Monday, March 2, 2015

የአውሮፓ ህብረት “ሪፖርቶቹን መንግስት ስለማይቀበል ነው ምርጫውን የማልታዘበው” አለ


የታዛቢነት ግብዣም ከመንግስት አልቀረበልኝም ብሏል የግንቦቱን ምርጫ ለመታዘብ ከመንግስት ግብዣ እንዳልቀረበለት የገለፀው የአውሮፓ ህብረት፣ ባለፉት ሁለት ምርጫዎች በታዛቢዎቼ የቀረቡ ሪፖርቶች በኢትዮጵያ መንግስት ተቀባይነት ማጣታቸውም ከታዛቢነት እንድርቅ ገፋፍቶኛል አለ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በ1997 እና 2002 ምርጫዎች የህብረቱን የትዝብት ሪፖርት ሙሉ ለሙሉ ሳይቀበለው መቅረቱ፤ ለዘንድሮ ምርጫ ሌላ የታዛቢ ቡድን የማሠማራትን ጥቅም አጣራጣሪ እንዲሆን አድርጓል ብሏል – የአውሮፓ ህብረት፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ፤ የአውሮፓ ህብረት በታዛቢነት አለመሳተፉ በምርጫው ተአማኒነት ላይ የሚያወጣው ለውጥ የለም ብሏል፡፡ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሣለኝ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የአውሮፓ ህብረት በራሱ ምክንያት ምርጫውን እንደማይታዘብ ማሣወቁን ጠቁመው፤ ምርጫውን የአፍሪካ ህብረት፣ የአገር ውስጥ ሲቪል ማህበራትና ተቋማት ይታዘቡታል ብለዋል፡፡ በአና ጐሜዝ የሚመራው የአውሮፓ ህብረት ታዛቢ ቡድን በ97 ዓ.ም የተካሄደውን ምርጫ ክፉኛ በመተቸቱ ከፍተኛ ውዝግብ ከመፈጠሩም በተጨማሪ፣ በ2002 ምርጫም ህብረቱ የምርጫው እለት ሂደቱ መልካም የነበረ መሆኑን ከገለፀ በኋላ፣ በጥቅሉ ምርጫው በአለማቀፍ መመዘኛዎች ሲፈተሽ ግን በርካታ ጉድለቶች አሉበት በማለት ሪፖርት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
satenaw.com

የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የሕይወት ጉዞ

(አንዱዓለም ተፈራ)
TPLF-Logo

መግቢያ
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ከተመሠረተ ጀምሮ የተለያዩ ስሞችን፣ መርኆዎችን፣ ተግባራትን፣ ባጠቃላይም ማንነትን ተከናንቧል። ይህ ማለት፤ በሂደቱ እየተቀያየረ የሄደ ድርጅት ነው። ሲነሳ፤ አሁን የያዘው እምነት፣ ግብና አሠራር አልነበረውም። እግረ መንገዱን ለዕለቱ የሚረዳውን የፖለቲካ አቋም እየውለበለበ ተጓዘ እንጂ፤ ዘላቂ የሆነ የፖለቲካ አቋም አልነበረውም። ይህ የሚነግረን፤ ይህ ድርጅት፤ አጋጣሚዎችን ተጠቃሚነትን፣ ሥልጣንን፣ ቂምና በቀልን፣ የሕልውናው መሠረቶች አድርጎ የተጓዘ እንጂ፤ መርኆ ወይንም ሕዝባዊ ግንዛቤ ያላነገበ ድርጅት መሆኑን ነው። ይህን ቡድን የሚያሽከረክረው የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይ ፍጹም ማርክሲስት አይደለም። የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ትግሬዎችን ነፃ ሊያወጣ የተነሳ ድርጅት አልነበረም። በርግጥ ስሙ፤ ከትግራይ ብሔራዊ ድርጅት፤ በብዙ መንገዶችና ስሞች አልፎ ( ንቅናቄ፣ ግንባር ) አሁን ወደ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ተሸጋግሯል። መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ ነውና፤ የዚህ ድርጅት የተለያዩ ስሞች፤ ጊዜያዊ ፍላጎቱን ለማሟላት መጠቀሚያ መገልገያዎች እንጂ፤ የእውነተኛ ተግባሩና ግቡ ገለጮች ስላልነበሩ፤ መለዋወጣቸው፤ ለመሪዎቹም ሆነ ለአባላቱ፤ ግድ አልሠጣቸውም።
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ባለቤቶች፤ ሕልውናቸው በጦርነት የታናጸና አሁንም “በጦርነት ላይ ያለን ነን!” ብለው የሚያምኑ ግለሰቦች ናቸው። ለዚህ መሠረቱ፤ ራሳቸውን የውጭ አድርገው መመልከታቸው ነው። ጠላት ብለው አማራውን፣ ኦሮሞውን፣ ኦጋዴኑን፣ አኙዋኩን፣ ደቡቡን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሒዶ ቤተክርስቲያንን፣ ደርግን፣ ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ግለሰብና ድርጅትን ፈረጁ። በዚህ ስሌት፤ መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ “ጠላት!” ተብሎ ተፈረጀበት ማለት ነው። የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ያዘዛቸውን ስላላደረጉ ጠላት ተባሉ። እናም ከ “ሌሎች” ተመደቡ። ምን ጊዜም ቢሆን “ሕዝቡ የኛ አይደለም፤ እኛም የሕዝቡ አይደልንም።” የሚል እምነት ስላላቸው፤ ዛሬ ወይንም ነገ ሕዝቡ ይነሳብናል የሚል ፍራቻ አላቸው። እናም እነሱ “የኛ” ብለው ከሰበሰቡት ውጪ ያለ ግለሰብ፣ ጋዜጠኛ ሆነ ሰላማዊ ሰልፈኛ፤ መምህር ሆነች እርጉዝ ሴት፣ ድርጅትም ሆነ ሌላ ስብስብ፤ “አጥፊያችን ስለሆኑ እናጥፋቸው!” የሚል ነው አመለካከታቸው። እናም ለማንኛውም የፖለቲካ ክስተት፤ መልሳቸው ያኔ በበረሃ በነበሩበት ወቅት ይሠጡት የነበረው መልስ ነው፤ “በለው!”፣ “አባረው!”፣ “እሰረው!”፣ “ግደለው!”። ይህ አጠቃላይ መገለጫው የሆነው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት የማንነቱ መግለጫ ነው። እስኪ የዚህን ድርጅት የሕይወት ጉዞና የሂደት ደረጃዎቹን እንመልከት። በዕድገቱ ያሳያቸው አራት የዕድገት ሂደት ደረጃዎች አሉ። አሁን አራተኛውን የሂደት ደረጃ በማጠናቀቅ ላይ ነው።
፩ኛ.       ፍርሃት
ይህ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የመጀመሪያ የዕድገት ደረጃው፤ ከተነሳበት፤ ትግራይን ገንጥሎ የራሱ የሆነ መንግሥት ማቋቋም ከሚለው መርኁ ወጥቶ፤ ኢትዮጵያን ለማጠቃለል ያደረገው ጉዞና፤ ሥልጣኑን በጁ የያዘበት ወቅት ነበር። በዚህ ሂደቱ፤ ለተለመው ሁሉ ዕቅድ፤ መነሻው ፍርሃት ነበር። በትግራይ የሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቀበለን ወይ? በትግራይ የሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኔ የበለጠ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲን (ኢሕአፓን) ይደግፍ ይሆን ወይ? በትግራይ የሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባርን (ጠርናፊትን) ከኔ ይልቅ ይቀበል ይሆን ወይ? በትግራይ የሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረትን (ኢዲዩን) ይደግፍ ይሆን ወይ? የሚሉት የመጀመሪያዎቹ እንቅልፍ ነሺ ፍርሃቱ ነበሩ። በነዚህ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ፍርሃት እንዲኖረው አስተዋፅዖ ያደረገው፤ በሁሉም ድርጅቶች ውስጥ፤ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች በአመራርና በአባልነት በዝተው መገኘታቸው ነበር።
ታዲያ ለነዚህ ድርጅቶች ሕልውና የነበረው መልስ፤ በግልጽ እንደታየው፤ በድርጅቶቹ ላይ ጦርነት መክፈት ነበር። በዚህ ሂደቱ፤ ስሞቹን ቀያይሯል። ግቦቹንም ለዋውጧል። ከውጪ ብቻ ሳይሆን፤ በድርጅቱ ውስጥ፤ ድርጅቱ የነበረውን ዓላማና ግብ አስመልክቶ ጥያቄ ያቀረቡትን ፈጅቷል። ፈጅቶም አልቀረ፤ ጊዜያዊ ሂደቱን ይረዱት ዘንድ፤ ግቦቹን ለዋውጧል። በዚህ ደረጃው ያደረጋቸው ጦርነቶች፤ በትግራይ ከሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅምና ፍላጎት አንጻር ጠላት ከሆነው ከደርግ ጋር ሳይሆን፤ በትግራይ የሚኖረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከደርግ ለማዳን ከተነሱ ድርጅቶች ጋር ነበር። በተጨማሪም፤ በዚህ ድርጅት ውስጥ አሽከርካሪ የሆኑት ግለሰቦች፤ የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይን መሠረቱ። ይህ ፍጹም የማርክሲስት ሌኒኒስት ድርጅት አይደለም።
