ነው፡፡ እንደ ሳሙኤል በዚህ አለም የማያልፍ ነገርን ሰርተን ማለፍ አለብን፡፡ በነፃነት ትግል ውስጥ ሳሙኤል ስም ሲነሳ ይኖራል፡፡ እንደ ሳሙኤል በህይወት ትርጉም ያለው ነገር መስራት ለህይወትም ትልቅ ትርጉም ይሰጣል፡፡ በኢትዮጵያ ከሉሲ ጀምሮ በሚሊዮን የሚቆጠር ሰው ሞቷል፡፡ ዋናው ነገር ግን 80ና 90 ቆይቶ መሞት አይደለም፡፡ እንደ ሳሙኤል በአጭር እድሜው ያመነበትን ሰርቶ መሞት ትልቅ ትርጉም አለው፡፡
እኛም 90ና 80 አመትን መጠበቅ ሳይሆን በ27 አመትም መቀጨት እንዳለ አውቀን አሁን መስራት ያለብንን በፍጥነት ማከናወን አለብን፡፡ በዚህ ግለኝነት፣ አግበስባሽነት በነገሰበት ሀገር ላይ ህይወትን ያህል ነገር ከፍሎ በደሙ ለእኛው ትውልድ አስተምሮ ሄዷል፡፡ ለሀገር፣ ለህዝብና ለእውነት መቆም የተከበረ ስራ መሆኑን ያውም ህይወቱን እንደሚያጣ አውቆት ለዓላማው በፍላጎቱ ሲሞት ከዚህ በላይ አስተማሪ አያስፈልግም፡፡ በወቅቱ ‹‹ይህ ትውልድ አይረባም፣ ሀገሩን አይወድም፣ ከዝሙትና ከመጠጥ ያለፈ ነገር አያውቅም፣ አይችልም›› የሚባለውን ሳሙኤል የሚባል ብርቱ ልጅ ከመካከላችን ወጥቶ እውነት እንዳልሆነ በተግባር አሳይቶናል፡፡ በዚህ ዘመን ደግሞ የጠፋው ከሳሙኤል አይደለም፤ ለራሳችን የቃል ኪዳን ሰው መሆን ነው፡፡ የሳሙኤልን ቃል የራስ አድርጎ መውሰድ፡፡ ክብር፣ ሞገስ፣ እውነትና ቃል ኪዳን ለራስ ነው፡፡ እሱ አከበርንለትም አላከበርንለትም የሚያምንበትንና የድርሻውን ሰርቶ ሄዷል፡፡ ለራሳችን ለእውነት፣ ለህዝብ፣ ለሀገር መቆም የሚያስከብር መሆኑን አስተምሮን አልፎአል፡፡
ይህንን ሳሙኤል እያወቀው ሞቶ የሰጠንን ክብር፣ ቃልና መስዋዕትነት ሳናጓድል አደራ የማንበላ ሰዎች እንዳንሆን፡፡ እኔ የምታገለው ለማንም አይደለም፡፡ ይች እግዚያብሄር የሰጠኝ እድሜ ትርጉም ያላት ሆና እንድታልቅ ስለምፈልግ ነው፡፡ ሳሙኤል በልጅነት እድሜው ቤተሰቦቹን አሳዝኖ ለእኛ ዋጋ ከፍሎልናል፡፡ ይህን ቃል ኪዳን ድርጅታችን እንደ ሰማያዊ፣ እያንዳንዳችን እንደ ግለሰብም፣ እንደማህበረስብና እንደትውልድም እንዳንበላ ብርታቱን ይስጠን እላለሁ፡፡

UN demands release of British activist jailed in Ethiopia amid torture fears

The Foreign Office has pushed for consular access to Andargachew Tsige with no tangible results, since the British citizen was abducted in Ethiopia a year ago
Yemi Hailemariam campaigns in London to demand the immediate release of her partner, British citizen Andargachew Tsege, who has been held in Ethiopia since June 2014.