በመጀመሪያ የብሔር ጥያቄ፤ ለማርክሲስት ሌኒኒስቶች፤ ለዋናው የዓለም አቀፍ የላብ አደሩ አምባገነንነት መሸጋገሪያ፤ የፖለቲካ መሣሪያ ነው። የብሔር ጥያቄ የአርሶ አደሩ ጥያቄ አይደለም። የብሔር ጥያቄ የላበደሩ ጥያቄ አይደለም። ይህ በትግራይ ለሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ የተለየ ሳይሆን፤ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ የሚናገር ሀቅ ነው። የብሔር ጥያቄ፤ “የኔን ወገን ለብቻዬ ልግዛው!” ባዩ የብሔርተኛ ከበርቴው መደብ ጥያቄ ነው። በዚህ የከበርቴ መደብ ዙርያ፤ ሥልጣን ናፋቂ ምሁራን ይኮለኮሉበታል። የብሔር ጉዳይን አስመልክቶ በማዘጋጀት ላይ ያለሁት መጽሐፍ ስላለ ሲወጣ ትንታኔውን ማየት ይቻላል፤ ለአሁኑ ግን በዚሁ ልለፈው። ይህ የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይ፤ የብሔራዊ ከበርቴውን የብቻ ሩጫ ለመግታት ያደረገው ጊዜያው የትግል ስልቱ ሳይሆን፤ ከሌሎች ታጋይ ኤትዮጵያዊ ድርጅቶች ለይቶ፤ በትግራይ የሚኖረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብቻው ለመገንጠልና ለመግዛት ያራመደው ግቡ ነበር። እዚህ ላይ ላሰምር የምፈልገው፤ የብሔርን ጥያቄ የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይ ሲያራምድ፤ ስልት አድርጎ ሳይሆን ግብ አድርጎ የያዘው እንደሆነ ማሳየቴን ነው። ይህ ደግሞ ከመሠረታዊ የማርክሲስት ሌኒኒስት እምነት ጋር የሰማይና መሬት ያህል ርቀት አለው። በዚህ ስሌት፤ የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይን፤ በመርኅ የሚመራ የፖለቲካ ድርጅት ሳይሆን፤ የአድማ ጠንሳሾች ወሮበላ ቡድን ነው ማለት ይቻላል።
ከላይ የተጠቀሱትን ድርጅቶች ካወጋ በኋላ፤ በትግራይ በሚኖረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያለውን ፍራቻውን በአእምሮው ጀርባ ሸጉጦ፤ አጋጣሚው በር ስለተከፈተለት፤ ወደፊት ሄጄ ሥልጣን ብነጥቅ የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ያደርገኛል? የሚለው ፍራቻው ዋናውን ቦታ ያዘ። እናም ለዚህ መፍትሔ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማጭበርበር፤ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኢሕዴን)፤ የሚል ተቀጥላ ድርጅት አቋቋመ። አከታትሎም የኦሮሞ ድርጅት መሠረተ። እንግዲህ እኒህ ድርጅቶች ምን ዓይነት አባላት ነበሯቸው? ምንስ ዓይነት አመራር ነበሯቸው? ነፃነትና የውስጥ አሠራርስ ነበሯቸው ወይ? ብሎ የሚጠይቅ ያለ አይመስለኝም፤ ግልጽ ነው። ከብት ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ይሆናላ! እንግዲህ በዚህ ወቅት የነበረው ፍራቻ፤ ለሂደቱ ወሳኝ የሆኑ እርምጃዎችን እንዲያተገብር አስገደዱት። ድርቅን ተጠቅሞ የትግራይ ወገናችንን ለሞት በሚዳርግ ሂደት አስገብቶ፤ ድርጅቱንና መሪ ግለሰቦችን በሚጠቅም መንገድ መሣሪያና ገንዘብ ሰበሰበበት። ለፖለቲካ ግቡ ያመቸው ዘንድ፤ የትግራይ ወገናችንን በገበያ አስደበደበው።
ቀጥሎም የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) የሚል ጋቢ በላዩ ላይ ደርቦ አሸሸ ገዳሜ ማለቱን ያዘ። ደርጋማ የሆነው የአረመኔው የመንግሥቱ ኃይለማርያም አምባገነን ቡድን በሩን ብው አድርጎ ስለከፈተለት፤ ይኼን አጋጣሚ ተጠቅሞ፤ ሕዝቡ በያለበት ባለ አቅሙ ቢታገልም፤ ሰተት ብሎ አዲስ አበባ ገባ። በዚህ ወቅት የነበረው ፍራቻ፤ ደርግ ያንሰራራብኝ ይሆን ወይ? ኢሕአፓ ተመልሶ ያድግ ይሆን ወይ? ሕዝቡ ባይቀበለኝስ? አማራው ምን ያደርገኝ ይሆን? የዓለም መንግሥታት ባያውቁኝስ? የሚሉት ነበሩ። ለዚህ መልስ ያደረገው፤ ካድሬዎቹን በየመንግሥታቱ መናገሻ ከተማ እየሄዱ እግር እንዲነሱ፤ የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባርን አቅፎና ሸዓቢያን ተደግፎ፤ መንግሥት እመሠርታለሁ እያለ ማባበል ነበር። ኢሕአፓ ከገባበት ገብቶ እንዳያንሰራራ ድምጥማጡን ማጥፋት ነበር። አማራውን ደግሞ በሁለት መንገድ ማጥቃት ያዘ። ባንድ በኩል የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኢሕዴን) በሚል ሻማ የጎለተውን የስም ድርጅት፤ ወደ የብሔራዊ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) የሚል የለውጥ ቀለም በማሽቆጥቆጥ፤ ከአማራ አለመወለድ ብቻ ሳይሆን፤ ፍጹም ዝምድና የሌላቸውንና አማራን በጠላትነት የፈረጁ የራሱ ሰዎችን ሰባስቦ በአመራር ላይ በማስቀመጥ፤ የይስሙላ ድርጅት ፈጥሮ መምታት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ፤ በመላ ኢትዮጵያ በሚኖረው አማራ ላይ በቀጥታ፤ በኑሮውና በመኖሪያው ላይ በተዘዋዋሪ በመዝመት፤ ሕልውናውን ማሣጣት ነበር። በሁሉም በኩል መተንፈሻ በሚያገኝበት ደረጃ ተሳካለት። ይህ የመጀመሪያው የዕድገት ሂደቱ ደረጃ ነበር።
፪ኛ.  መደላደል
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ከላይ በቁጥር አንድ የተዘረዘረውን በተግባር ካዋለ በኋላ፤ ፍርሃቱን እንደተሸከመ ወደ መደላደሉ ተሸጋገረ። ምን ጊዜም ቢሆን ከላይ የተዘረዘረው እስከ ዘለቄታው የማይለቀው ፍርሃት መሆኑን ልብ ማለት አለብን። በዚህ በሁለተኛው የዕድገት ደረጃ ላይ፤ የመጀመርያ ተግባሩ፤ የሚፈልገውን የመደላደያ ሕገ መንግሥት ማጽደቅ ነበር። በዚህም ላይ የሀገሪቱን አስተዳደር በሚፈልገው መንገድ አዋቀረ። በየቦታው የራሱን ሰዎች መደበ። የይስሙላ ምርጫዎችን አዘጋጀ። የመጀመሪያውን ፍራቻውን ለመቋቋም የተጠቀመበትን የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባርን አረመኔያዊ በሆነ መንገድ አሰናበተ።
ከደቡቡ የኢትዮጵያ ክፍል አማራ ያላቸውን ኢትዮጵያዊያን፤ በቀጥታ ራሱ ድርጅቱ በማዘዝም ሆነ በመሳተፍ አፈናቀለ፣ ሀብታቸውን ዘረፈ፣ ገደል። አሽከር የሚሆኑትን የሹመት ካባ በማከናነብ፤ የድርጊቱ ወራሽ አደረጋቸው። በአኝዋኮች ላይ፣ በኦጋዴኖች ላይ፣ በኦሮሞዎች ላይ ዘመተ። እኒህ ተግባራቱ፤ ለመደላደል ያመቹኛል ብሎ የወሰዳቸው ነበሩ። ተደጋጋሚ የይስሙላ ምርጫዎችን አካሄደ። ጠንካራ ተቃዋሚዎች ይሆናሉ ያላቸውን፤ እንደ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉትን ገደለ።  መጀመሪያ ያዋቀራቸውን አስተዳደራዊ ግዛቶች በወዘ። አላደረግኩም እያለ የማለ የተገዘተበትን በግልጽ አደረገው። ወልቃይትን፣ ጠለምትን፣ የጠገዴን ግማሽ አካልና በወሎ ደግሞ ሁለት ወረዳዎችን ወደ ትግራይ ጠቀለለ። እዚህ ላይ ሁለት ወፍ በአንድ ደንጋይ እንዲሉ፤ አማራውን አሳነሰ፤ የራሱ የሚለውን የትግራይ ክልል በለሙ የአማራው ክልል መሬት አሰፋ። ለይስሙላ ያሳየውን የዴሞክራሲ ጭላንጭል እንዳልነበር አደረገ። በዚህ የመደላደል ወቅቱን አጠናቀቀ።
፫ኛ.  እብሪት