The UN has demanded the immediate release of a Briton held on death row inEthiopia for more than a year, an intervention that campaigners say exposes Britain’s poor diplomacy towards the case.
Experts from the UN Human Rights Council have advised Ethiopia to pay Andargachew Tsige “adequate compensation” before sending him home to London, an abrupt hardening of its position on the case at a time when Britain pursues a softly, softly approach with no tangible reward.
Internal Foreign Office emails, disclosed for the first time, reveal that even before Tsige was kidnapped and jailed in an unknown location in June 2014, British officials had voiced fears at “the real risk of torture if [Tsige is] returned to Ethiopia”, along with “fair trial concerns”.
An eight-page judgment from the UNHRC’s working group on arbitrary detention handed to Ethiopia suggests such fears have been realised, saying that there is “reliable evidence on a possible situation of physical abuse and mistreatment which could amount to cruel, inhuman and degrading treatment.”
Tsige, 60, a father of three from London, and known to friends as Andy, was arrested in Yemen’s main airport while in transit and forcibly removed to the Ethiopian capital, Addis Ababa.
He is prominent in Ethiopian politics, having been leader of opposition partyGinbot 7, which has called for democracy, free elections and civil rights. The government has accused him of being a terrorist and in 2009 he was tried in his absence and sentenced to death.
Foreign secretary Philip Hammond has refused to demand his urgent release, preferring to push for consular access, a request rejected by Ethiopia. Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, who lives in London with their children, has spoken to him just once by telephone since his abduction.
Another internal government email from the UK ambassador to Ethiopia to Laurence Robertson MP, who heads the all-party parliamentary group on Ethiopia, describes the Ethiopians as “obdurate”.
Hammond recently attempted to harden up the UK’s position on Tsige, calling for rapid progress in the case, but campaigners say this remains significantly short of what is required. Another recent Foreign Office statement made no mention of Tsige, but welcomed the “generally peaceful environment” of the recent Ethiopian elections, which saw the government locking up political opponents and journalists.
Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, said: “Despite the injustices that have been – and continue to be – committed against this British national, the foreign secretary refuses to ask for Andy’s release and his return back home to his family in Britain.
“The UN is right to be taking action and demanding Andy’s immediate release from his unlawful detention. The UK’s refusal to do the same is an unacceptable abdication of responsibility to one of its citizens.”
Kevin Laue of the human rights organisation Redress, which helps torture survivors, said: “The UK government should be outraged by this behaviour and should be responding in the strongest possible terms.” A Foreign Office spokesman said: “The foreign secretary has raised this case with the Ethiopian foreign minister on 13 separate occasions, most recently on 29 April 2015. The minister for Africa raised this again on 11 June. We will continue to lobby at all levels, conveying our concern over Andargachew Tsige being detained without regular consular visits and access to a lawyer.”
Source: theguardian