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ አንደኛና ሁለተኛውን የዕድገት ደረጃዎቹን ካጠናቀቀ በኋላ፤ ቀንደኛውን ተቃዋሚ አጠፋሁ ብሎ ደረቱን ነፋ። አሁን በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ክንፉን ዘረጋ። ልቡን አሳበጠ። ለወደፊቱ ሊነሱ ይችላሉ የሚላቸውን በእብሪት አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት፤ ሌላ ተቃዋሚ እንዳይነሳበት፤ ከግር ከግሩ መንቀል ያዘ። በአኳያው ደግሞ፤ በትግራይ ክፍለ ሀገር ሙሉ ለሙሉ ቁጥጥር በማድረግ፤ ሕዝቡ ያለሱ ሌላ አማራጭ እንዳያስብና እንዳይኖረው፤ የሚችለውን አደረገ። ሕዝቡን ወርቅ ነህ አለው። ታሪክህ ከሁሉ ይበልጣል አለው። አንተ የተለየህ ነህ አለው። ከጎንደርና ከወሎ ለም መሬት ነጥቆ የወሰደውን ከትግራይ ሰው ወስዶ አሰፈረበት። ይህ ሁሉ ጥረት፤ በትግራይ ያለው ኢትዮጵያዊ፤ የሱ ዋና ደጋፊ በመሆን እንዲያገለግለው ነበር።
ከመደላደሉ ወጥቶ፤ ከውጭ ሀገር ሊመጣ የሚችልበትን ጫና፤ ከኔ የተሻለ አታገኙም በሚል እብሪት፤ ተቋቋሚ ለመሆን ዛተ። ይህ ግን እነሱ የሚፈልጉትን በሙሉ በተግባር እያዋለ፤ የሀገራችንን ክብር ለነሱ በመገበር ነበር። ለሙን የሀገራችንን የእርሻ መሬት በኪሱ ለሚያስገባው ልቃሚና፤ ለወደፊቱ ሀገራችን እንድትስቃይ በሚዳርግ ርካሽ የብዝበዝ የእርሻ ዘዴ ቸበቸበው። ለዚህ ማስተማመኛ እንዲሆነው፤ የተጠናከረ ተቃዋሚ እንዳያድግ ከሥር ከሥሩ መምታቱን የዕለት ተዕለት ሥራው አደረገው።
በሀገር ውስጥ ምንም ዓይነት የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ያልፈቀደው እንቅስቃሴ እንዳይኖር በሩን ሁሉ ጥርቅም አደርጎ ዘጋ። ሕዝቡ ምንም ዓይነት ዜና እንዳያገኝ፤ የውጭ ሀገር የስልክና የድረገጽ አገልግሎት በሀገር ውስጥ በመገደብ፤ ሀገራችን በነዚህ አገልግሎት ከዓለም የመጨረሻውን ወለል እንድትይዝ አደረገ። ባሁኑ የዓለም የሥልጣኔ ደረጃ፤ ከዓለም በስልክና በኢንተርኔት አገልግሎት የመጨረሻውን ወለል መታቀፍ፤ በሀገር ያለውን መንግሥት ምንነት ገላጭ ነው። በእብሪት የማይደረግ የለም። በተጨማሪም የሀገራችንን ጥሬ ቁጥብ ሀብት በማናለብኝነት በመዝረፍ፤ ሕንጻዎችን ጀኔራሎች፤ የንግድ ባለቤትነቱን ሚኒስትሮች፤ ፈላጭ ቆራጭ አዛዥነቱን የድርጅቱ ካድሬዎች፤ የኪሳቸው ንብረት አደረጉት። ድርጅቱ የሀገሪቱን ታሪክ ማጥፋትና ማንኛውንም ግለሰብ በራሱ ምስል መቅረጽ ያዘ። መጽሐፍት በሙሉ እሱ የሚለውን ብቻ ማስፈር ያዙ። የራሱ ምሁራን የትምህርት መስኩን አጠቃለው ያዙ። በማንኛውም መንገድ ሀብታሞችና አዛዦች የድርጅቱ ቅምጥሎች ብቻ እንዲሆኑ ተደረገ። ሕዝቡ በረሃብ፣ በጥማት፣ በመብት እጦት ዳሸቀ። የእብሪተኛ መጥፎ ገጹ ግን፤ ቀጥሎ የሚመጣውን ማገናዘብ አለመቻሉ ነው። ይህ እብሪቱ ከ “ጠላት!” ብሎ ከመደባቸው፤ እስከ “የኔ!” ያላቸው ክፍሎች ድረስ በመጎንተሉ፤ ጠላቶቹ እየበዙ ብቻውን የቀረበት ሀቅ ከተፍ እንዲል አደረገበት።
፬ኛ.  ቁልቁል
አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት ብሎ ወደ መጨረሻው የዕድገቱ ደረጃ በመጓዝ ላይ ያለው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ሕይወት፤ አራተኛውን ደረጃ የያዘው፤ ድርጅቱ ሳያውቀው፣ ሳይዘጋጅለትና ሳያቅደው ነው። ጉዱ ደግሞ፤ ይህ ዕድገት ሊከተል የቻለው፤ ራሱ ባስቀመጠው የፖለቲካ ፍልስፍናና የአስተዳደር መመሪያ ተመሥርቶ ነው። በርግጥ በዕለት ተዕለት ኑሮው ላይ ብቻ ያተኮረ አካል፤ የረጅም ዘመን ጥርቅም ሂደት የሚያስከትለውን ውጤት ከሩቅ መገንዘብ አይችልም። የሆነውም ይኼው ነው። ሥልጣን ይዞ፣ ተደላድሎ፣ እብሪት ጎጥሮት ከሰነበተ በኋላ፤ ሌላ ሰውነት ያዘ። የነበረበት፣ የታገለለት፣ መሠረታዊ የሆነው ዓላማው ግቡን መታ ብሎ፤ የአመራሩ አባላትና በጉያቸው የሸጎጧቸው የቤተሰብ ጥርቃሚዎቻቸው፤ ከስብስብ አንድነት ይልቅ፤ ባሁን ሰዓት የየግል ሕልውናቸው የበላይነቱን ወስደ። እስከዛሬ ሙጫ ሆኖ አንዳቸውን ከሌላቸው አጣብቆ የያዛቸው የ “ሌሎች” ፍርሃት፤ እየደበዘዘ ሄደና፤ መደላደሉ እብሪትን አስከትሎ፤ እስካሁን ያቆየንን እስከዘለዓለሙ እየተገበርን እንቀጥላልን የሚለው፤ ወደ ግል ሕይወታቸው አስተሳሰባቸውን እንዲያቀኑ አደረጋቸው። ፍርሃቱ ሲጠፋ፤ የመተባበሩ ፍላጎት ደበዘዘ። እናም ሀብት ተሯሩጦ ለግል መሰብሰቡ ደራ። ካሁን በኋላ ቁልቁል መሄድ እንጂ ጣራውን አልፎ ሌላ ጣራ ማበጀት አይቻልም። ጣራውን ደረሱበት። ከንግዲህ ወደ ታች ብቻ ነው ቀሪው ሕይወታቸው።
መደምደሚያ
ከመጀመሪያው ተቆራኝቶት የነበረው ፍርሃቱ መታገስ በያዘበት ደረጃ፤ እንደጋሪ ፈረስ ዓይኖቹ በመደላደሉ ደልበው፤ በእብሪቱ ተጋርዶ፤ ባሁኑ ሰዓት ሳያውቀው በዙሪያው ያለው ሂደት ከቁጥጥሩ ውጪ ሆነ። ዙሪያው ሲገለባበጥ፤ መደናበር ያዘ። እናም የታገሰለት ፍርሃት ዓይሎ አጎደረበት። ቀንድ ሆኖ ከራሱ ላይ ተጫነው። መደላደሉና እብሪቱ ከፍርሃቱ ጋር ተደማምረው የበለጠ አደናበሩት። የኢትዮጵያ ሕዝብ ተብትቦ ከያዘው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የፖለቲካ ስንሰለት ራሱን እያላቀቀ መጣ። እስከዛሬ የሰማው፣ የተቀበለው፣ የቆመለት ሁሉ ለራሱ ለሕዝቡ ሕይወት ሳይሆን፤ ለትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መተንፈሻ ሳምባ መሆኑን ተረዳ። ፖለቲካው ትርጉም፤ ኑሮው ጣዕም አጣ። እናም፤ “የለም አንድ ነን!” “ባንድነት እንነሳ!” አለ። “ኢትዮጵያ አንድ ናት! አትከፋፍሉን! ጠላታችን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብቻ ነው!” አለና ተነሳ። ካሁን በኋላ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር አውሬነቱ ብቻ ነው የቀረው። ይገድላል። ሰው ይበላል። አይመርጥም። ለኛ ለውጪሰው ኢትዮጵያዊያን ያለን መንገድ፤ በአንድነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን መሰለፍ ነው። መሰባሰቢያችን፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት መቀበል፣ የኢትዮጵያ ሀገራችንን ዳር ደንበርና ለም መሬት ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ማለት፣ የሕግን የበላይነት መቀበል፣ እና የያንዳንዱ/ዷን ኢትዮጵያዊ(ት) የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብት ተቀብለን፤ እያንዳንዳችን በኢትዮጵያዊነታችን የምንሳተፍበት የፖለቲካ ምኅዳር እንዲኖር መጣር ነው። እንበርታና ተግባራዊ እንሁን። ኢትዮጵያዊያን እናቸንፋለን።

የፀረ-ኢትዮጵያዊው ገዥ ሥጦታዎች አያባሩም!

(ልንጠቀምባቸው ይገባል፤ ካወቅንበት)
አንዱዓለም ተፈራ
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር በተደጋጋሚ ለታጋዩ ክፍል የሚያደርገው ልገሣ፤ ማብቂያ ዲካ የለውም። አሁን ደግሞ እልል የሚያስብል ስጦታ ፊታችን ላይ ዘርግፎልናል። በሰላም የሚታገሉትን ድርጅቶች፤ ለማፈራረስና ለመጪው ውድድር እንዳይሳተፉ ለማድረግ፤ ባለ በሌለ ጉልበቱ ዘምቶባቸዋል። ይህ የሚጠበቅ ነው። በርግጥ ሁሉንም ታጋይ ድርጅቶች በአንድ ጠፍር አንቆ ለማጥፍት መጣሩን የሚሳየው ድርጊቱ፤ ሳያውቀው የታጋይ ድርጅቶቹን በአንድነት እንዲሰልፉ በሩን በርግዶ ከፍቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ ታጋይ ድርጅቶች፤ ከገዥው ድርጅት አንጻር አንድ በመሆን፤ አማራጭ ሆነው እንዲቀርቡ ከመጎትጎት ቦዝኖ አያውቅም። አሁን፤ ከመቼውም በላይ ይህ ጉትጎታ በሀገር ውስጥ በሰላም እየታገሉ ያሉትን ሀገራዊ ድርጅቶች፤ እንዲተባበሩ እየገፋቸው ነው። ለዚህም የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ከፍተኛ ድጋፍ ታክሎበታል። ይህ እልል ያሰኛል። ልንጠቀምበት ይገባል፤ ካወቅንበት! ድርጅቶችም እየሰሙና እየተቀበሉት ነው። ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው የነበረው ደስ የሚያሰኘው ዜና እልል አሰኝቶኛል።
የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ከመድረክ ጋር በትብብር፤ ከሰማያዊና ከመኢአድ ጋር ደግሞ ውህደት ፈጥሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ስሰማ፤ አሁን የድሉ መንገድ በደንብ ተጠረገ አልኩ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ድርጅቶቻችሁን መታገያ አድርጉ እንጂ አታምልኳቸው ሲል የነበረውን አዳመጡ። “ትግሉ ትግል የሆነው፤ በዚህ ወይንም በዚያ ስም በሚጠራ ድርጅት በመካሄዱ አይደለም። ትግሉ የሚቀጥለው ድርጅታችንን ስለከለከላችሁን ወይንም ስለፈቀዳችሁልን አይደለም። የምንታገለው በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሀቅ፤ ትግሉን ግድ ስላደረገው ነው።” በማለት ተነሱ። ከመሰሎቻችን ሀገር አቀፍ ድርጅቶች ጋር አንድ ሆነን እንታገላለን አሉ። ስሙን ውሰዱት አሉ። ከዚህ በላይ ለትግል ሕይወትን መሥጠት የት አለ? ቆራጥነት የት አለ። ለዚህ እኮ ነው አንዱዓለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዩት ዓለሙ፣ በቀለ ገርባ እና ሌሎች እስር ቤት የሚማቅቁት። እናም አሁን ትግሉ የሀገር ሆነ። ትግሉ ለሀገር ሆነ። አንድነት፣ መኢአድና ሰላማዊ ተቀላቅለው ሲሰለፉ፤ ማንም ሳይቀድመኝ የመጀመሪያው አባል ለመሆን ለሩጫዬ ተዘጋጅቻለሁ። ያንዳቸውም አባል አልነበርኩም። አሁን የሁሉም ልሆን ነው። ይህን ጥሩ ሥጦታ ከንቱ ላባክነው አልፈልግም።
ድሮውንም ሥልጣን በምንም ዓይነት መንገድ እንደማይለቅ ያሳወቀው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ በሰላም እየታገልን፤ አቤቱታችንን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እናሰማለን ያሉትን ሰላምተኞች፤ መፈናፈኛ አሳጥቶ አፍኗቸዋል። አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ፤ በራሱ የዕለት ተዕለት ሕግ ማውጣትና ማፈረስ ባህርይ፤ ሕጋዊ አይደላችሁም ብሎ አንዳንዶቹን እንዳይወዳደሩ፤ ሌሎችን ደግሞ ሰርጎ በመግባት የሱ ተቀጥላዎች እንዲሆኑ እየኮለኮላቸው ነው። ይህ ሁሉ ድካሙ የሚያሳየው፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ምን ያህል የኢትዮጵያን ሕዝብና ምርጫውን እንደሚፈራ ነው። ባለፈው ጊዜ ምርጫውን 99.6% አቸነፍኩ ያለ ፓርቲ፣ የሀገሪቱን ገንዘብ፣ መንግሥታዊ መዋቅርና የሰው ኃይል በሙሉ ለራሱ ምርጫ ያዋለ ፓርቲ፣ የምርጫ ቦርዱን በቁጥጥሩ ሥር ያደረገ ፓርቲ፣ ለምን ተወዳዳሪዎቹን እና ምርጫውን ይፈራዋል። ግልጽ ነው። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እምነት የለውም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ታጋዮች ደግሞ፤ አሁንም በሰላም መንገድ፤ ከመቼውም የበለጠ በመጠናከር፤ በገዥው ፓርቲ ፍላጎትና ሕገ-ደንብ ሳይሆን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ቆራጥነት ትግላቸውን ወደፊት ይገፉታል።
በሰላማዊ ትግል የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ሥልጣኑን ወዶ አይለቅምና በትጥቅ ትግል እንዝመትበት ለሚሉት፤ ይሄ በር አይከፍትም። የትጥቅ ትግል የራሱ የሆነ ሁኔታዎች አሉት። ይልቁንም ያሁኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መደናበር፤ ምን ያህል የሰላማዊውን ትግል እንደሚፈራውና እንዳይካሄድ ያለ የሌለ ጉልበቱን እንደሚያፈስበት ያስረዳናል። ለምን ብንል፤ የሕዝብ ድጋፍ የሌለው ስለሆነ ነው። የሕዝቡ ድጋፍ ከታጋዮች ጋር ነው። የሕዝቡ ድጋፍ ከሰላማዊ ታጋዮች በሆነበት ቦታ፤ ሰላማዊ ትግሉ ያብባል። ያድጋል። ይጎለብታል። የይስሙላ ግደባዎች አያቆሙትም። ጊዜያዊ አጥሮች የሚያዘገዩት አጥሮቹን እስኪያፈርሳቸው ድረስ ብቻ ነው። ሰላማዊ ታጋይ ድርጅቶች በምርጫዎች መሳተፍ አለባቸው። የሚሳተፉት ምርጫውን በመጠቀም ለሕዝቡ መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ፣ ምርጫው ምን ያህል ውሸት እንደሆነ ለማሳየት፣ ለሕዝቡ የትግል ተሳትፎ በር ለማስፋትና ለማሳደግ እንጂ፣ የፓርላማ ወንበር አሟቂዎችን ቁጥር ለማብዛት አይደለም። ይህ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት የሚመራው በፓርላማው ሳይሆን፤ በጀርባው ባስቀመጠው የጉልበት መዋቅሩ ነው።
በዚህ አሁን በሙሉ ኃይሉ እየተካሄደ ባለው ሰላማዊ ትግል ያገኘነው ዋናው ትምህርት፤ ይህ ትግል፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣኑ ባለቤት በማድረግ በኩል፤ የሚሳካው፤ መላ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት፤ በአንድ የትግል ማዕከል በሚመራ ትግል እንጂ፤ በተናጠል በሚደረግ ትግል አለመሆኑን ነው። መፍትሔ ለማምጣት በአንድነት መሰባሰብ፣ በአንድ ራዕይ መነሳትና መታገል ግድ መሆኑ ተስመረበት። ይህ እልል ያስብላል፤ ልንጠቀምበት ከቻልን።
በዚህ እየተደረገ ባለው ሰላማዊ ትግል፤ አንድ ዋና የኢትዮጵያዊያን ጠላት መኖሩን ተማርንበት። ትግሉ የሚያተኩረው የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣኑ ባለቤት ለማድረግ ነው። ለዚህ ደግሞ ዋናው ጠላት የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርና የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብቻ ነው። ሥልጣኑ በኢትዮጵያ ሕዝብ እጅ እንዲሆን፤ መላ ታጋዮች ባንድነት መታገል ያለባቸው መሆኑን ሁላችን እናውቃለን። እንዳይሰባሰቡ እስካሁን ያገዳቸው ምንም ሆን ምንም፤ አሁን ካሉበት ወጥተው ወደ ስብስቡ እንዲቀርቡ መንገዱ ግልጽ፣ በሩ ክፍት ሆኗል።
የታጋዮች ወደ አንድ መጠቃለልና ከድርጅቶች ሕልውና ይልቅ የሀገር ጉዳይ ቅድሚያ ማግኘቱ፤ የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያዊት ልብ እንደሚያንኳኳ ጥያቄ አያስፈልገውም። በሩጫ የመጀመሪያው አባል ለመሆን ግን የሚቀድመኝ እንዳይኖር ተዘጋጅቻለሁ። በርግጥ ብዙ እጅግ ብዙ ከኔ በፊት አባል ለመሆን እንደሚሽቀዳደሙ ጥርጥር የለኝም። ሁላችንም እልል እንበልና ለሩጫው እንዘጋጅ። እኔ ጫማዬን አጥልቄያለሁ። eske.meche@yahoo.com በሉ የዚህ ስብስብ ድርጅት አባል አብረን እንሁን።