Friday, July 3, 2015

የሳሙኤልን ገዳይ መደበቅ ያልቻለው ድራማ

ጌታቸው ሺፈራው
ዜጎች በተራ ‹‹ወንጀል›› 14 ከዚህ አለፍ ሲል 28 ቀን እየተቀጠሩ በሚመላለሱበትና በሚጉላሉበት ሀገር፣ አባሪው እንኳ ባልተያዘበት ሁኔታ፣ ይህ ነው የሚባል ምርመራ ሳይደረግ የሳሙኤል አወቀ ገዳይ በ17 ቀን ውስጥ 19 አመት እስራት እንደተፈረደበት ተሰምቷል፡፡ ትናንት ችሎቱን የተከታተሉት ሰዎች በግምት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ለሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የነበረውን ድራማ በስልክ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ስልክ የሚጠልፈው ኢህአዴግ ሪፖርቱ ‹‹ሳሙኤልን አልገደልነውም›› የሚለውን ድራማቸውን የሚያራክስ መሆኑን ተረድቷል፡፡ የፍርድ ቤቱ ድራማ ቀድሞ በሰማያዊ በኩል እንዳይወጣ ጉዳዩ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሪፖርት ከተደረገ ከደቂቃዎች በኋላ በራሱ ካድሬዎች በኩል ቀድሞ ‹‹ፍርዱን!›› ይፋ አደረገ፡፡ ዛሬ ደግሞ እነ ፋና እየተረባረቡበት ነው፡፡ ከምንም በላይ ወንጀሉን የግል ሲያደርጉት ድምፀታቸው ግን ሳሙኤልን ማን እንደገደለው ግልጽ እያደረገባቸው ነው፡፡Samuel Awoke, member of Semayawi party, killed by TPLF
ሳሙኤል አወቀ ከአንድ አመት በላይ ካድሬዎችና ደህንነቶች ‹‹እንገድልሃለን›› እያሉ እየዛቱበት መሆኑን በማህበራዊ ገጹ አስቀምጧል፡፡ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት በፖሊስ ታድኖ ታስሯል፡፡ ከሀገር ውጣልን ብለውት ‹‹አልሰደድም›› ብሎ ነገረ ኢትዮጵያ ላይ ጽፏል፡፡ ከደህንነት፣ ካድሬዎችና የፖሊስ አዛዦች የሚደርስበት ማስፈራሪያና ዛቻ ከሶስት ጊዜ በላይ በነገረ ኢትዮጵያ ተዘግቧል፡፡ ለአብት ያህል ሰኔ 10/2006 ዓ.ም ነገረ ኢትዮጵያ ላይ ‹‹ጠበቃው በፖሊስ እየታደነ ነው›› በሚል ዜና ‹‹ህዝብ እየተበደለ ነው ብለህ የአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ አስተያየት ሰጥተሃል:: አገር ለቀህ ካልተሰደድክ እንገድልሃለን›› መባሉ በዋቢነት ተቀምጧል፡፡
የደንበኞች አስተያየት መስጫ ላይ የጻፍከው አንተ ነህ ተብሎ በተከሰሰበት ወቅት የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸጋዬ መንግስቴ ዳኞች በተገኙበት ‹‹በማንኛውም ጊዜ መንገድ ላይ ይዛችሁ ማሰር ትችላላችሁ፡፡ ዴሞክራሲያዊም ሆነ ሰብአዊ መብት የሚባል አይሰራም›› ብለውታል፡፡ የደብረማርቆስ ፖሊስ ኮማንደር ‹‹አስደፋሃለሁ!›› ብሎ ዝቶበታል፡፡ ከመገደሉ አንድ ወር በፊት እግሩን ሰብረውታል፡፡ ከመገደሉ ሁለት ሳምንት በፊት በተፈጠረበት ከፍተኛ ስጋት ‹‹ብታሰርም መንፈሴ አይታሰርም፣ ከገደሉኝም ትግሌን አደራ›› ሲል ተናዝዟል፡፡
ሳሙኤል አወቀ ድብደባ ሲፈፀምበት፣ ከዛም በኋላ ሲገደል በድንገት መብራት መጥፋቱን የአካባቢው ነዋሪዎች እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ሳሙኤል አወቀ የተገደለው ከምሽቱ 1፡30 አካበቢ ነው፡፡ በዚህ ወቅት እሱን ሌት ተቀን ይከታተሉት የነበሩት ፖሊሶች እንኳን በቦታው አልነበሩም፡፡ የተገደለው መሃል ከተማው ላይ ሆኖ እያለ ፖሊስ የደረሰው ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ነው፡፡ ከ1፡30 በኋላም በቦታው የደረሰው ፖሊስም ሳሙኤልን በግል የሚያውቀው መሆኑ ምን አልባት ‹‹አርፈህ ተቀመጥ!›› ተብሎም ስላልቻለ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ያም ሆኖ ተሰቃይቶ እንዲሞት ስለተፈለገ በሚመስል መልኩ ፖሊስ ደርሶ እስኪጣራ ተብሎ ሀኪም ቤት እንዳይደርስ ተደርጓል፡፡
የሳሙኤል አወቀ ገዳዮች ከተባሉት መካከል አንዱ ወዲያውኑ ማታ እንደተያዘ ተነገረ፡፡ ተባባሪዎቹ ግን ሊያዙ አልቻሉም፡፡ እንግዲህ ተባባሪዎቹ ባልተያዙበት፣ በዚህ ፍትህ በሚራዘምበት ሀገር የሳሙኤል አወቀን ገዳይ ሰኔ 25/2007 ዓ.ም በተገደለ በ17 ቀን ውስጥ የ19 አመት እስር ተፈርዶበታል ተብሏል፡፡ በትናንትናው ዕለት በዋለው ችሎት የሳሙኤል ቤተሰቦችና ሌሎች ወጣቱን የሚያውቁት ግለሰቦችም ተገኝተው እንደታዘቡት፣ አቶ ተቀበል ገዱ 19 አመት ተፈረደበት በተባለበት ችሎት ዳኛው ስለ ፍርድ ሂደቱ ምንም ነገር አላነበቡም ተብሏል፡፡ ፍርዱ ሲነበብ ሳሙኤል እንዴት እንደተገደለ በምርመራና በፍርድ ሂደቱ የተገኙት ሀቆች መገለጽ አለባቸው፡፡ ግን ደግሞ የሚያሳጡ ሆኑና በፍጥነት 19 አመት እንደተፈረደበት ተናግረው ወጥተዋል፡፡