በኢህአዴግ ለባርነት የተሸጠችው ወገን ሰቆቃ


ኢትዮጵያ - “ህጋዊ የኮንትራት ሰራተኛ”፤ ሳውዲ - የባሪያ ባሪያ!!
genet-a
ገነት አበበ ሞላ ትባላለች፤ የልጅነት ጊዜዋን ሩጣ ያልጠገበች በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ ኮረዳ ነች። ከዛሬ 3 አመት በፊት ነበር በኑሮ ውድነት የተጎሳቆሉ ቤትሰቦችዋን ከድህነት ለመታደግ በወቅቱ እስከ ገጠር በዘለቀው የአሰሪና ሰራተኛ የደላሎች ዘመቻ ከአርሲ ኮሌ ወረዳ ኩዬ ከተማ ተመልምላ የማይጨበጠውን የአረቡን ዓለም መከራ ለመጋፈጥ ተስፋ ሰንቃ ወደ ሳውዲ አረቢያ ያቀናቸው።
በወቅቱ በሰው ልጆች ህይወት ዶላር ለማግበስበስ በየአካባቢው በተከፈቱ የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲ ደላሎች ከእናቶቻቸው ጉያ ተነጥቀው ለአቅመ ሄዋን ያልደረሰውን እድሜዎቻቸውን ቆልለው ፓስፖርት የወሰዱ ህጻናት ሳይቀሩ በቀን 1500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች ያለህይወት ዋስትና ወደ ሳውዲ አረቢያ በጅምላ ይላኩ የነበረበት ወቅት በመሆኑ ወጣት ገነትም ሰው እንደሆነው እሆናለሁ ብላ በፌስታል የተሞሉ ልብሶቿን ይዛ የምትወዳቸውን ወላጆቿን በዕንባ የተሰናበተቸው። አንድም ቀን ከቤት ወጥታ የማታውቀውን ገነት አስረክበው ወደ ቀዬያቸው የተመለሱ ወላጆቿ የገነትን ድምጽ ቢናፍቁም ባህር አቋርጣ ሳውዲ ሄደች ከተባለ ወዲህ ወራት ተቆጥረው ዓመት ቢደፍንም ገነትን የበላ ጀብ አልጮህ አለ።
ወትሮስ ለማን አቤት ሊባል? “የገነትን ስቃይ ማን ይወቅላት?” ክፉ አጋጣሚ ሆኖ  በአሰሪዎቿ “ኃይል” ወደሚባል ገጠራማ የሳውዲ ግዛት ለስራ የተወሰደችው ገነት ወግ ባህሉ ቋንቋው ባዕድ በሆነባት ሃገር ሁሉም ነገር እንዳሰበቸው እና እንደተነገራት አልነበረም።  ታዲያ ገነት ከቤትሰቦቿ ጋር ስትለያይ ሲያነቡ የነበሩት አይኗቿ እንባ እንደቋጠሩ ነበር    ፍጹም ከባድ የሆነውን የአረቡን ዓለም የቤት ስራ የተጋፈጠቸው፡፡
genetበማለዳው ምናምን ቢጤ ቀማምሳ ለአመታት ተጠርጎ የማያውቀውን አቧራ የለበስና ቆሻሻ የተከመረበትን ግቢ ከአሰሪዎቿ በምልክት በተሰጣት ትዕዛዝ ስታፀዳና ከ4 ያላነሱ መኪኖችን ስታጥብ መዋል የዘወትር ተግባሯ ሆነ። በዚህ መልኩ ለወራት የተዋሃዳትን የአሰሪዎን የቤት ውስጥ ስራ ጨምሮ የማይመለክታትን ከባድ ስራዎች ሁሉ ካጠናቀቀች በኋላ ለሌላ አረብ ተላልፋ እየተሰጠች የቤት ሰራተኛ ለሌላቸው የሰፈሩ አረቦች ሁሉ አገልጋይ ሆናለች።
ገነት እረፍት የላትም እንደ ዘበኛ መኪና በመጣ ቁጠር የግቢ በር ትከፍታለች፤ የአሰሪዎቿን መኪናና ግቢ ታጥባለች፤ ከባድና ቀላል የሆኑ እቃዎችን እስከ 3ኛ ፎቅ ተሸክማ በመውጣት ከአቅም በላይ የሆነና የማይመለከታትን ስራ በግዳጅ እንድትሰራ ትደረጋለች። ከቤተሰቦቿ ከተለየች ወዲህ በስልክ ወላጆቿን አግኝታቸው የማታውቀው ገነት ከሥራው ክብደት ይልቅ በናፍቆት ከሰውነት ጎዳና የወጣው አካሏና የልጅነት ወዝ በቁም የተገነዘች ሬሳ አስመስሏታል፡፡
በአስሪዎቿ ታግት በደል የሚፈጸምባት ገነት አበበ ሞላ ከሚፈፀምባት ግፍ እና በደል  እግር ወደ መራት በመሄድ እርሷን ከባርነት ለመታደግ የሞከረችበትም አጋጣሚ እንደነበር ይነገራል። ከዚያ ወዲህ ገነትን ለማግባባት ብዙ ሞክረው እንዳልተሳካላቸው የተረዱት አሰሪዎቿ ገነት ላይ የሚያደርጉትን ክትትል በማጠናከር የስራ ግዳጅዋን ስትጨርስ ባዶ ቤት ይቆለፉባታል። የቤት ሰራተኛ እጥረት የገጠማት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በአሰሪዎቿ የታገተቸው ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ገነት አበበ ለአሰሪዎቿ እያበረከተች ካለው ነጻ አገልግሎት ባሻገር በወር እስከ 3800 በሚደርስ ክፍያ ለሦስተኛ ወገን ተላልፋ በመሰጠት ጥሩ የገቢ ምንጭ እስከ መሆን መድረሷ ይነገራል። ከአንዱ የአረብ መኖሪያ ወደ ሌላው የአረብ መኖሪያ ቤት እየተቀባበሉ ያለ በቂ እረፍት የአረብ አገልጋይ ለመሆን የተገደደቸውን ኢትዮጵያዊት “የኮንትራት ሰራተኛ” ከማለት ይልቅ በኢህአዴግ ህጋዊ ፈቃድ አግኝቶ በሚንቀሳቀስ አሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ የተሸጠች ባሪያ ማለት ይቀላል።
አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ ሴብሪን “sebirn” እየተባለ በሚጠራ አንድ ኤጀንሲ አማካኝነት ተዋውላ “ህጋዊ” በሆነ መንገድ ለስራ ሳውዲ እንደገባች የሚነገርላት ገነት ዛሬም የድረሱልኝ የሰቆቃ ድምጽዋን ታሰማለች – የሚሰማት ካገኘች!
አሁን አሁን ለህይወቷ የምትሳሳው ገነት ይገሉኛል በሚል ስጋት በድብደባ ከተጎሳቆለው አካሏ ባሻገር ሌሎች ምስጢራዊ በደሎችን ለግዜው ከመግለጽ መቆጠቧን ለልጅቷ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይገልጻሉ። እነዚህ ወገኖች አቤቱታቸውን በጅዳ ለኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ቢገልጹም እስክ አሁን የገነት የሰቆቃ ድምጽ ምላሽ አላገኘም፡፡
ሰሞኑን በደመወዝ ጥያቄ በጥይት የቆሰለችውን ኢትዮጵያዊት ከወራት ቆይታ በኋላም ቢሆን እውነታውን በአካል ሄደው ያረጋገጡት የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ሃላፊዎች የሰቆቃ ድምጽ ለምታሰማው ወጣት ገነት አበበ ሞላ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ይጠበቅባቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ በዚህ መልኩ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ እንደ ጨው ተበትነው ያሉበት ሁኔታ በውል የማይታወቅ ግፍ እና በደል እያስተናገዱ የሚገኙ እህቶች መኖራቸው በተደጋጋሚ ተገልጾል። (Ethiopian Hagere Jed Bewadi)

Ethiopia shall overcome

(Yilma Bekele)
struggle
In May of 2005 the noble idea of bringing change by peaceful means died a violent death in Ethiopia. The Tigrai People Front declared in no uncertain terms power sharing is not part of the equation. They have proved it three times since then. What part of that do we have a problem accepting?
The TPLF party does not just whisper. They shout so loud that the whole body shakes from the vibration caused by the violent, vile and wild savage scream.
That did not stop well-meaning and brave Ethiopians from trying to convince the mafia crowed to reconsider their ugly ways. Like a clock work the Tigrai Liberation Front in power strikes back in a savage manner. Every time it is something old, something new and something different. The intent is to scare, punish and humiliate. Ato Meles used to get a report on the condition of his prisoners including their diet. He mentioned it during one of his press conferences regarding the weight of Andenet’s Chairperson he has in prison. That is how sick the deprived mafia group are like.
The Tigrai Front has been busy this election season. First they created a clone of Andenet and banned the real Andenet. Andenet members joined Semayawi or Blue party in mass and continued their political activities. They refused to go home quiet.
The Tigrai liberation Front has a new answer to this dilemma. They denied the candidacy of Chairman Yelkal Getahune of Semayawi Party in his district. How did they do that? They created a lottery system to fill the allotted number of candidates for the seat. Of course his name was not drawn. A very simple solution backed by the courts, security apparatus and their very own custom made and drawn to fit Constitution.
Both Andenet and Semayawi Party are legally registered political parties and everything they do is above board and designed to win the hearts and minds of the Ethiopian people so they can vote them in to office. You cannot be more legal than that. Their conviction to take it to the limit despite the daily violence and constant threat to the individuals and their families is a testament to the conviction and strength of their character.
The Tigrai Liberation Front to no one’s surprise is finding itself boxed in. It is referred to as catch 22. It is the paradoxical situation our Woyane friends are caught in. They have to repress violently to stay in power but the violence creates more determined enemies necessitating more violence on their part that breeds focused and cunning enemies. Time is against the Front. Violence and repression is the only trick they got in their survival bag and it is not a lasting tool to stay in power. Ask Mengistu, ask Mubarak, ask Assad, they will tell you.
The question is what are the victims doing about this injustice? Right now we are witnessing different responses from those affected by this virus. There is Semayawi and Andenet parties that have been trying to play by the rules but are faced with a brick wall with barbed wire. They are constantly resetting their response. There is Ginbot7 which has merged with Patriotic front that has resolved to do what is necessary to achieve freedom and smash the wall. The combined forces of the two is harbinger of things to come. The battle can be fought on many fronts as the number of combatants’ increases.
We also have Medrek trying to climb two trees because they have two legs. They have been attempting to do that the last four years and the fact that it is not possible has not discouraged them. They have become Tigrai fronts loyal opposition allowed to give the show some needed color. Some of Medreks leaders have been at this job of serving the Front since 2005. Remember they are the ones spared of Kaliti after Ato Meles’s riot. God knows how they dare face the Ethiopian people but due to our culture and history constantly being degraded the concept of shame has disappeared from our vocabulary.
The Tigrai Liberation Front is not alone in this quest to dominate and perpetuate their form of ethnic based democracy. Twenty years have given them plenty of time to experiment with all sorts of formula to perfect their impossible dream of building an independent Tigrai, create a dynasty to leave something behind for their children or if all fails to leave a legacy of disintegrating Ethiopia branded as a failed state.
The Western enablers couldn’t care less if Tigrai Liberation Front survives or not. Their concern is having a stable but friendly Ethiopia and they would work with whoever emerges from this mess. Right now the notorious organization is the only one that is delivering the promise of stable and puppet on a leash Ethiopia.
More than the Western enablers it is the Ethiopians themselves that are scrambling over each other’s dead body to stand behind the ethnic regime. Inside the country those organized under the banner of EPDRF are the main foot soldiers of the Front. They furnish the human resource to make such criminality possible.
The Liberation Front masquerading as a government is not going to go away. On the other hand the longer it stays in power the harder it would be to recover from the disaster that is surely to follow its demise. If is not the question it is when we should worry about. The ethnic issue relentlessly fertilized by the Front is the most dangerous to handle.
Right now the situation in Ethiopia is quiet but smoldering. The Tigrai front is using all its resources to convince the captive population the sun would not rise in Ethiopia without them in power. The country is awash with both carrot and stick. The sacred ‘Dedebit’ has been put on display to show the sacrifice and heroism of the Woyane warriors. Such notable bloogers as Daniel Berhane have been taken on a friendly tour accompanied with ambulances to tell us about the historic site. We are instructed to be thankful.
The equality of kilils organized on ethnic basis and referred to as ‘Nation nationalities’ is of course a major accomplishment by our benefactor the Tigrai liberation Front and the poor grateful citizens are brought out for display. As usual something unexpected happened. An audio of the pep talk given was made available to the rest of us.
The speaker was Abay Tsehaye a founding member of TPLF (ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) and a non-elected official with power. Abay is one of those Woyane that wield considerable power always from the back ground. He is Chairman of Commercial bank of Ethiopia, Minster of Federal affairs and board member of EFFORT among others. This notorious terrorist is the one that planed the destruction of Waldeba Monastery to grow sugar. His domain includes the Police force and Administration of Addis Abeba.
The leaked audio is a perfect example of what is wrong with Ethiopia and Ethiopians. This non-elected official was heard lecturing the Oromo puppets serving him to hurry up with the taking of land or else face the wrath of the Front. His language was harsh his tone was dismissive, and his threat left nothing to the imagination. When you consider OPDO the Oromo ethnic party to be equal to TPLF on paper this audio shows how disgraceful this unequal relationship has always been. Don’t worry the Amhara, Gambella, or Sidama puppets do not fare any better.
Semayawi and Andenet parties are evaluating their next move. Under the dire circumstances they are finding themselves in they are still doing all they could to live free or die trying. They might not achieve their goal but all of us are in awe of their conviction and we all go to bed praying for our God to give them strength. No one can say they died of a coward’s death. No one can say they sold their country and honor for power and money. No matter what happens today we all know that by standing up for what is right they have already won.
Patriotic Front and Ginbot7 have been preparing their forces. It takes time and patience to confront such a criminal regime that uses all resources to fight the last battle. Today we feel empowered to think there is a group that is ready to speak with Woyane in the language they know and understand. Some of us are very impatient. It is understandable. But it is always better to be cautious and prudent when facing such an enemy that feels cornered. They can afford to sacrifice hundreds of combatants for every one of our brave solders. Remember the war the waged with Eritrea. We lost over eighty thousand while Eritrea sacrificed just twenty thousand. That is how Woyane operates.
It would really help if the large force of the Diaspora could join this battle for liberation. It would be considered a game changer. It would lesson our sacrifice. Unfortunately Ethiopia’s children are not as they used to be. Their culture has been watered down so much they have turned into nomads. We have become ghosts of our past. Today we are supplied the best Teff while our people are starving, we receive ready-made Enset while it is a luxury item at home, the Berbere and Mitmita the Shuro and the raw coffee is the envy of every merchant in Ethiopia. Come to any city USA and you can see the stores overflowing with stolen products from our people.
The Diaspora makes Woyane possible. The Diaspora has become the outside Medrek. They both complain about the injustice of Woyane but both sit under the feet of Tigrai Liberation Front waiting for crumbs to fall. Abbay Tsehaye, Debre Tsion, Bereket Simon, Sebhat Nega all laugh at us and the Western enablers shake their head when they see such degradation and willing acceptance of servitude.
Here in the USA we celebrated the struggle of our African people for justice and equality that was waged fifty years back. I am sure plenty of Ethiopians stood tall and proud by the accomplishments of our African Diaspora led by martin Luther King and others. I ask you a question my dear reader what do you think the outcome would have been if MLK was preaching to Ethiopians? Do you think the Montgomery bus boycott would have succeeded? Do you think the march from Selma to Montgomery would be celebrated today?
The answer to both would be no. All you have to do is look at Ethiopian (Woyane) Airlines and see what boycott is all about. You just need to visit Ethiopian restaurants and see the meaning of boycott written all over the menu. Pure Injera, tasty Kocho from Sidama and Ethiopian Beer is our answer to boycott. Go ahead climb two trees because you have two legs like Medrek is doing, please continue condemning Woyane with a loud voice for all to hear but do not forget to build your condominium on stolen land. Rage all you want against ethnic politics but do not forget to shed crocodile tears for the disintegration of our mother land.
Today all our newspapers and web sites are full of the daily injustice committed by the enemy. Every news item you read is a reminder that we are powerless, leaderless and sinking fast as people and country. You see that and naturally conclude the might Woyane is bigger than life. Most Ethiopians let alone at home even in the Diaspora are scared stiff when thinking about Woyane. The fear they created has frozen our thinking and sapped our energy and made us feeble.
It is up to each one of us to get out of this defeatist mind set. Our news media should strive to empower us. There are so many good things our people are accomplishing to help each other under dire circumstances and that is what we should talk about. Pretty soon we will celebrate our own victories but shouldn’t we start preparing our mind to tackle the heavy work that is awaiting us when we smash the evil empire. That is how we help Semayawi and Andenet. That is how we encourage Patriotic Front Ginbot7 to hasten their preparations. We know we are going to win. Good always triumphs over evil and it is no different this time around.  A Luta continua-the struggle continues.
Source: goolgule