ገዳይ ተብሎ የተያዘው አቶ ተቀበል ገዱ ‹‹እኔ ሳሙኤል አወቀ የሚባለውን ሰው አላውቀውም፡፡ ግደለው ተብዬ ገንዘብ ስለተሰጠኝ ነው የገደልኩት፡፡›› ማለቱ ከእስር ቤት ሾልኮ ወጥቷል፡፡ ‹‹ማን ነው ገንዘቡን የከፈላችሁ?›› ሲባል ደግሞ ‹‹እኔ እሱንም አላውቀውም፡፡ ለእኔ ገንዘቡን የሰጠኝ ያልተያዘው ጓደኛዬ ነው፡፡ እንድንገድልለት የፈለገውም ሰውም የሚያውቀው እሱ ነው›› ማለቱን እስረኞቹ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ ከዚህ በፊት በዋለ ሌላ ችሎት ገዳይ የተባለው ሰው ‹‹ለምን ገደልከው?›› ሲባል ሻይ ቤት ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት ሳሙኤል ቀድሞ በዱላ ስለመታው እንደገደሉት ገልጾአል፡፡ ይሁንና ይህ ከሳሙኤል ግላዊ ባህሪ ጋር የሚሄድ አይደለም፡፡ ይህንንም ገዳይ ተብሎ የተያዘውና የተፈረደበት አቶ ተቀበል ገዱ እንደገና እጁን አውጥቶ ዳኛው እድል ሲሰጡት ‹‹ቅድም ሻይ ቤት ውስጥ ስለተጣላን ነው የገደልኩት ያልኩት አቃቤ ህጉ በል ስላለኝ ነው፡፡ አላውቀውም፡፡›› እንዳለ ችሎቱን የተከታተሉት ይናገራሉ፡፡
ሳሙኤል በተገደለ ማግስት ካድሬዎች ግድያው ከጥብቅና ጋር በተያያዘ ነው በሚል ጉዳዩን ከኢህአዴግ ካድሬዎችና ደህንነቶች እራስ ለማውረድ ጥረው ነበር፡፡ በወቅቱም ሳሙኤል የተገደለው ለጥብቅና ቆሞለት ከነበረው አርሶ አደር ጋር አለመግባባት በመፈጠሩ ነው እያሉ ለማስመሰል ጥረዋል፡፡ ይሁንና በትናንትናው የፍርድ ቤት ውሎ ፍርድ ቤቱ ለገዳዩ ማቅለያ ሲያቀርብ ‹‹የቀን ሰራተኛ በመሆንህና በዚህ ስራም ቤተሰብን የምትደጉመው አንተ በመሆንህ አንቀፁን ከ38 ወደ 31 አውርደንልሃል›› ሲሉ ተደምጧል፡፡ በዚህም መጀመሪያ ካሉት ከአርሶ አደርነት ወደ ቀን ሰራተኝነት ቀይረውታል፡፡ ይህም መጀመሪያ ግድያው ፖለቲካዊ አይደለም ለማለት ካድሬዎች ከደንበኝነት ጋር ያያዙትን ውድቅ የሚያደርግ ነው፡፡ በእርግጥ የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት መጀመሪያ አካባቢ አቃቤ ህግ ሳሙኤል የተገደለው ከደንበኝነት ጋር በተያያዘ ለማስመሰል ጥረው ነበር፡፡ ይህኛው ድራማ አላስኬድ ሲል በትዕዛዝ እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሳሙኤል አወቀን ቤተሰቦች ለማስተዛዘን ወደ ጎጃም ያቀኑት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት አባይ በርሃ ላይ ተይዘው እስከ ምሽቱ 2፡30 ከታሰሩ በኋላ ቢፈቱም ወደ ለቅሶው እንዳይሄዱ መኪና እና ቁሳቁሶቻቸውን መነጠቃቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መርማሪዎቹ በተደጋጋሚ ይጠይቁት የነበረው ጥያቄ ‹‹ሳሙኤልን ማን ገደለው?›› የሚል ነበር፡፡ ይህም የሚያሳየው መረጃዎች ያጋለጡትን የሳሙኤል ገዳይ በድራማ ለመደበቅ ያደረጉት መንደፋደብ ነው፡፡ ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ ትናንትናው የፍርድ ውሎና አሁንም ድረስ የቀጠለው ፕሮፖጋንዳ የሚያሳየው ሳሙኤል በፖለቲካ አመለካከቱ የተገደለ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ለመሸፈን ፍርድ ቤት አድርጎት የማያውቀውን እጅግ የተፋጠነ ‹‹ፍርድ›› ሰጥቷል፡፡ መጀመሪያ ከደንበኝነት ጋር በተያያዘ ነው የተገደለ ብለው አሁን የማያውቀው የቀን ሰራተኛ ነው የገደለው ብለዋል፡፡ እነሱ ‹‹ሻይ ቤት ውስጥ ተጣልተን ነው የገደልኩት›› እንዲልላቸው ቢፈልጉም እሱ ግን እንደገና ‹‹ይህን እነሱ ናቸው በል ያሉኝ›› ብሎ መስክሮባቸዋል፡፡ ገዳይ ተብሎ ለተያዘው ሰው ገንዘብ የሰጠው አባሪ አልተያዘም፡፡ በእርግጠኝነት አምልጦ አይመስለኝም፡፡ ግድያውን ካቀነባበረው ሰው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ እንዳይያዝ ስለሆነ እንጅ፡፡ ሆኖም ይህ ሁሉ ድራማ ገዳዩን መደበቅ አልቻለም፡፡ ከምንም በላይ ድራማው ሳሙኤል ባለፈው አንድ አመት በሚዲያና በማህበራዊ ደረ ገጹ ያሰፈራቸው እማኝነቶችና ሌሎችን መረጃዎች ያጋለጡትን ገዳይ መደበቅ አልቻለም፡፡
Source: ecadforum