Sunday, March 1, 2015

Facts and Documents on Case of Zone9 Bloggers and Journalists

After nine months continuous appearance to the federal High court 19th criminal bench for 20 times the court finally have decided to hear evidence by the prosecution. The evidence hearing will start on march 30 for 3 consecutive days. with in the last nine months
- 87 days of interrogation had been conducted on all nine detainees.
- The charges had been amended twice, and totally three charges had been presented against the ten bloggers(one in absentia) and journalists
- Zone 9 Bloggers and Journalists appeared to the court 20 times
- Female detainees could not be visited by friends and relatives. their visit is restricted to 6 persons and only for 20 min in a day.
- Two family members/ friends had been temporarily detained by security officers because they have attempted to take picture of the detainees in the court compound not in the court room.
- In all court appearances the bloggers and journalists have seen with smile and strong spirits.
- The defendants asked the presiding judge to be replace for the reason he showed bias during the trials, which was denied by the court.
- More than 85% of the evidence used against the defendants is articles from their blogs and campaign statements.
- their case has been presented for the UN working group on arbitrary detention
The following are the main documents which helps to understand the charges and the evidence presented.

አሁንም ደግመን እንነግራችኋለን

pg7-logoኢትዮጵያችን እግዚአብሔርንና ሰውን በማይፈሩ ጨካኞች እጅ ወድቃ የመከራ አገር ከሆነች ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። በህዝባችን ላይ የተመዘዘው የመከራ ሰይፍም ወደ ሰገባው የሚመለስ አልሆነም። እንዲያውም በህዝባችን ላይ ሲዘንብ የቆየው የመከራ መንፈስ እንደገና ታድሶ ገና “ልክ እናስገባችኋለን” የሚል የጣዕረ ሞት ድምፅ ከህወሃት መንደር እየተሰማ ነው።
አባይ ፀሃይ የሚባለው ወላዋይና አደር ባይ ግለሰብ በህዝቡ ላይ ሲፈፅመው በኖረው ወንጀል ገና የረካ አይመስልም። ሌላ ግዲያ፤ ሌላ ስደት፤ ሌላ የላቀ መከራ ለኢትዮጵያዊያን ደግሶላቸዋል። አባይ ፀሃይ ለአዲስ አበባ ከተማ ልቀት እርሱ ብቻ አሳቢ፤ እርሱ ብቻ ተቆርቋሪ ሁኖ ራሱን ሹሟል።የአዲስ አበባም ሆነ በአካባቢው የሚኖረው ኗሪ ህዝብ ግን አባይ ፀሃይን የሚያውቁት በእኩይ ተግባሩ እንጂ በደግ ተግባሩ እንዳለሆነ እኛ ልናስታውሰው እንወዳለን። በዚህ ግለሰብ አማካሪነት የተጀመረው ኗሪውን ህዝብ የማፈናቀል፤ ቤተሰብን የመበተን፤ የህዝቡን አብሮነት የማፍረስ ተግባር ገና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል “ገና ልክ እናስገባችኋለን” በሚል መፈክር ሥር እንደሚቀጥል ታቅዷል። አዲስ አበባን በማስፋፋት ሰበብ ብዙ ገበሬዎች ከኖሩበት መንደር ያለምንም ካሳ ተፈናቅለው የሌላ ሎሌ እንዲሆኑ መደረጉ የሚረሳ አይደለም። ይሄን የአንድን ህዝብ ማንነት የማጥፋት ድርጊትን የተቃወሙ ብዙ ወጣቶች በሞት እና በእሥራት እንደተቀጡም አረሳነውም። ትላንት የፈሰሰው ደም ሳይደርቅ፤ የፈሰሰው እንባ ሳይታበስ፤የተበተነው ሳይሰበሰብ፤ የተሰበረው ሳይጠገን እንደገና ለሌላ ዙር ጥፋት እየተዘጋጁ እንደሆነ ነግረውናል።
አባይ ፀሃይ “ልክ እናስገባችኋለን” ሲል የተማመነው ጠመንጃ ያነገተውን ኢትዮጵያዊ ወታደር እንጂ ህዝብን እንዳልሆነ እናውቃለን። ወታደር አገሩን መጠበቅ፤ ህዝቡንም ከጥፋት መታደግ፤ አጠቃላይ የአገሪቷን ህግም ማስከበር ዋናው ተልዕኮው ነበር። የአገራችን ወታደሮች ግን ዋናውን ተልእኳቸውን ትተው ኢትዮጵያን እንደ አገር እንዳትቀጥል የሚያደርጉ ቡድኖችን እድሜያቸውን ለማራዘም እየሰሩ እንደሆነ እያየን ነው።በአገራችን ጠመንጃ የታጠቁ ኃይሎች መከላከያ ኃይል አባላት፤ የፖሊስ አባላት፤ የፌዴራል ፖሊስ አባላት እና በአገራችን ታሪክ በነፍሰ ገዳይነቱ የሚታወቀው አግዓዚ የተባለው ክፍለ ጦር አባላት እና የአገር ውስጥ ደህንነት አባላት የህወሃትን ዕድሜ ለማራዘም ከልብ የመነጨ ፍላጎት አላቸው ብለን አናምንም። እነዚህ ኃይሎች የወጡበትን ጎጆ፤ ነገ ዞሮ መግቢያ የሚሆናቸውን ማህበረሰብ ወደውና ፈቅደው ያፈርሳሉ ብለን ለማሰብ ይቸግረናል።በሌላ በኩል ደግሞ ድርጊታቸው ብዙዎችን እያስከፋ እንደሆነም እናውቃለን።
አሁንም ደግመን ደጋግመን በኢትዮጵያችን ጠመንጃ ላነገቱ ኃይሎች መልዕክት መላካችንን አናቋርጥም። ጠመንጃውን ያነገቱ ኃይሎች ካነገቱት ጠመንጃ የተለዩ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ስሜት አሏቸው፤ ፍላጎት አሏቸው፤ ማሰብ የሚችል አዕምሮም እንዳሏቸውም የሚካድ አይደለም።የሚያዝንና የሚደሰት ስሜት፤ ለመኖር ፍላጎት፤ በጎውን ከክፉ ለመለየት የሚያስችል አዕምሮ ያሏቸው ስለሆነ ፈፅሞ እስከ ሚመሽ ድረስ መልዕክታችንን ከመስደድ አናቆምም። መልዕክታችንም አጭርና ግልፅ ነው። በዚያች አገር ውስጥ ጠመንጃ የታጠቀው ኃይል ጋር ጠላትነት የለንም።በእኛ እምነት መከላከያ ኃይል፤ ፖሊስ እና የደህንነት ሠራተኞች ጠላቶቻችን አይደሉም። እኛ ጠላት የምንለው ጠመንጃ የታጠቀውን ድሃ እና ከርታታ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ይህን ኃይል በገዛ ወገኑ ላይ ሰይፉን እንዲመዝ እና የንፁሃንን ደም እንዲያፈስ የሚያደርገውን ኃይል ነው።የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ለተሻለ ውጤት የሚያበቃው አማራጭ ስለሌለው ሂሊናው እየወቀሰውም ቢሆን የገዛ ወገኑን ደም እያፈሰሰ ለመቆየት የተገደደ ይመስላል። ይህን ማለታችን የድርጊቱን መፈፀም ትክክል ነው እያልን አይደለም። በማንኛውም መለኪያ የንፁህ ሰውን ደም ማፍሰስ ትክክል አይደለም። በሰማይ በእግዚአብሄር ፊት የሚያስጠይቅ፤ በምድር በሰው ዘንድም የሚያስወቅስ ክፉ ተግባር መሆኑን ሳንናገር አናልፍም።
እስከ ዛሬ የተሻለ መረጃ ስለሌለኝ፤ የተሻለ አማራጭ ስላጣሁ፤ የተሻለን መንገድ ለመፈለግ ሁኔታው ስላልፈቀደልኝ ከሂሊናየ ውጪ ሁኜ ለመኖር ተገድጄአለሁ የሚለው ምክንያት አሁን አብቅቷል። አሁን መረጃ አለ፤ ኢትዮጵያን እንደ አገር እንድትቀጥል ለማስቻል የተሻለ አማራጭም አሁን ተዘጋጅቷል። መረጃና አማራጭ መንገድ ካለ ደግሞ ከሂሊና ጋር ታርቆ እንደ ሰው ለመኖር ሁኔታው የተመቸ ሁኗል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፤ የፖሊስ ሠራዊት አባላት፤የአገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎች ሆይ ስሙን !
ህወሃቶች እናንተን ተገን አድርገው የገዛ ወገኖቻችሁን “ልክ እናስገባለን” ማለታቸውን ሰምታችኋል የሚል ግምት አለን። ልክ ማስገባት ማለት-ከሥራ ማባረር፤ከትውልድ ሥፍራ ማፈናቀል፤ እስር ቤት መጨመር፤ ለስደት መዳረግ እና መግደል ማለት ነው። የአባይ ፀሃይ ልክ ማስገባት ይሄን ይመስላል።ይሄን የምትፈፅሙት ደግሞ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች ትሆናላችሁ። ወገኖቻችሁ በህወሃቶች እጅ እንባቸውን በመዳፋቸው ሲያፍሱ ኑረዋል።በህወሃት አገዛዝ ሥር ያለች አገራችሁ ከውዳቂ አገራት ተርታ ገብታለች፤ ከዓለም አስር ፍፁም ድሃ አገሮች መካከል አንዷ ሁናለች።የአገራችሁ ወጣቶች ሞትን ፊት ለፊታቸው እያዩ ተሰደው የዓዞና የበርሃ ዕራት ሁነው ቀርተዋል። ከዚህ የተረፉትም የዓረብ መጫወቻ ሁነዋል። ይህ ሁሉ መከራ ህወሃት በተባለው ክፉ ዘረኛና ቂመኛ ቡድን ይፈፀማል። አሁን ይሄን በቃ ለማለት ግዜው ነው። ከእንግዲህ ወዲያ ታዝዤ ነው፤ ለእንጀራ ብየ ነው፤ ልጆቼን ላሳድግ ብየ ነው፤ አማራጭ አጥቼ ነው፤ የሚሉ ምክንያቶች ሚዛን የሚያነሱ ባለመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም።
አሁን አስተማማኝ አማራጭ አለ። የኢትዮጵያ ውረደት ያንገበገበን፤ የህዝባችን ጉስቁልና ያስቆጨን ወገኖች የአያቶቻችንን ጋሻና ጦር አንስተን ለግዳጅ ተዘጋጅተናል። ከመቸውም ግዜ በተሻለ ህዝባዊ መሠረት ላይ የቆመ ድርጅት መሥርተን ንቅናቄ ጀምረናል። ትግላችን ኢትዮጵያዊያን ከተዘፈቁበት ጭለማ ወደ ብርሃን የሚያሻግር ነው። ትግላችን ህወሃት የጫነውን የዘረኝነት ቀንበር የሚሰብር ነው። ትግላችን ህወሃት የዘረጋውን የዝርፊያ መረብ የሚበጣጥስ ነው። ትግላችን ህዝቡን በሙሉ የተጫኑ ጥቂት መንደርተኞች ሥፍራቸውን እንዲይዙ ማድረግ ነው።ትግላችን ጎጠኛ አስተሳሰብን አምክኖ ብሄራዊ ስሜትንና ውህደትን የሚፈጥር ነው። ትግላችን ዜጎች በዜግነታቸው ብቻ በኢትዮጵያ ውስጥ በማንኛውም ሥፍራ ያለ ፍርሃት የሚኖሩበትን ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን አብዛኛው ህዝብ በመረጠው መንግስት የሚተዳደርበት፤ ይህም መንግስት ህዝቡን ፈርቶና አክብሮ የሚሠራበት ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አገሩንና ህዝቡን የሚጠብቅ እንጂ የገዛ ወገኑን ደም በከንቱ የሚያፈስበት ሁኔታ እንዲያበቃ የሚያደርግ ነው።ጠመንጃውን ያንገትከው ኃይል የቀረበልህ አማራጭ መሥመር ይሄ ነው።
ደግመን እንነግርሃለን አሁን አማራጭ መንገድ አለህ። በገዛ ወገኖችህ ላይ ስይፍህን ለመምዘዝ እምቢ የማትል ከሆነና አሁንም በዚያው በጭለማ መንገድ መሄድን ከመርጥክ መጨረሻህ መልካም አይሆንም። እኛ እንድሆንን ተነስተናል። ከመንገዳችን የሚያቆመን ምዳራዊ ኃይል አይኖርም።የቃየል ልጆች ሲያጠፉን እንዲያው ዝም ብለን የምንጠፋ አይደለንም።ከእኛ ዘንድ እውነት አለ፤ ከእኛ ዘንድ የነፃነት ብርሃን አለ፤ ከእኛ ዘንድ የፍትህ ዘንግ አለ፤ከእኛ ዘንድ የእኩልነት ሚዛን አለ፤ ከእኛ ዘንድ እግዚአብሄር አለ።ይሄን ሁሉ ይዘን እናሸንፋለን እንጂ አንሸነፍም።የምናሸንፈው ለበቀል እንዳይደለ አሁንም እንነግራችኋለን። የምናሸንፈው በክፉው ላይ መልካሙን ዘር በመዝራት ነው።በጭቆና ላይ ነፃነትን፤ በአድልዎ ላይ ፍትህን፤ በህግ አልባነት ላይ የህግ የበላይነትን፤ በጎጠኛ አስተሳሰብ ላይ ብሄራዊ አስተሳሰብን ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። የጎሰኛነትን አጥር አፍርሰን የኢትዮጵያዊነት ስሜት ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። እኛ ስናሸነፍ የሚሆነው ይሄው ነው። ከእኛ ዘንድ የበቀል ስሜት የለም። ከእኛ ዘንድ ያለው ሁሉም ከህግ በታች ሁኖ ህግና ፍትህ እንዲነግሱ የሚያስችል ብርቱ ፍላጎት ነው።
ስለዚህ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች እኛ ከቆምንለት ቅዱስ ዓላማ ጋር እንድትተባበሩ እንጠራችኋለን።ኑና የጭለማ ኃይሎችን ምሽግ አፍርሰን የብርሃን ልጆችን አምባ አብረን እንሥራ። ኑና አብረን የወገኖቻችንን እምባ እናብስ። ኑና በግፍ ያለፍርድ የታሠሩትን እናስፈታ ።ኑና የጭቆናን ቀንበር አብረን እንስበር። ኑና አብረን አገራችንን ከፍ ከፍ እናድርጋት።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!