Thursday, July 2, 2015

British Amb.: Ethiopian election results bad for democracy

Britain’s Ambassador said: “It is starting to sound as if the ruling party and its allies will have a 100 percent of the seats in parliament. And I think that is not good for democracy; that is what you get in places like North Korea. But actually in Ethiopia you need some diversity of opinion in parliament.”
The Ambassador made the remark during an interview with the English-weeklyThe Reporter. The interview, published in the weekend, was conducted days before the officially announcement of final election results last Friday. Nonetheless, a total win by the ruling party EPRDF and its allies was widely expected since the last week of May.Photo - Ambassador Greg Dorey
The Ambassador’s remark came at about the same time British Foreign Minister issued a strong statement regarding Andargachew Tsige‘s case.
Western diplomats in Addis Ababa, unlike elsewhere,  seldom remark on domestic politics, especially since the 2005 post-election crisis that impacted relations with a couple of diplomatic missions.
Here is the Ambassador’s comment:
Question: What is your take on the recent election in which the ruling party won all the 547 seats in parliament? Would you characterize it as free, fair and credible?
Ambassador Greg Dorey:
I think it is a pity that we couldn’t observe that election. First of all, The European Union (EU), which observed election[s] in Ethiopia in 2005 and 2010, was not invited this time; we needed an invitation. If you are going to have an observation mission, it needs cooperation from the government. It was clear that the government did not want the EU observation mission to come on this occasion.
Very unusually, diplomats were [are] not allowed to observe election [s here]. Though, peculiarly, it seems ok for the African Union (AU) mission to have diplomats as part of the election observation mission. I have observed elections in many other places such as Pakistan even in the remote tribal areas but not permitted here.
So, we don’t have first-hand information on what went on. I think we will wait until we hear the official announcement of results and I expect we will then comment [the interview was conducted last week]. But we have some concerns especially regarding the relative lack of political space in the run-up to the election.
It is starting to sound as if the ruling party and its allies will have a 100 percent of the seats in parliament. And I think that is not good for democracy; that is what you get in places like North Korea. But actually in Ethiopia you need some diversity of opinion in parliament.
But, that is not to say that the current government is doing a bad job when it comes to development; it is doing a good job overall. However, in a democracy, it is health[y] to have somebody who is articulating alternative views. And in the previous parliament one out of 547 MPs seemed a bit inadequate.
I think it would be a sign of Ethiopia growing and developing and being part of the global democratic family, if in the future we see rather more substantial opposition within parliament, I think that will be good for the country.
I am not in a position to comment on allegations of electoral abuses, as I said we did not observe. However, I think if the government has got 100 percent of the seats in parliament, it will be very important to ensure that in the coming years, those people who voted for other parties, and I do think a lot of people voted for other parties, feel that they have a say in the running of the country; and that their views are represented at the highest level. That would be important for the stability and sustainability of the future.
Source: hornaffairs